Tuesday, July 23, 2013

የዘር ፖለቲካ የትም አያደርሰንም!!

ለዚህ ፁሁፍ መንደርደሪያ የሆነኝ በፌስቡክ ግድግዳላይ ተፅፎ ያየሁት አስታያት ወይም commentመነሻነት ነው
ኢትዮ ጵያ ገደል ትግባ የሚል ፁሁፍ አይቼነው በእውነት ለመናገር ቆሽትዬ ነው የደበነው በርግጥ ይህን ግለስብ
ለዚ አባባሉ ያስነሳው ዓብይ ምክንያት ሰሞኑን በሶሻል ሚዲያው ላይ ትልቅ አነጋጋሪ የሆነውን የንግግር መንሽራተት
ወይም የአፍወለምታነው የግለሰቡ የንግግር ስተት ምናልባት አንድ ቀን ወደ ራሱ ቀልብ ሲመጣ በይቅርታ ሊስተካከል
ይችል ይሆናል ሆኖም ገን ትልቋን ኢትዮጵያ ገደል ትግባያለውን ነው የሶስት ሺ ዘመን ታሪክ ያላትን፣ የመጀመሪያ
የሰውልጅ ዘር መገኛ የሆነችውን፣በጀግንነትና  ለመላው የጥቁር ህዝብ የነፃነት ተምሳሌትና ኩራት የሆነችውን
 በቅዱስ መፃሀፍ ውስጥ 40 ጊዜ የተገለፀች ኢትዮጵያ እጆቿን ወደ እግዛብሔር ትዘርጋለች ተብሎ የተጻፈላት
እውን ነብር ዥንጉርጉርነቱን ኢትዮጵያዊ ኢትዮጵያዊነቱን አይለውጥም የተባለለት።
       እንግዲ ኢትዮጵያ ስንል የትኛዋን ኢትዮጵያ ነው፧
እስቲ ያሳያቹሁ የትግራይ ህዝብ እጆቹን ወደ እግዛብሔር፣የኦሮሞ ህዝብ እጆቹን ወደ እግዛብሔር ፣የአማራ ህዝብ
እጆቹን ወደ እግዛብሔር ወይም ሌሎችም ብሄር ብሄርሰቦች እጆቻቸውን ወደ እግዛብሔር ይዘርጋሉ እንኳን ተብሎ
አልተጻፈም ወይም አልትገለጸም ሰለዚህ እምዬ ኢትዮጵያ ማለት የነዚህ ሁሉ ብሄር ብሄረሰቦች የድምር ውጤት መሆኖን
መገንዘብና ማወቅ አለብን ።
      በታሪክ እንደምንረዳው በነብዩ ማህመድ ፍት ህና ሰላም ታገኛላቹሁ ተብለው ወደ ኢትዮጵያ ሂዱነው ተብለው
የተሰደዱባት ከዚህም የተነሳ ኢትዮጵያኖችን አትንኮቸው ነው የተባለው እንደውም በታሪክ የመጀመሪያ የስደተኛ
ተቀባይ አገር ሊያስብለን ይችል ይሆናል።
   ስለዚህ ሁላችንም የወያኔ አገዛዝ የጠላናቸውና የምንታገላቸው በጠባብነታቸው ዘረኝነታቸው ነው እንጂ
አንዳንዶች እንደሚሉት ከሰሜን ሰለመጡ ወይም የትግሪኛ ቋንቋ በመናገራቸው አይደለም በአንደኛ ደርጃ
አገሪቶን እያስተዳደሩ ያሉት ገዥዎቻችን የኢትዮጵያዊነት ደም ወይም ሞራል ፣ፍቅር ስሌላቸው ነው
የሁላችንም ትኩረት መሆን ያለበት የሁላችን ጠላት ወደሆነው ወደ ወያኔ ከፋፋይና ጎጠኛ መንገስት ነው
የችግሮቻችን መፍትሄ የሚገኙት በመነጋገር፣ በመግባባት፣በመቻቻል፣በመደማመጥ እንጂ በመሰዳደብ በዘርኝነት
የትም አንደርስም ።
    ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!!!!!!
     ዳዊት ወንድሙ!!!!!!!!

No comments:

Post a Comment