Friday, January 31, 2014

ወያኔን ያሸበረው የግንቦት 7 መንገድ ምንድነው?

የትግራይን ሕዝብ ከብሄር ጭቆና ነጻ አወጣለሁ በሚል ጠባብ ዓላማ ተደራጅቶና ታጥቆ ለበትረ ሥልጣን የበቃው ህወሃት ወይም ሕዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ ሥልጣን ከተቆጣጠረ 23 አመት ሊሞላው እነሆ ጥቂት ወራቶች ብቻ ቀርተውታል።
ለጋራ ቤታችን ለሆነቺው አገራችን ኢትዮጵያና በአስተዳደር በደል ለከፋ ድህነት ለተዳረገው መላው ሕዝቦቿ የሚሆን አንዳችም ራዕይ ሳይኖረው ለመንግሥትነት ሥልጣን የበቃው ይህ ቡድን ላለፉት 23 ዓመታት ከግል ኑሮአቸው አሻግረው የአገርንና የወገንን ጥቅም ማየት የማይችሉ ወይም የማይፈልጉትን በዙሪያው አሰባስቦ እያካሄደ ካለው ዘርፈ ብዙ የሃብት ምዝበራ ወንጀል በተጨማሪ እየፈጸመ ያለው የመብት ጥሰትና አፈና ተዘርዝሮ የሚያልቅ አይደለም።
ሰሞኑን እያፈተለኩ በመውጣት ላይ ከሚገኙ ምስጥራዊ የድምጽ መረጃዎች ለማረጋገጥ እንደተቻለው ደግሞ ለጥቂቶች የሃብትና የብልጽግና ምንጭ የሆነው ሥልጣን ከእጃቸው እንዳይወጣ በአንድ በኩል በምርጫ ስም እንዴት አድርገው ሕዝቡን ቀፍድደው የምርጫው ተሳታፊ ማድረግ እንደሚችሉ ሲዶልቱና በሌላ በኩል ደግሞ በቁጥጥራቸው ሥር የሌሉትንና ለሥልጣናቸው ያሰጉናል ያሉዋቸውን የደሃዉን ልጅ በማጋፈጥ እንዴት በጦርነት እንደሚጨፈልቁዋቸው ሲመክሩ ተሰምተዋል።
ከወያኔው ቁንጮ አንዱ የሆነው በረከት ስሞን በየደረጃው ላሉት የአገዛዙ ሹሞችና ካድሬዎች ባደረገው ገለፃ መሬትን የመንግሥት ባደረገው ኮሚኒስታዊ አዋጅ ምክንያት የመንግሥት ጭሰኛ ለመሆን የተፈረደበትን ሰፊውን አርሶ አደር “ተኛ ስንለው ይተኛል፤ ቁም ስንለው ይቆማል ፤ እንደፈለግን ብንበድለው እንኳ አያማርረንም ” እያለ ሲዘባበትበት ተደምጦአል ። በአንድ ለአምስት ኮሚንስታዊ አደረጃጀት ተጠርንፎ የወያኔ የንግድ ድርጅቶች ብቻ የሚያቀርቡትን ማዳበሪያና ምርጥ ዘር ያለውዴታው እንዲራገፍበትና ከአቅሙ በላይ ዕዳ እንዲቀፈቅፍ የተፈረደበት የኢትዮጵያ አርሶ አደር በዚህ አይነት ንቀት ደረጃ የሚዘባበትበትን መሪ ከወያኔው በረከት ስሞን በፊት ገጥሞት አያውቅም ። ለወደፊትም ሊያይ አይፈልግም ። ወያኔን ሥልጣን ላይ ለማምጣት የሰሜኑ ክፍለአገራችን አርሶ አደር የተጫወተው ሚና ተዘንግቶ በበረከት ስሞን እንዲህ መዋረዱ እጅግ ያሳዝናል። ለነገሩ ከፍተኛ የህይወት መስዋዕትነት ከፍሎ ለድል ያበቃው የትግራይ ሕዝብ ቁም ስቅሉን እያየ አይደል?
ሌላው አስገራሚ ክስተት በአገር ደህንነት ሥራ ላይ የተሰማሩ ዜጎች ባደረጉት ዝግ ስብሰባ ታማኝነታችን ለአገራችን ነው ወይስ የሥርዓቱን አገዛዝ ዕድሜ ለማራዘም? ብለው ላነሱት ጥያቄ የጠቅላይ ሚንስትር ተብዬው የህግ አማካሪ ጌታቸው ረዳ የሰጠው መልስ ነው። ደህንነት ብቻ ሳይሆን የመከላኪያ ሠራዊትና ፖሊስ ጭማር ታማኝነታቸውና ግዴታቸው ሥርዓቱን ሥልጣን ላይ ማቆየት መሆን አለበት ሲል ጌታቸው እንቅቹን ነግሮአቸዋል ። በምላሹ “ላለፉት 23 አመታት እያደረግነው ያለው ይሄው ሆኖ ሳለ አሁን ምን ብታስቡ ነው ጥያቄ ያነሳችሁ?” የሚል ይመስላል ። ይባስ ብሎም ሥርአቱን ለመጠበቅ ያልቻለና በግንቦት 7 መንገድ የሚጓዝ ደህንነት ሠራተኛ የተስፋየ ገብረስላሴን ያህል የደህንነት እውቀት ቢኖረውም ሆነ እስራኤል አገር የዓመታት ስልጠና ያገኘ ቢሆን ዋጋ የለውም ብሏቸዋል።
ለመሆኑ ወያኔዎች እንደመርገም የቆጠሩትና ተከታዮቻቸውን የሚያስፈራሩበት የግንቦት 7 መንገድ ምንድ ነው።?
ግንቦት 7 የፍትህና፤ የነጻነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ አገራችን ኢትዮጵያ የእያንዳንዱ ዜጋ ዴሞክራሲያዊና ሰብዓዊ መብት የተከበረባት፤ የኢኮኖሚ ብልፅግናና ማኅበራዊ ፍትህ የሰፈነባት ፤ የዜጎች ሕይወት፣ ደህንነትና ጥቅም የተከበረባት እና የሕዝቧ አንድነትና ትስስር የጠነከረባት ሃገር ሆና ማየትን ብቸኛ ራዕይ አድርጎ በመንቀሳቀስ ላይ የሚገኝ ድርጅት ነው። ይህንን ራዕይ እውን ለማድረግ ደግሞ እስከ ዛሬ በጠመንጃ ኃይልና በጉልበተኖች ጡንቻ ከአንዱ ወደሌላው የሚፈራረቀው የመንግሥት ና የፖለቲካ ሥልጣን በሰላማዊና ዲሞክራሲያዊ ሂደት የሚያዝበትን ፤ የሃገሪቱ ዜጎች ምርጫ በተግባር የሚገለፅበት፤ ማኅበራዊና የፖለቲካ ችግሮች በዲሞክራሲያዊ መንገድ የሚፈቱበት እና ዲሞክራሲያዊ ባህል የሚበለፅግበት ብሄራዊ የፖለቲካዊ ሥርዓት መገንባት አማራጭ የሌለው ነው ብሎ ያምናል።
ይህ ደግሞ ያለምክንያት አይደለም። ወያኔ የዓለም አቀፍ ድጋፍ ለማግኘት ሲል ለዲሞክራሲያዊ ምርጫ በሩን ከፈት አድርጎ በነበረበት ምርጫ 97 ወቅት ከተገኘው ልምድና ከተመዘገበው ውጤት ሕዝባችን በአምባገነኖችና በከፋፋዮች ለመገዛት አለመፈለጉን በግልጽ አስመስክሮአል።
ንቅናቄያችን ግንቦት 7 ሕዝባችን በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ በነቂስ ወጥቶ መሪዎቹን የመረጠበትንና ድሉን የተነጠቀመበትን ታሪካዊ የግንቦት 7 1997ን ቀን ምን ጊዜም አይረሳም። መጠሪያ ስሙንም በዚያ ታሪካዊ ቀን የሰየመው ሕዝብ የተነጠቀውን ድል በማስመለስ ፍትህ የሰፈነባት፤ የበለጸገችና የተከበረች አገር ባለቤት እንሆን ዘንድ ነው። ሁላችንም አትራፊ እንጂ ተጎጂ ለማንሆንበት ለዚህ ቅን አለማና ራዕይ ደንቃራ ሆኖ የተገኘው ወያኔና ለግል ጥቅማቸው ሲሉ ከወያኔ ጋር የተጣበቁ አንዳንድ ባዕዳን አገሮች ናቸው።
ወያኔ የግንቦት 7 መንገድ የሚለው ለዚህ ክቡር ዓላማ ሲባል እንቅፋት የሆነውን ሥርዓቱን በሁለ- ገብ ትግል አስገድዶ ለሰላማዊ የሥልጣን ሽግግር አካል ማድረግ ካልተቻለ ደግሞ በተባበረ ትግል አስወግዶ በምትኩ በሕዝብ ለሕዝብ ከሕዝብ የሚመጣ ሰላማዊ የመንግሥት ሥርዓት መመሥረትን ነው። ይህንን የተቀደስ አላማ ለማክሸፍና የተጀመረውን ትግል ለመጨፍለቅ ሲባልም ወደ ሥልጣን ለመምጣት በጦርነት ማግዶ ካስጨረሳቸው የደሃ ልጆች በእጥፍ የሚበልጡትን መልምሎ በጸረ ሽምቅ ውጊያ ከማሰልጠን ጎን ለጎን ለግንባታ ቢውል ስንት ፋይዳ ሊያስገኝ ይችል የነበረ በርካታ ገንዘብ በማፍሰስ ተቃዋሚ ድርጅቶችን ድምጽ ለማፈንና ለመሰለል እየተንቀሳቀሰ ይገኛል።
ለአገራችን ሉአላዊነት ጠቀሜታው እስከዛሬ ምንም ባልታወቀ ጦርነት ወደ መቶ ሺ የሚጠጉትን ያስጨፈጨፈ፤ የተልዕኮ ጦርነት ለማካሄድ በመንግሥት አልባዋ ጎረቤት ሱማሌ እስከዛሬ ቁጥራቸው ያልተገለጸ ወገን ያስፈጀ ፤ ለሥራ ፍለጋ ውትድርና የገቡትን ወጣቶች ለይቶ በሰላም አስከባሪ ስም በድንበር ዘለል ጦርነቶች እየማገደ ገንዘብ የሚቀበል፤ ስለአገርና ስለወገን ምን ሊገደው ይችላል?
ትናንት ትግል ላይ በነበሩበት ወቅት የቀደምቶቹ መንግስታት ልጆቻቸውን ለትምህረት ወደ ፈረንጅ አገር እየላኩ የደሃውን ልጅ በጦርነት ይማግዳሉ በማለት በጅምላ ሲከስ የኖረ ዛሬ በተራቸው ልጆቻቸውን ብቻ ሳይሆን ዘርማንዘሮቻቸውን ታይቶ በማይታወቅ ብዛት ወደ ፈረንጅ አገር ለትምህርት እየላኩ ለነጻነታችንና ለክብራችን የምንታገለውን እርስ በርስ ለማጨራረስ ሲዶልቱ ዝም ብሎ መመልከት ከየትኛውም ቅን ዜጋ የሚጠበቅ አይሆንም።
ስለሆነም የበላይ አዛዦቻቸው በሚሰርቁት የሕዝብ ገንዘብ ፎቅ ላይ ፎቅ እየገነቡ ሃብት በሚያካብቱት አገር ሠራዊቱን እረፍት ለመንሳት ሆን ተብለው በሚቀሰቂሱት ግጭቶች ከአንዱ ማዕዘን ወደ ሌላው ማዕዘን ያለ ዕረፍት እየተንከራተተ ያለው የመከላኪያ ሠራዊት ፤ የፖሊስና የደህንነት ኃይል ለአገዛዙ አልታዘዝም በማለት ተገዶ ሥልጣን ለሕዝብ እንዲያስረክብ የማድረግ ወገናዊ ሃላፊነቱን እንዲወጣ ግንቦት 7 የፍትህ የነትጻነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ጥሪውን ያቀርባል።
የግንቦት 7 መንገድ የኢትዮጵያ ሕዝብ ለዘመናት የተጠማውን ፍትህ እኩልነትና ነጻነት በአገራችን ለማስፈን አሁን ሥልጣን ላይ ያለው የጎጠኞችና የዘራፊዎች ስብስብ በማስገደድ ወይም በማስወገድ ሰላማዊ ህጋዊና ዲሞክራሲያዊ የሥልጣን ሽግግር እንዲኖር ማድረግ ነው። ይህንን ደግሞ የሚፈሩት በሥልጣን ቱርፋትና በሃብት ዘረፋ የሰከሩ ብቻ ናቸው።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ

Wednesday, January 29, 2014

30C3: To Protect And Infect - The militarization of the Internet

Source http://youtu.be/XZYo9TPyNko

“በዝዋይ የታሰሩት ባለቤቴ እዛው እስር ቤት መሞታቸውን ሕዝብ ይወቅልኝ” – ወ/ሮ ፈሪሃ አብድርሃማን

በዳዊት ሰለሞን

(ፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ እንደዘገበው) አቶ አህመድ ነጃሽ ሐሰን በ2002 ዓ.ም በተደረገ አገር አቀፍ ምርጫ በድሬዳዋ ክልል የኦሮሞ ኮንግረስ/ መድረክን በመወከል ተወዳድረው ነበር፡፡የፖለቲካ ተሳትፏቸውን እንዲያቋርጡ በተለያዩ መንገዶች ሲነገራቸው ቢቆዩም በሰላማዊ መንገድ ተቃውሞ ማሰማትና መደራጀት ህገ መንግስታዊ መብት መሆኑን በመጥቀስ ሲከራከሩ መቆየታቸውን ባለቤታቸው ወ/ሮ ፈሪሃ አብድርሃማን የሱፍ ለፍኖተ ነጻነት አስታውሰዋል፡፡
በ2003 የመንግስት የጸጥታ ሰዎች አቶ አህመድን በኦነግ አባልነት ተጠርጥረሃል በማለት ያስሯቸዋል፡፡የ57 አመቱ አህመድ ከታሰሩ በኋላ ለአራት ወራት ያህል በህይወት ይኖሩ ወይም ይሙቱ ለቤተሰብ ሳይታወቅ ከቆዩ በኋላ ፍርድ ቤት ቀርበው በኦነግ አባልነት ተከሰው ይፈረድባቸዋል፡፡ፍርዳቸውን ተከትሎም ለምርመራ ከቆዩበት ማዕከላዊ ወደ ዝዋይ ወህኒ ቤት እንዲዘዋወሩ ይደረጋሉ፡፡
ከአቶ አህመድ ነጃሽ ያገኟትን አንድ ልጅ ለብቻቸው የማሰደግ ዱብ ዕዳ የወደቀባቸው ወይዘሮ ፈሪሃ ገቢያቸው በመቋረጡ ስራ ፍለጋ ወደ አረብ አገር ያቀናሉ፡፡በአረብ አገር ያለሙትን ማግኘት ባለመቻላቸው ወደ አገር ቤት ይመለሳሉ፡፡ካልተሳካው ስራ ፍለጋ መልስ ወይዘሮዋ ባለቤታቸውን ለመጠየቅ ወደ ዝዋይ ሲያመሩ የማረሚያ ቤቱ ሃላፊዎች ባለቤታቸው ወደ ቃሊቲ መዘዋወራቸውን ይነግሯቸዋል፡፡
ከዝዋይ በቀጥታ ወደ ቃሊቲ በማምራትም ይጠይቃሉ፣ቃሊቲዎች እንዲህ አይነት እስረኛ ወደ እነርሱ አለመምጣቱን በመጥቀስ ያሰናብቷቸዋል፡፡ከብዙ የዝዋይና ቃሊቲ ምልልስ በኋላ አቶ አህመድ በጠና ታመው ምኒሊክ ሆስፒታል እንደገቡ ይነገራቸዋል፡፡ምኒልክ ሆስፒታል ለጥየቃ ባመሩበት ወቅት መጥፎውን ዜና ይሰማሉ፡፡አቶ አህመዲን ይህችን አለም ከተሰናበቱ ረዘም ያሉ ወራቶች ተቆጥረዋል የሚል፡፡
አስከሬን የለ፣ የት እንደተቀበሩና የሞታቸው መንስኤ ምን እንደነበር የሚያስረዳ የለ፣ ሁሉ ነገር ድፍንፍን ያለባቸው ወይዘሮዋ ለፍኖተ ነጻነት በሰጡት ቃል‹‹የመንግስት ሰዎች ምንም አይነት ቀና ምላሽ እንደማይሰጡኝ አውቃለሁ ነገር ግን በታሰሩበት ወቅት ፍጹም ጤነኛ የነበሩት ባለቤቴ መሞታቸውን ህዝቡ ይወቅልኝ ብለዋል፡ ፡የኦሮሞ ኮንግረስ በኋላም የኦፌኮ ፕሬዘዳንት የሆኑት ፕሮፌሰር መራራ ጉዲና የአቶ አህመድን ሞት ከባለቤታቸው እንደሰሙ በመጥቀስ ነገር ግን ምንም ማድረግ አለመቻሉን አውስተዋል፡፡
ምንጭ ዘ-ሐበሻ

Monday, January 27, 2014

“የትግራይ ሕዝብ በአንድ ቤተሰባዊ ቡድን ለሚመራ ድርጅት በንብረትነት ለማገልገል የተፈጠረ ሕዝብ አይደለም” – በዲያስፖራ የአረና ደጋፊዎች መግለጫ

(ዘ-ሐበሻ) ሰሞኑን በትግራይ የህወሓት መሪዎችና ካድሬዎቻቸው ከየመንደሩ የተውጣጡ ነብሰ ገዳይ፣ ስብሰባ በታኝና አፋኝ የዱዬ ቡድኖችን በተለያየ መልኩ በማደራጀት በአረና ትግራይ አባላትና አመራር ላይ የከፈቱትን አዲስ የመንጥርና የድብደባ ዘመቻን አስመልክቶ በዲያስፖራ የአረና ትግራይ ድጋፍ አስተባባሪ ኮሚቴ ለዘ-ሐበሻ በላከው መግለጫ ድርጊቱን አወገዘ።
“ትግራይ እንደነ አሉላ አባ ነጋና ዮሐንስ የመሳሰሉ የብዙ ጀግኖች ዓፅም የተቀበረባትና አኩሪ ታሪክ ያላት ምድር ብትሆንም ዛሬ ህዝብዋ በአንድ ቤተሰባዊ ቡድን ለሚመራ ፓለቲካዊ ድርጅት በሞኖፓልና በንብረትነት ለማገልገል የተፈጠረ ህዝብ አድርገው በመቁጠር እንደ ህፃን ልጅ አፍህን ያዝ እየተባለ በካድሬ ዱላ እየተኰረኰመ ሲኖር ማየች እጅግ የሚያሳዝን የታሪክ ጠባሳ ነው።” የሚለው ይኸው መግለጫ “ስለሆነም ህወሓት በህዝቡም ሆነ የተለየ አመለካከት ይዘው በሚንቀሳቀሱ ወገኖቻችን ላይ የሚያካሂደው የስነ ልቦናና የአክል ጥቃት የዲሞክራሲ መርህ የሚፃረር ኢ ሰብኣዊ ተግባር ብቻ ሳይሆን የዜጎች ሕገ መንግስታዊ መብት የሚጥስ ሕገ ወጥ ተግባር ስለሆነ ድርጊቱን እናወግዛን።” ብሏል።
“ህወሓት/ኢሕአዴግ በትረ ስልጣኑን ከተጎናፀፈና ካደላደለ ወዲህ ከሱ የተለየ አመለካከትና ሃሳብ ያላቸው ወገኖች ሁሉ የተለያዩ ቀለማ ቀለሞችን በመቅባት፣ የፈጠራ ስም በመለጠፍና ሰበብ አስባብ በመፈለግ በቀጥታም ሆነ በረቀቀ መንገድ የመመንጠር፣ የማፅዳት፣ የመሰወር፣ የማሰር፣ የመግደልና እርስ በርስ የማናቆር ስራ ዋነኛ የስርዓቱን ባህርይ መገለጫ ሆኖ መቆየቱ እሙን ነው።” ያለው የአረና ደጋፊዎች መግለጫ “የእርምጃው ዋናው ምክንያትም እውነት ተቃዋሚዎቹ የሀገርና የህዝብ ጠላቶች ስለሆኑ አይደለም። ነገር ግን ጥያቄያቸው “ስለ ሀገራችንና ህዝባችን ጉዳይ እኛም ያገባናል!! አባቶቻችን ደም ከፍለው ያቆዩልንን ሀገር የመጠበቅ የኛም ግዴታ ነው!! ዘላቂ ልማትና ዕድገት የሚመጣው እውነተኛ ዲሞክራሲ፣ የሕግ ልዕልና፣ ፍትሕ፣ ነፃነት፣ ሰላምና አንድነት ሲረጋገጥ እንጂ በጡንቻ አይደለም!! ሕገ መንግስቱ የሰጠንን የመናገር፣ የመፃፍ፣ የመደራጀት፣ የመንቀሳቀስ፣ የእምነት፣ የመምረጥና የመመረጥ ነፃነታችንን ይከበር!!” ብለው ሰላማዊና ሕጋዊ መንገድን ተከትለው በቆራጥነት ስለተንቀሳቀሱና ስለጠየቁ ብቻ መሆኑን ማንም ቅን ህሊና ያለው ኢትዮጵያዊ ሊገነዘበው የሚችል ጉዳይ ነው።” ብሏል።
በዲያስፖራ የአረና ትግራይ ድጋፍ አስተባባሪ ያወጣው መግለጫ ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ይቀጥላል፦
ሰሞኑን የመድረክ አባል ከሆኑት የፓለቲካ ድርጅቶች አንዱ “በአረና ትግራይ ለሉዓላዊነትና ለዲሞክራሲ” አባላትና ከፍተኛ አመራር ላይ እየደረሰ ያለው ግፍና አፈና ማየቱ በቂ ይመስለናል። የአረና ትግራይ ፈጣን ዕድገትና በህዝቡ ዘንድ ተቀባይነት እያገኘ መሄድ ያስደነጋጣቸው የህወሓት ካድሬዎችና መሪዎቻቸው እንቅስቃሴውን ለመግታት የማይፈንቅሉት ድንጋይና የማይሸርቡት ተንኰል እንደሌለ በተደጋጋሚ አይተናል። ዛሬም እንደለመዱት አዲስ የማጥቃት ስልት በመቀየስ ነብሰ ገዳይ፣ በታኝና አፋኝ የዱሩየዎች ቡድን በተለያየ መልኩ በሕቡእና በግልፅ በማደረጃት በአረና አባላትና መሪዎች ላይ አዲስ የመንጥር ዘመቻና ጥቃት ጀምሯል።
የማጥቃት ዘመቻው ቀደም ብሎ በሽሬ እንዳስላሴ የተጀመረ ሲሆን ሰሞኑን ደግሞ በባሰ መልኩ በአዲ ግራት ከተማና በሌሎች አካባቢዎችም በስፋት ቀጥሏል። በዚሁ ተከታታይ ዘመቻቸው ያነጣጠሩት አረና ትግራይ የጠራውን ስብሰባ እየተከታተሉ መበተን፣ ህዝቡን ወደ ስብሰባው እንዳይሄድ በተለያዩ ዘዴዎች ማስፈራራትና ማሰናከል፣ በታኝ የዱሩየዎች በዱን በማደራጀት ለመበጥበጥና ለማወክ ያለ የሌለ ሀይላቸውን በማንቀሳቀስ ስብሰባዎችን እንዲቋረጡ አድርጓል።
(ከዚህ ቀደም የአረናን ሕዝባዊ ስብሰባ እንዳይሳተፉ የተከለከሉ የሽሬ ነዋሪዎች – ፎቶ ከአብርሃ ደስታ) – ፎቶ ፋይል

ጉዳዩን በቅርብ ተከታትለን እንዳረጋገጥነው የሚያሳዝነውና የሚያስገርመው ስብሰባውን መበተኑና መቋረጡ ብቻ ሳይሆን ህዝቡን ለመቀስቀስ በአካባቢው የተሰማሩ በሶስት ከፍተኛ የአረና ትግራይ መሪዎች በአፋኝና በታኝ ቡድን እንዲደበደቡ ማደረጋቸውና ማሰራቸው ነው። የዚሁ ጥቃት ሰለባ ከሆኑት ሰዎች ውስጥ አቶ አስገደ ገብረስላሴ የቀድሞ የህወሓት መስራችና አስልጣኝ የነበሩ፣ አቶ አብርሃ ደስታ የመቀሌ ዩኒቨርሲቲ የፓለቲካ ሳይንስ መምህርና ተመራማሪ፣ አቶ ዓንዶም ገብረስላሴ የዓረና ማእከላይ ኮሚቴ አባልና የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ ይገኙባቸዋል።
በአንጋፋ ወንድሞቻችን ላይ የደረሰባቸው ኢ ሰብኣዊ ጥቃት እጅጉን ያስቆጣንና ያስገረመን ቢሆንም በኛ እምነት ይህ ሁሉ ግፍና መሰሪ ተግባር በድምር ሲታይ የሚከተሉትን ሓቆችንና ክስቶችን የሚያመላክቱ የስርዓቱን ባህርይ ገላጭ ናቸው ብለን እናምናለን።
1. ህወሓት ታሪክ፣ ባህልና ሕግ የማይገዛው፣ መሰረታዊ እውነታዎችንና ዲሞክራሲያዊ መርሆዎችን የሚፃረርና የህዝቡን ሉዓላዊ ህልውና የሚያፈርስ የጥፋት መንገድ እየተከተለ በመሄድ ላይ እንደሆነ የሚያሳይ የቀቢፀ ተስፋ እርምጃ መሆኑን ራሱ በራሱ ጋሃድ እየሆነ መምጣቱ የሚያመላክት ነው።
2. ይህ ዓይነቱ ጭካኔ የተሞላበት ድርጊት የሚያሳየን ህወሓት ራሱን ከመንግስትነት ወደ ተራ ዘራፊነትና ማፊያነት በመቀየር የዜጎችን ድህንነት ለመጠበቅ የማይችል ሕገ አልባና የሻገተ ስርዓት መሆኑን ራሱን በራሱ እያስመሰከረ ያለ ድርጅት መሆኑን እንገነዘባለን። አንድ መንግስት በራሱ ህዝብና በገዛ ወገኑ ላይ ነብሰ ገዳይና አፋኝ ቡድንን በማደራጀት ዜጎቹን በአደባባይ ማስደብደብ ማለት የባዕድ ወራሪ እንኳን ያላደረገው ከዚህ የባሰ ጭካኔ፣ ውድቀትና ዝቅጠት አለ ብለን አናምንም።
3. የህወሓት ፀረ ህዝብ ተግባር ለይስሙላ ስለዲሞክራሲና ስለየብዙሃን ፓርቲ ስርዓት ይናገር እንጂ በተግባር በህዝብ ፊት ቀርቦ ለመከራከርና ለመዳኘት አቅምና ሞራል የሌለው፣ በህዝቡ ዘንድ ምን ያህል የተተፋና ጊዜ የጣለው ድርጅት መሆኑን ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ነው። ህወሓት የትግራይ ህዝብን ነፃነትና ደህንነት ጠባቂ ለመሆን ቀርቶ የነገ የሀገር ተረካቢና ተስፋ የሆነውን ወጣት በነፃነት አየር ተኰትኵቶና የወገንና የሀገሩን ፍቅር ተላብሶ እንዳያድግ ወኔን የሚያኰላሽ ትውልድ ገዳይ ድርጅት መሆኑን ከተግባሩ በላይ ሌላ ምስክር የሚያሻ አይደለም።
4. ህወሓት የትግራይ መንግስት ነኝ ይበል እንጂ ራሱ የፃፈውን ሕገ መንግስት እንኳ ጠንቅቆ የማያውቅ፣ በተግባር የሕገ መንግስቱን መሰረታዊ መርሆዎችን የሚፃረር ስራ የሚሰራ አፍራሽ ድርጅት መሆኑን ራሱን በራሱ እያስመሰከረ ይገኛል። የትግራይ ህዝብ እየተዳደረ ያለው ራሱ ባፀደቀው ሕገ መንግስት መሰረት ሳይሆን ገና በበረሃ የነበረው የደደቢት የካድሬ ሕግ መሆኑን ካለው ተጨባጭ ሁኔታና ከተግባራቸው መረዳት ይቻላል።
5. ህወሓት የትግራይ ህዝብ ነፃ አውጪ ነኝ በማለት የትግራይ ህዝብ ነብዪ መስሎ ለመቅረብ ይሞክር እንጂ በተግባር ግን የታገለለትን አላማ የሚፃረር ስራ የሚሰራና የህዝቡን ተስፋ እያጨለመ የሚገኝ ድርጅት መሆኑን ራሱ በራሱ እያስመሰከረ ይገኛል።
6. የጥቃቱ መንሲኤ ካድሬዎቹ እንደሚሉት የአረና ትግራይ አባላትና ደጋፊዎቻቸው የህዝብ ጠላት ስለሆኑ፣ ሕግ ስለጣሱ፣ የትምክሕተኞች አመለካከት ስለሚያራምዱ ወይም የደርግ ስርዓትን ዳግም ለመመለስ የሚታገሉ ስለሆኑ አይደለም። አረና ትግራይ ሕገ መንግስቱ የሚጠይቃቸው መመዘኛዎችን አሟልቶ በሕጋዊ መንገድ ተመዝግቦ በሰላማዊ መንገድ የሚታገል ድርጅት መሆኑን ይታወቃል። ይሁን እንጂ “አያ ጅቦ ሳታማኸኝ ብላኝ” እንደሚባለው ሁሉ ከጥቃቱ በስተጀርባ ያለው ሚስጢር ግን ባንድ በኩል ገዢው ፓርቲ በሀገር ደረጃ በተለይም በትግራይ ምድር እነሱ የማይቆጣጠሩት ትርጉም ያለው ነፃ የፓለቲካ ድርጅት እንዲፈጠር ፍፁም አይፈልጉም። በሌላ በኩል ደግሞ በትግራይ ህዝብ ላይ ያላቸው ንቀትና ዝቅተኛ ግምት የሚያሳይ ነው። ሕብረተሰቡ በፓለቲካ ድርጅትና በህዝብ መካከል ያለው ግንኙነትና ነፃነት፣ የዲሞክረሲ “ሀ ሁ”፣ ሕገ መንግስታዊ መብቱንና ታሪኩን በትንሹ ያውቃል ብለው ቢገምቱት ኖሮ እንዲህ ዓይነቱ ዓይን ያወጣ አረሜናዊ ተግባር አይፈፁምም ነበር።
የተከበራችሁ በሀገር ውስጥና በውጭ የምትኖሩ ውድ ኢትዮጵያውያን!!
እኛ በዲያስፓራ የምንኖረው የአረና ትግራይ የድጋፍ አስተባባሪ ኮሚቴና መላ የትግራይ ተወላጆች በሀገራችን ኢትዮጵያ ውስጥ በየማዕዝናቱ በተለይም በበንሻንጉል፣ በጋምቤላ፣ በደቡብና በሌሎች ቦታዎች በወገኖቻችን ላይ የሚፈፀሙ አፈናዎችና እንግልት በቅርብ ስንከታተልና በተለያየ መልኩ ድምፃችንን ስናሰማ ቆይተናል። በቅርቡ በሳውዲ ዓረቢያ በሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ወንድሞቻችንና እህቶቻችን ላይ የደረሰው ልብ ሰባሪ የሆነ አሳዛኝና አሳፋሪ ዜና ስንሰማም በቁጣ ስሜት በመነሳሳት በያለንበት ከሌሎች ወገኖቻችን ጎን በአደባባይ ቆመን ጭኾናል። አውግዘናልም። ዛሬም በተመሳሳይ መልኩ እንደተለመደው በትግራይ በወገኖቻችን ላይ እየተካሄደ ያለው ጥቃትም ከዚሁ ተለይቶ የማይታይ ስለሆነ አሁንም የተሰማንን ቁጣና ብሶት ይህንን የጋራ መግለጫ በይፋ እንድናወጣ ተገደናል። ያልታደለች ሀገር ሁሉጊዜ መርዶ ነውና!
ትግራይ እንደነ አሉላ አባ ነጋና ዮሐንስ የመሳሰሉ የብዙ ጀግኖች ዓፅም የተቀበረባትና አኩሪ ታሪክ ያላት ምድር ብትሆንም ዛሬ ህዝብዋ በአንድ ቤተሰባዊ ቡድን ለሚመራ ፓለቲካዊ ድርጅት በሞኖፓልና በንብረትነት ለማገልገል የተፈጠረ ህዝብ አድርገው በመቁጠር እንደ ህፃን ልጅ አፍህን ያዝ እየተባለ በካድሬ ዱላ እየተኰረኰመ ሲኖር ማየች እጅግ የሚያሳዝን የታሪክ ጠባሳ ነው። ስለሆነም ህወሓት በህዝቡም ሆነ የተለየ አመለካከት ይዘው በሚንቀሳቀሱ ወገኖቻችን ላይ የሚያካሂደው የስነ ልቦናና የአክል ጥቃት የዲሞክራሲ መርህ የሚፃረር ኢ ሰብኣዊ ተግባር ብቻ ሳይሆን የዜጎች ሕገ መንግስታዊ መብት የሚጥስ ሕገ ወጥ ተግባር ስለሆነ ድርጊቱን እናወግዛን። እንዲሁም በግፍ የታሰሩ ወገኖቻችን ከእስር እንዲፈቱና በነሱ ላይ ድብደባ ያደረሱ የማፊያና የነብሰ ገዳይ ቡድን አባላትም በአስቸኳ ለፍርድ እንዲቀርቡ አበክረን እንጠይቃለን።
በስልጣን ላይ ያለው ገዢው ፓርቲ ዜጎቻችንን ለያይተህ ግዛ በሚል ፈሊጥ በየተራ እንደ ፈለገ እያጠቃን እንዲኖር ምቹ ሁኔታ የፈጠርንለት እኛው ራሳችን በተለያየ ጎራ የየራሳችን ጎጆ አበጅተን በረባም ባልረባም በመነጣጠላችን መሆኑን እሙን ነው። ህዝብ ከተባበረ ምን ዓይነት ለውጥ ሊያመጣ እንደሚችል በሌሎች አጋጣሚዎች አይተናል። ስለዚህ በሀገር ቤትም በውጭም የምንኖር ኢትዮጵያውያን ሁሉ ለሀገርና ለወገን ሲባል መለስተኛ ልዩነታችንን ወደ ጎን ትተን በዜጎቻችን ላይ እየደረሰ ያለው አስነዋሪ ጥቃት በጋራ ልንቆምላቸው ይገባል። በመሆኑም ዛሬ በትግራይ ወገኖቻችን ላይ እየደረሰ ያለው በደል ነገ በሌሎች ክልሎችም የሚደርስ ጉዳይ ስለሚሆን ድርጊቱን በጋራ እንድናወግዘው ወገናዊ ጥሪያችንን እናቀርባለን።
ጀግናው ኩሩና ታጋሽ የትግራይ ህዝብም በአካል ይቆጣጠሩት ይሆናል እንጂ የህወሓት ካድሬዎችና መሪዎቻቸው የሚሰሩትን አስቂኝና አሳዛኝ ድራማ ይስቷል ብለን አናምንም። ማን በሙሱና ተነክሮ ጨለማ ለብሶ የሀገርና የህዝብ ሀብት እየዘረፈና ወደ ዉጭ እያሸለከ እንዳለ ማን ደግሞ ለሀገሩና ለወገኑ በፅናት እየታገለ እንዳለ በውል ይገነዘባል። ትላንት ማን ከጎኑ እንደቆመ ማን ደግሞ ለሻዕቢያ ወረራ ለጅብ አሳልፎ እንደሰጠው ስለሚያስታውስ የጊዜ ጉዳይ እንጂ ልቡ ከማን ጋር እንዳለ ጠንቅቀን እናውቃለን። በአጠቃላይ የትግራይ ህዝብ ክብሩንና ማንነቱን በሻዕቢያ በመደፈሩ፣ ለም መሬቱንና አንጡራ ሀብቱን ለባዕድ አሳልፎ በመሰጠቱ፣ ራሱ የሰራውን ቤት፣ በደሙና በአጥንቱ ራሱ የገነባትን ሀገር ፈርሶ የባሕር በር የሌላት ጎራዳና ሽባ ሀገር ይዞ በመቅረቱ ደስተኛ ነው ብለን በፍፁም አናምንም።
ስለሆነም ዛሬም ለገዢው ፓርቲ ህወሓት/ኢሕአዴግ መሪዎችና ካድሬዎቻቸው ደግመን ደጋግመን ልናስገነዝባቸው የምንፈልገው ጉዳይ አንድና አንድ ብቻ ነው። በሀገራችን ፍትሕ የጠማው፣ በረሃብ አለንጋ የሚገረፍና በልቡ የሸፈተ ህዝብ እስካለ ድረስ እናንተ የምትፈፅሙትን ጊዜው ያለፈበትና አረሜናዊ የቀቢፀ ተስፋ እርምጃ ትግሉን የበለጠ እንዲግልና እንዲጎለብት ያደርገዋል እንጂ በፍፁም አይገታውም። እኛም የበለጠ እንድንጠነክርና ቀና ብለን በፅናት ከህዝባችን ጎን እንድንቆም ያደርገናል እንጂ አንገታችንን እንደማንደፋ ደግመን ልናረጋግጥላችሁ እንወዳለን።
ኢትዮጵያ ሀገራችን ለዘላለም ትኑር

Prof Mesfin on Ethio Sudan border dispute


Sunday, January 26, 2014

የወያኔ የውሸት ዘገባዎች ሲጋለጡ

“ኦክስፋም” በመልካም ሥራቸው ከታወቁ ትላልቅ ዓለም ዓቀፍ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች አንዱ ነው። በቅርቡ አንድ መቶ ሀያ አምስት አገሮችን ያካተተ ከምግብ አቅርቦትና አጠቃቀም ጋር የተያያዘ ጥናት ውጤት ይፋ አድርጓል። ጥናቱ አራት ዝርዝርና አንድ አጠቃላይ አመላካቾች አሉት።
1. አመላካች አንድ: የምግብ እጥረት
ይህ አመላካች “በየአገሮቹ ምን ያህል ለበላተኛው የሚበቃ ምግብ አለ?” የሚለውን ይለካል። በጥናቱ ውጤት መሠረት በምግብ እጥረት እጅግ የተጎዱ የመጨረሻዎቹ አስር አገሮች የሚከተሉት ናቸው: – ቡሩንዲ፣ የመን፣ ቻድ፣ ኢትዮጵያ፣ ማዳጋስካር፣ ናይጄሪያ፣ ላኦስ፣ ባንግላዴሽ፣ መካከለኛዉ አፍሪካ ሪፑብሊክ እና ህንድ። ኢትዮጵያ አገራችን ከመጨረሻ አራተኛ ናት።
2. አመላካች ሁለት: ለምግብ የመክፈል አቅም (Affordability)
ይህ አመላካች “የአገሩ ሕዝብ በአገሩ ዋጋ ምግብ ገዝቶ ለመብላት ምን ያህል አቅሙ ይፈቅድለታል?” የሚለውን የሚመልስ ነው። አሁንም ከመጨረሻ እንጀምር። አንጎላ፣ ዚምባቡዌ፣ ቻድ፣ ጉያና፣ ኢትዮጵያ፣ ናይጄሪያ፣ ኮንጎ፣ ኬንያ፣ ጋምቢያ እና ኢራን የየአገሩ ሕዝብ ምግብ መሸመት የሚቸገሩባቸው አገሮች ናቸው። አገራችን ኢትዮጵያ ከመጨረሻ አምስተኛ ናት።
3. አመላካች ሶስት: የምግብ ጥራት
ይህ የምግብ ይዘትንና የአያያዝ ንጽህናን የሚመለከት ሲሆን ኢትዮጵያ፣ ማዳጋስካር፣ሞዛምቢክ፣ ቻድ፣ ቶጎ፣ ዛምቢያ፣ ማሊ፣ ናይጄሪያ፣ ባንግላዴሽ፣ ሌሶቶ ከመጨረሻው እስከ አስረኛ ደረጃ ይዘዋል። ኢትዮጵያ በምግብ ጥራት የመጨረሻዋ አገር ናት።
4. አመላካች አራት፡ የሰውነት ውፍረት እና የስኳር በሽታ
ይህ አመላካች ከልክ ያለፈ ውፍረት ዓለም ዓቀፍ የጤና ችግር እየሆነ በመምጣቱ የገባ አመልካች ነው። ኢትዮጵያ ከፍተኛ ጥሩ ውጤት ያመጣችሁ በዚህ አመላካች ብቻ ነው። ኢትዮጵያ አብዛኛው ሕዝቧ ቀጫጫ ነው፤ የስኳር በሽታም እንደሌላው አገር የተስፋፋባት አገር አይደለችም።
5. አማካይ ውጤት
የእነዚህ አራት አመላካቾች ድምር ውጤት አጠቃላይ ውጤትን ይሰጣል። በአጠቃላይ ውጤት: ቻድ፣ ኢትዮጵያ፣ አንጎላ፣ ማዳካስካር፣ የመን፣ ቡሩንዲ ናይጄሪያ፣ ሞዛምቢክ፣ ዚምባቡዌ፣ ሴራሊዮን ከመጨረሻ እስከ አስረኛ ወጥተዋል። ኢትዮጵያ ከመጨረሻ ሁለተኛ ነች።
ይህ ምንን ያመለክታል?
ወያኔ ባለፉት አስር ዓመታት በተከታታይ ከ11% በላይ ኢኮኖሚውን አሳድጌዋለሁ ሲለን ነበር። እድገቱ ያተኮረው ገጠር፤ ምንጩም ግብርና ነው ብሎን ነበር። ሐቁ ግን ከላይ የተመለከተው ነው።
እርግጥ ነው የወያኔ ሹማምንት በከተሞች ሕንፃዎችን ይገነባሉ፤ በገጠሮች በመቶዎች ሄክታር የሚለካ ለም መሬት ይዘው ፈጣን ገንዘብ በሚያስገኙ የአበባ፣ የጫትና የቃጫ ምርት ላይ ተሰማርተዋል። ከራሳቸውም አልፈው ሀብታም የውጭ አገራት ሸሪኮቻቸውን በአገራችን ለም መሬት ይበልጥ ያበለፅጓቸዋል። የእነሱ የግላቸው፣ የቤተሰቦቻቸው፣ የዘመዶቻቸው እና የሸሪኮቻቸው ኢኮኖሚ እየተመነደገ መሆኑን እናውቃለን። ይህን በገዛ ዓይኖቻችን የምናየው ሀቅ ነው።
ሆኖም ግን የእነሱ ኢኮኖሚ ማደግ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ማደግ አለመሆኑ እናውቃለን። አገራችን ከጓረቤት አገሮች ጋር ስትነፃፀር ወደ ኋላ እየቀረች መሆኑ ያንገበግበናል። በቅርቡ አክስፋም በጥናት ያረጋገጠዉ የኢትዮጵያ ገበሬዎች በየቤታቸው ከወዳጆቻቸው ጋር በምስጢር የሚያወሩትን እውነት ነው።
ከሳምንት በፊት ደግሞ “ኢኮኖሚክ ኢንተለጀንስ ዩኒት” የተሰኘው ታዋቂ የምርምር ተቋም አንድ የጥናት ውጤት ይፋ አድርጎ ነበር። በዚህ የጥናት ውጤት መሠረት በዓለም በከፍተኛ ፍጥነት እያደጉ ያሉ አስር አገሮች በቅደም ተከተል ሞንጎሊያ፣ ሴራሊዮን፣ ቱርክሜንስታን፣ ቡታን፣ ሊቢያ፣ ኢራቅ፣ ላኦስ፣ ቲሞር-ሊስቲ፣ ኤርትራ እና ዛምቢያ ናቸው። በዝርዝሩ ውስጥ ኢትዮጵያ አገራችን የለችበትም።
በዓለም አቀፍ መድረኮችም የወያኔ መረጃዎች ውሸትነት እየተጋለጡ መሆናቸው በጎ ምልክት ነው። የሚያሳዝነው ግን ይህንን ሀቅ የሚያዉቁ ምዕራባዉያን ለጋሽ አገሮች አሁንም ወያኔን እየረዱና እየደገፉ ሥቃያችን የሚያራዝሙብን መሆኑ ነው።
ለዚህም ነው ግንቦት 7፡ የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ዘላቂ መፍትሔ ሊመጣ የሚችለው በአገራችን መሠረዊ የሆነ የአስተዳደር ለውጥ ሲኖር ነው ብሎ የሚያምነው። የወያኔ አገዛዝ በዲሞክራሲያዊ አስተዳደር እስካልተተካ ድረስ የኢትዮጵያ አብዛኛው ሕዝብ መደህየቱ፤ ጥቂት ሀብታሞች ደግሞ በብዙሀኑ ድህነት መበልፀጋቸው አይቀርም። የወያኔ ውሸቶች ለኢትዮጵያ ድሀ ምግብና መጠለያ አይሆኑለትም። ለኢትዮጵያ ዘላቂ ጥቅም ማምጣት የምንችለው ወያኔን አስወግደን በምትኩ ለሕዝብ ሁለተናዊ እድገት የሚጨነቅ መንግሥት መምረጥ ስንችል ብቻ ነው።
ስለሆነም ግንቦት 7፡ የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ በውሸት እድገት እያደናቆረን፤ በተግባር ግን እያደኸየን ያለውን ዘራፊውን ወያኔን አስወግደን በሕዝብ ነፃ ምርጫ የተመረጠ መንግሥት እንዲኖረን ትግላችን እናጠንክር ይላል።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!

Saturday, January 25, 2014

አብርሃ ደስታ አዲግራት ላይ በሕወሓት ካድሬዎች ተደበደበ

(ዘ-ሐበሻ) የአረና ለትግራይ ፓርቲ በትግራይ ክልል የተለያዩ ከተሞች ሕዝብን የማነቃቃስ ስብሰባዎችን በመጥራትና በማወያየት ላይ የሚገኝ ሲሆን በሚያደረጋቸው ሰላማዊ እንስቃሴዎች በሕወሓት ካድሬዎች ፈተና እየገጠመው ይገኛል። ዛሬ ከወደ አዲግራት የደረሰን መረጃ እንደሚያመለክተው በፌስቡክ፣ በትዊትር እና በተለያዩ ድረገጾች ላይ “አብርሃ ደስታ ከመቀሌ” እያለ የሚዘግበው መምህር ድብደባ ተፈጽሞበታል።
አረና ፓርቲ ነገ እሁድ ጁላይ 26 ቀን 2014 በአዲግራት ከተማ የጠራውን ሕዝባዊ ስብሰባ ለሕዝብ ለማስተዋወቅ በከተማዋ በሚንቀሳቀሱበት ወቅት በሕወሓት ካድሬዎች በተደራጁ በተባሉ ወጣቶች “ሕዝብ መቀስቅሳችሁን አቁሙ” በሚል ጥቃት የተፈጸመባቸው አሰገደ ገብረ ሥላሴ፣ አምዶም ገብረስላሴና አብርሃ ደስታ ላይ ሲሆን በአብርሃ የደረሰው ድብደባ ከፍተኛ ጉዳት ባያደርስም አቶ አሰገደ እና አንዶም ወደ ሃኪም ቤት ተወስደው ህክምና እንደተደረገላቸው ለዘ-ሐበሻ የደረሱት መረጃዎች አመልክተዋል።
በተያያዘ ዜና በተጨማሪ የአዲግራቱን ስብሰባ ለማስተጓጎል ሕወሓት ወታደሮችን በማሰማራት የአረና ሰዎችን በማሳሰር ላይ እንደሚገኝ የደረሰን ዜና አመልክቶ ለማሰር የቀረበው ምክንያትም “ሕዝብ በስብሰባ እንዲሳተፍ ቀስቅሳችኋል” በሚል ነው።
ከዚህ ቀደም የአረና አባላት በተንቤይን ሕዝባዊ ስብሰባ ጠርተው የነበረ ስሂን እዚያም እስር እና እንግልት እንደደረሰባቸው ዘ-ሐበሻ በወቅቱ መዘገቧ አይዘነጋም።
(ከዚህ ቀደም የአረናን ሕዝባዊ ስብሰባ እንዳይሳተፉ የተከለከሉ የሽሬ ነዋሪዎች – ፎቶ ከአብርሃ ደስታ) – ፎቶ ፋይል

Thursday, January 23, 2014

ከቃሊቲና ቂሊንጦ እስር ቤቶች በላይ የሚያንጸባርቁ ከዋክብት – ዳዊት ከበደ ወየሳ (አትላንታ) [ጋዜጠኛ]

(ይህ ጽሁፍ የርዕዮት አለሙ የልደት በአል በአዲስ አበባ በተከበረበት ወቅት; ከውጭ አገር ንግግር እንዳደርግ በተጋበዝኩበት ወቅት… የስራ ባልደረቦቼን እስክንድር, ውብሸት እና ርዕዮትን በማሰብ የተዘጋጀ ነው)
ይህ ሳምንት የታላቁ ማርቲን ሉተር ኪንግ የልደት በአል በመላ አሜሪካ የሚከበርበት ነው:: በአሜሪካ ከክርስቶስ ልደት ቀጥሎ ስራ እና ትምህርት ቤት ተዘግቶ ልደቱ የሚከበርለት አንድ ሰው ቢኖር ማርቲን ሉተር ኪንግ ብቻ መሆኑን ልብ ይበሉ:: የማርቲን ሉተር ኪንግ የልደት በአል በሚከበርበት ወቅት በህይወት ዘመኑ ለጥቁር ህዝብ ነጻነት ያደረገው አስተዋፅኦ ይታወሳል:: በህይወት በነበረበት ወቅት ለሰው ልጅ እኩልነት ተሟግቷል; የነጻነት ቀንዲልን ለኩሷል:: ሆኖም እኩልነት እና ነጻነትን ሳያጣጥም በበርሚንግሃም እስር ቤት ተጥሎ ፍዳውን እንዲቆጥር ተፈርዶበት ነበር:: በመጨረሻም የሰውን ልጅ ክብር እና ነጻነት በማይደግፉ ሰዎች ህይወቱ ማለፉ ይታወቃል – መልካም ስራዎቹ ግን አላለፉም::

ዛሬም በአገራችን ስለፍትህ, ስለነጻነት የሰበኩና የደሰኮሩ; የጻፉና የመሰከሩ… ለሃቅ ቆመው፣ ግፍ የተሰራባቸው፣ ከአገር የተሰደዱና የወጡ፤ በግፍ ሰንሰለት ለጨለማ እስር የተዳረጉ ወገኖቻችን ብዙ ናቸው:: እስክንድር፣ ውብሸት፣ ርእዮት፣ አንዷለም እና ሌሎች ኢትዮጵያውያን ራሳቸውን በሰብአዊነት መሰረት ላይ ስላነጹ እና ሃሳባቸውን በነጻነት ስለገለጹ መጨረሻቸው እስር እና እንግልት ሆኗል::
እንደ እውነቱ ከሆነ ሃሳብን በነጻነት መግለጽ… ብሎም የህዝብ ልሳን ሆኖ ለህዝብ የቤዛነት ዋጋ መክፈል የሚያስከብር እንጂ የሚያሳስር አልነበረም:: በመሆኑም ለነጻ ፕሬስ መክፈል የሚገባቸውን ዋጋ ከመጠን አሳልፈው የከፈሉት፤ ርዕዮት አለሙ፣ እስክንድር ነጋ እና ውብሸት ታዬ… ሶስቱም ከአገራቸው አልፈው በአለም አቀፍ ደረጃ እውቅና አግኝተዋል:: በአለም አቀፍ ደረጃም በልዩ ልዩ አለም አቀፍ የጋዜጠኞች ማህበራትና ተቅውውማት ለሽልማት ታጭተው አሸናፊ ሆነዋል::
የ’ነዚህ የስራ ባልደረቦቼ ብዕር… ህዝብን ሳይሆን የተወሰኑ ወገኖችን አሸብሮ ሊሆን ይችላል:: እነርዕዮት አለሙ በዚህ አይነት ሰበብ አስባብ በቃሊቲ እና በቂሊንጦ እስር ቤት ታግተው፤ ነጻነታቸውን አጥተውና ህክምና ተነፍገው ይታሰሩ እንጂ፤ ለእውነት የቆሙ ወገኖች ግን ለመልካም ስራቸው ሽልማትን አልነፈጓቸውም::
ማርቲን ሉተር ኪንግ በበርሚንግሃም እስር ቤት ታስሮ ቢማቅቅም የአሜሪካም ሆነ የአለም አቀፉ ማህበረሰብ አልዘነጋውም:: ቆይቶም ቢሆን የአለም አቀፉ ኖቤል ተሸላሚ እስከመሆን ደርሷል:: ዛሬ በእስር ላይ የሚገኙት የነጻው ፕሬስ ጋዜጠኞች የኖቤል ተሸላሚ ባይሆኑም አለም ግን አልረሳቸውም:: ከታሰሩበት የጨለማ ወህኒ ቤት ጀርባ፤ ከብረት ፍርግርግ እና ከግድግዳዎቹ ባሻገር በመቶዎች፣ በሺዎች እና በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰዎች እነዚህን ጋዜጠኞች በመልካም ስራቸው ያስታውሷቸዋል; ይዘክሯቸዋል:: ስለሆነም የጻድቃን ሞት፤ የሰማዕትነት ጽድቅ ተደርጎ እንደሚቆጠረው ሁሉ… የነ እስክንድር፣ ውብሸትና ርዕዮት እስር፤ ከቶውኑ ዋጋ ቢስ እና ፍሬ አልባ ሊሆን አይችልም::
ኢትዮጵያ ውስጥ በነበርኩበት ወቅት በፕሬስ ጉዳይ ተደጋጋሚ የሆነ እስር ደርሶብኛል:: በ’ነዚህ የእስር እና እንግልት ጊዜያት ግን… ከጨለማው እስር ቤት ማዶ ለምን እንደታሰርኩ የሚረዱ ሺዎች በመኖራቸው ሁልጊዜ እጽናና ነበር:: በተደጋጋሚ እስር ቤት እየመጣ የሚጠይቀኝ እና የዋስ መብቴን አስጠብቆ ከእስር እንድወጣ ያደርገኝ የነበረው ወላጅ አባቴ፤ “የታሰርከው ሰርቀህ ወይም ሌላ ወንጀል ሰርተህ ሳይሆን፤ እውነትን ስለተናገርክ ነው:: ስለዚህ አንገትህን ቀና ልታደርግ እንጂ ልትሸማቀቅ አይገባህም::” የሚል አጽናኝ ቃል ሁሌ ይነግረኝ ነበር:: ዛሬ አባቴ በህይወት የለም:: ቃሉ እና ምክሩ ግን አብሮኝ አለ:: በእስር ላይ ለሚገኙ የነጻው ፕሬስ ጋዜጠኞች፤ “አንገታችሁን ቀና አድርጉ!” የሚለውን መልዕክት አጋራቸዋለሁ::
ዛሬ በጋዜጠኞቻችን ላይ የተለያዩ ክሶች ተመስርቶባቸው መታሰራቸው ሳያንስ; ከታሰሩም በኋላ በሃሰት ሊወነጅሏቸው የሚሹ ብዙ ግራ ዘመም ሰዎች መኖራቸውን ታዝበናል:: በአሜሪካ ከፍተኛ የአየር ሽፋን አግኝቶ ዲሞክራቶችን በመሳደብ የሚታወቀው ራሽ ሊምቦ የተባለ ጋዜጠኛ በቅርቡ ኔልሰን ማንዴላ በሞት ሲለዩ… “ብታምኑም ባታምኑም ኔልሰን ማንዴላ አሸባሪ ነበሩ::” ብሎ ሰፊ ሙግት ፈጥሮ ነበር:: ይህ አባባሉ ለኛ እና ለሌሎች አፍሪቃውያን ሊገርመን ይችል ይሆናል:: ነገር ግን የራሳቸው አመዛዛኝ ህሊና ያልፈጠረባቸውና ይህን ሰው በጭፍን የሚከተሉት ሰዎች “አዎ ማንዴላ አሸባሪ ነበሩ” ብለው ቢሉ ሊገርመን አይገባም::
ዛሬም ባገራችን በተመሳሳይ መልኩ የነርዕዮት አለሙን መልካም ስም ጥላሸት ለመቀባት እላይ ታች የሚሉ ሰዎች ሊኖሩ ይችላሉ… እኛ ግን እንላለን:: “ወንጀል አልሰራችሁምና አንገታችሁን ቀና አድርጉ!” ስማችሁ ከቃሊቲና ከቂሊንጦ እስር ቤቶች በላይ፤ በጠራው ሰማይ ላይ ያንጸባርቃል፤ ቃለ ሃቃቹህ በአየር ናኝቶ… ኢትዮጵያዊያን ባሉበት ሁሉ በመላው አለም ላይ ተሰራጭቷል::
የማርቲን ሉተር ኪንግ ልደት ሲከበር መልካም ስራዎቹ እንደሚወደሱ ሁሉ፤ ዛሬም ሆነ ወደፊት የነርእዮት አለሙ ልደት ሲከበር መልካም ስራዎቻቸው በተደጋጋሚ ይነሳሉ ይዘከራሉ:: ዛሬ ማንዴላን አሸባሪ ብለው የሚከሱ ሰዎች እንደመኖራቸው መጠን; በተመሳሳይ መልኩ ለነርእዮት አለሙ ተመሳሳይ ስም የሰጡና ያሰጡ… ለመስጠት እና ለማሰጠት የሚጥሩ ሰዎች አሉ:: እኛ ግን የተለኮሱ ሻማዎች ይዘን ልደት ስናከብር; የብርሃናችን ጮራ፤ ሌሎች የፈጠሩትን የጨለማ ድባብ ሰንጥቆ… አንዳች ብርሃን እንደሚፈነጥቅላቸው በማመን ነው:: ዛሬ የርዕዮት አለሙን የልደት ቀን ስናከብር፤ ያለፍትህ የታሰሩትን ፍትህ የሚፈልጉትን፤ ነጻነት የተጠሙትን ነፍሶች በማሰብ ጭምር ነው::
መልካም ልደት – ርዕዮት!
ምንጭ ዘ-ሐበሻ

Monday, January 20, 2014

On Behalf of Semayawi Party, Thanks!

Alemayehu G Mariam
Semayawi with MLKThank you one and all who came out to the town hall meetings in the U.S. and Europe over the past several  weeks and supported Semayawi Party!
In a report last week, Ethiomedia.com described Semayawi Party (SP) as the “newest opposition sensation” which “raises new hopes” for nonviolent change in Ethiopia. Yilikal Getnet, Semayawi Party’s young and dynamic chairman, presented Ethiopians in various U.S. and European cities his party’s vision of the Beloved New Ethiopia founded on hope, peace and unity.
Beginning with the first North American town hall meeting in Arlington, VA on December 15, 2013, Yilikal told his audiences that he did not come to the U.S. to solicit financial support or to beg for money. His primary mission was to introduce his party to Ethiopians living abroad, share with them his Party’s vision, positions and programs, review some of its humble accomplishment in the short time the Party has been in existence and most importantly to answer any and all questions  about the Party. He did an outstanding job as the spokesman-in-chief of his Party. He answered all questions put to him without evasion or obfuscation. He addressed policy issues with thoughtfulness and insight. His presentations were complete with anecdotal and statistical facts. He awed his audiences with his razor sharp logic and spellbinding eloquence and wit. I am proud that I was able to stand beside Semayawi Party and Yilikal during this tour and show my unreserved support.
I thank all of those Ethiopians in the Washington, D.C. area, Atlanta, Houston, Dallas, San Jose, Los Angeles, Las Vegas and Seattle for their moral support and financial help to Semayawi Party. Thank you all; I am so proud of you!
On behalf of Semayawi Party Support Group North America, I thank all of those Ethiopians who showed up at the town hall meetings, listened attentively, asked challenging questions and gave generously. Most importantly, on behalf of Semayawi Party I thank all party members and active supporters who braved the rain, snow, sleet and gloom of night to attend the meetings and show their unwavering support. Your support has made all the difference.
When I asked Yilikal of his general impressions of his first ever U.S. tour, he was effusive in his gratitude and praise. He was awed by the passionate patriotism of the Ethiopians he met; he was deeply moved by their heartfelt concerns for the future of the country; and he is inspired by their advice and counsel to help Ethiopia’s youth. He is grateful not only for the extraordinary support Semayawi Party received in the U.S. in such a short time but also the respect, love and understanding he was shown by all.
Scenes from the tour
The Semayawi Party tour was at once an educational, inspirational, confirmational, exceptional and even emotional experience for all of us. For me, the tour represented memorable “moments of truth”. I had written and talked about Ethiopia’s youth and their historic destiny for so long that it was a dream come true to stand on the side of a political party (and in my view a youth movement) that is formed by youth, for the youth and of the youth. After all, 70 percent of Ethiopia’s population is today under the age of 35.
It was a special honor and privilege for me as a member of Ethiopia’s Hippo Generation (older generation) to work so closely with members of the Ethiopia’s Cheetah Generation (younger generation). These young people were amazing. I marveled at the agility of their minds, dazzled by their insights and foresightedness, overwhelmed by their decisiveness in taking action, fascinated by their proficiency in the deployment of technology, awe-struck by their technical organizational skills and thrilled by their harmonious working relationships.  I confess I thoroughly enjoyed my role as a full-fledged honorary Cheetah (though I regard myself to be a “Chee-Hippo”, a member of the intermediate generation whose job is to build bridges to connect the Cheetah and Hippo Generations) giving  advice and counsel, consulting, answering questions and showing up wherever I was needed as a witness for Semayawi Party.
The one word that best describes our collective experiences in the Semayawi Party tour is “humbling”.  We were overwhelmed by the passionate convictions of fellow Ethiopians who are determined to help birth the Beloved New Ethiopia that treats all of its citizens equally and respects the rights and dignity of each citizen. We were inspired by those who rejected all attempts to divide and dehumanize Ethiopians along ethnic, religious, regional and linguistic lines. We were grateful to those who schooled us on the mistakes of the past and showed us ways of avoiding known pitfalls. We were emboldened by those who assured us that we should never fear failure itself but the fear of failure which is paralyzing and incapacitating. We were comforted by those who promised and pledged to support us for as long as its takes so long as we continue the peaceful struggle for change. We were delighted by the curiosity of those genuinely interested in finding out about Semayawi Party.
We also experienced a few somber notes. We were saddened by the cynicism of some who had given up hope. “All of those who have come before you have failed. You probably will too”, they declared. We understood their disappointments. We were amused by the arrogance of others who thought the young people just did not know what they were doing and tried to lecture us on what should and should not be done. We did not mind. We are always ready to learn. We were engaged by the doubting Thomases. “We have seen them come and go? You don’t sound much different from the others. What makes you so special, so different?”, they would ask pointedly with slight derision. Doubt is the foundation of faith and we did all we could to convince them that the New Beloved Ethiopia will be built by Ethiopia’s young people, with the support of the older generation of course. We listened patiently and respectfully to those who bellyached, grumbled, moaned and groaned. They had legitimate reasons to do so.
We also learned a great deal about ourselves and what we must do. We had to defend and explain our mode of struggle. “How could you expect to win against a powerful regime with a proven history of barbaric brutality, with all the  weapons of war and police and security forces?” Our response was the same as Gandhi’s “Strength does not come from physical capacity”, nor does it come from guns, tanks and war planes. “It comes from an indomitable will.” We have the indomitable will to press on with our nonviolent struggle. An indomitable will powered by love is invincible.
We preached that change must first take place in the hearts and minds of individual men and women before it can happen in society at large. We must therefore struggle with the demons of hate and revenge that have taken residence in our hearts before we can struggle with those who seek to demonize us. We are tolerant and respectful of those who disagree with our ideas, methods and means. In matters of principle, we shall always stand our ground. We believe in nonviolent social and political change. On this principle, we can agree to disagree with anyone without being disagreeable. We believe we should be judged on our own merits, and not on the achievements or mistakes of others. We are keenly aware that we must practice what we preach. That means we must maintain the highest standards of accountability, transparency and civility. We know our supporters expect us to be different, show more integrity and forthrightness and be open minded. We shall aim to practice these virtues in our daily lives.
The struggle ahead: Ethiopian David against the TPLF/EPDRF Goliath
The struggle for nonviolent change in Ethiopia will be a difficult one requiring great sacrifices. We are not unmindful that the regime will do everything in its power to weaken and destroy Semayawi Party. We take it for granted that the regime in power in Ethiopia today will arrest, jail, torture, conduct kangaroo trials and kill Semayawi Party members. To predict regime persecution of Semayawi Party persecution is like predicting the sun will rise tomorrow. We know the regime’s standard operating procedure for the last 23 years. Semayawi Party leaders and members are not afraid. They are not afraid of goons with guns. There is a new breed of young Ethiopian leaders on the rise and unafraid of thugs clad in the stolen mantle of state power. Eskinder Nega, Reeyot Alemu, Woubshet Taye, Andualem Aragie, Olbana Lelisa, Bekele Gerba, Abubekar Ahmed and so many others languish in the infamous Meles Zenawi Prison in Kality because they refused to be intimidated and bullied by the regime in power.
Those of us committed to nonviolent change in Ethiopia struggle to win the hearts and minds of all Ethiopians. We measure our victory by the number of people we are able to convince to choose the path of peaceful change. Those in power measure their victories and how powerful they are by the number of Ethiopian corpses they can scatter on the battlefield. I believe the outcome of this struggle was foretold and foreordained long ago. There was once a mighty man called Goliath. Clad in armor of iron and brass, Goliath would strut over the hill day after day and terrorize the people. Feared by all, no one would dare challenge Goliath. Then came a meek young shepherd named David who feared no one but God. David decided to fight Goliath not for the rewards of gold, silver or riches but to restore the pride, dignity and faith of his people. David was offered a sword, spear, armor and an iron helmet. He chose to fight Goliath with a sling and five smooth stones. Goliath huffed and puffed and taunted little David to come out and fight him. David met Goliath and Goliath was no more.
Semayawi Party is Ethiopia’s David standing up to a fearsome and loathsome Goliath known as the TPLF/EPDRF. Semayawi Party stands up against the mighty TPLF/EPDRF Goliath armed to the teeth with guns, bombs, tanks, artillery and warplanes. Semayawi Party stands against a Goliath with a legion of repressive police and security cadres unrivalled in Africa today. Semayawi Party stands against a Goliath backed by billions of dollars of international aid money, loans and stolen cash from the people. Semayawi Party stands against a Goliath in whose blood courses the poison of hate and division, in whose mind circulates falsehoods and deceit, in whose spirit dwells despair and misery and in whose heart darkness itself lives and breathes.
Semayawi Party is poised to fight the TPLF/EPDRF Goliath armed only with a sling and five smooth pebbles called Love, Truth, Hope, Peace and Unity. In the end Semayawi Party will win against the TPLF/EPDRF Goliath; and Goliath will be saved, saved indeed, because Semayawi Party’s pebbles do not kill; they only heal.  It is an honor for me to be the water carrier for Ethiopia’s David standing up to the TPLF/EPDRF Goliath.
Let’s give Semayawi Party a chance, a fighting chance
It was a distinct honor and privilege for me to be the “keynote speaker” at the various Semayawi Party town hall events. I did not consider myself a “keynote speaker”. I showed up as a volunteer “witness”.  I became a witness to ask, and hopefully to convince, Ethiopians in the U.S. to give Semayawi Party a chance, a fighting chance, a sporting chance as it struggles to stand up to the TPLF/EPDRF Goliath.
I wholeheartedly support Semayawi Party because I believe Ethiopia’s young people are the only ones with the vision, energy, intelligence and passion to change the destiny of their country and build the New Beloved Ethiopia. Today, 70 percent of Ethiopia’s estimated 94 million people consists of young people under the age of 35. The vast majority of the victims of human rights violations in Ethiopia today are young people. The targets of political persecution and harassment, arbitrary arrests and detentions, torture, abuse and maltreatment in the prisons are largely young people. Young Ethiopians are disproportionately impacted by pandemic unemployment and lack of educational and economic opportunities. The yearning of Ethiopia’s youth for freedom and change is self-evident. Change, peaceful change, will come to Ethiopia but it will be like the arrival of train that is late. The only question is whether the country’s youth will seek change through increased militancy or by other peaceful means.”
For the past eight years, I have tried to make a small contribution to the human rights struggle in Ethiopia. It is a responsibility I took much later in life. I have no greater honor than to hear Ethiopian Cheetahs and Hippos telling me that they have learned something from my weekly commentaries or speeches. What more can a teacher ask?
In the past I have asked, urged and pleaded with my readers to support the cause of human rights and the dignity of the individual. Now, I ask, actually I plead, with my readers to support Ethiopia’s young people and Semayawi Party which I believe represents the interests of the young people more than any other party in existence today.
I do not want my readers to support Semayawi Party not because I support them, but because they deserve support on their own merits. When I decided to support Semayawi Party, I asked a few questions: 1) Do I truly believe in nonviolent social and political change?  2) If I truly believe in nonviolent change, who do I believe is best positioned in Ethiopia today to effect such a change? 3) If the young people can effect such a change, what can I do to help them?
We can all help Semayawi Party in the Ethiopian Diaspora in a variety of ways. Those with means can help financially to the extent of their abilities. Semayawi Party needs a lot of financial help to do its organizational work and to sustain its outreach efforts. There are other equally important ways we can provide support to Semayawi Party. Learning about Semayawi  Party and educating others is valuable support. Providing Semayawi technical support in all areas including policy analysis and development is vital, and Ethiopian scholars and academics could play a critical role in this regard. Spreading Semayawi’s message of hope, unity and peace is more important support than any other form of support. Defending Semayawi against false accusations and fear and smear campaigns is invaluable support. Giving moral support and inspiring Semayawi Party leaders and members to greater heights is priceless. Cheerleading for Semayawi is support that every patriotic Ethiopian could perform every day.
On a personal note…
It was an amazing experience for me to work with the young people in the Semayawi Party support groups. For so many years I have sought to teach, preach and reach out to Ethiopia’s young people in my weekly commentaries and occasional speeches. I am delighted to serve in the capacity of advisor to the young professionals, business entrepreneurs and university students doing the heavy lifting for Semayawi Party stateside.  The proliferation of support groups for Semayawi Party throughout the world rekindles my belief that Ethiopian Cheetahs united can never be defeated.
I want to share a few personal observations  about  Semayawi Party chairman Yilikal Getnet. Over the past eight years, I have met many Ethiopian political, business and community leaders in one context or another. Many of these leaders have impressive qualities. I consider character the most important quality in any political leader.
Yilikal is a young engineer who has given up on his professional ambitions and subordinated his family’s interest to work for nonviolent change in Ethiopia. It takes great character and personal integrity to make such a choice. I observed  different aspects of Yilikal’s character during the tour. He proved himself to be a man of principle. He was challenged that his nonviolent way idealistic and doomed to fail. He argued convincingly that violence is the weapon of the weak. No one can change hearts and minds by force and violence. He was challenged to tow the politically correct line that Ethiopia must remain a collection of  klililistans (kilils) and the only rights that matter are the rights of “nations and nationalities”.  He convincingly defended the principle that when individual rights are respected and preserved, group rights are necessarily protected and preserved. He was challenged that the brutal regime could persecute him, jail, torture and kill him and others in the party  leadership . He was unafraid because he and other Semayawi Party leaders formed their party ready to do the right thing and make any sacrifices for their country and fellow Ethiopians.
When Yilikal was lectured and hectored that Semayawi Party was creating divisiveness by separating the young and old, he categorically denied such allegations. As a matter of principle, he made it clear that there has to be a generational division of labor. The older generation of Ethiopians could play a decisive role as advisors and supporters while the younger generation did the heavy lifting and suffered the street beating and jailing.  However, only the Cheetahs have the will power, stamina, fortitude, energy and creativity to bring about lasting change. I said, “Amen!” Yilikal was chastised for not “uniting” his party with others to oppose the ruling regime. He said his party works and coordinates with other parties but there are fundamental differences in policies, strategies and tactics that make “unity” challenging. He wondered why the rest of us in the Diaspora who urge opposition unity inside the country are unable to teach by example by uniting and working together against the regime on the outside.
There is one quality that I appreciated most in Yilikal, his humility.  Yilikal is a young man of small physical stature. He has on more than one occasion commented on the fact that he is somewhat vertically challenged. In reality he is truly a humble giant. He showed genuine respect and appreciation to all those he met. He listened attentively and patiently to them. He showed restraint and good judgment even when asked deliberately  provocative questions. He never lost his cool and told it like it is when it comes to the truth. He never presented himself as a “party leader” or someone special. He was easily approachable and showed candor in his public and private dealings.
I appreciated Yilikal’s sense of humor.  As we toured the various  sites, I tried to convince him that there were indeed Cheetahs and Hippos populating the town hall meetings. Looking from the stage into the audience he could only see younger Cheetahs sitting next to older Cheetahs. He wanted me to point which ones were the Cheetahs and Hippos. I could not. There were only older Cheetahs sitting next  to younger Cheetahs. I learned an important lesson. Being a Cheetah or a Hippo is as much a state of mind as a state of being.  Thank you younger and older Cheetahs  for coming out and supporting  Semayawi Party Cheetahs!
Give Semayawi Party a chance! 
Semayawi Support-North America
P.O. Box 75860
Washington DC, 20013
Website:  http://www.semayawiusa.org/
Email: info@semayawiusa.org
To donate: http://www.semayawiusa.org/donate/
Donation can be made by check/money order, PayPal or direct deposit to Semayawi Support-North America account.
Thank you…
source  Ethiopian media forum.

Sunday, January 19, 2014

ዛሬ የሚያስፈሯሯችሁን እስከ ዘላለሙ የማትሰሙበት ግዜ ይመጣልና አትፍሩ

ህወሃት የሚያራምደው የዘረኝነት ፖለቲካና፤ የተዘፈቀበት የሙስና አዘቀት ሊወጣ ከማይችልበት አዙሪት ውስት ከተውታል።ከእንግዲህ ወዲህ ለህወሃቶች የቀራቸው አንድ አማራጭ ብቻ ነው። ሁሉንም ዜጎች በዘረኝነት ሰንሰለት አስሮ ቀጥቅጦ እና አፍኖ መግዛት ቀጣዩ ቅዥታቸው ነው።
የዚህ አፍኖ የመግዛት ቅዥታቸው መገለጫም ዜጎች ህወሃት ስለሚፈፅመው ወንጀል ምንም ዓይነት መረጃ እንዳያገኙ ማድረግ አንዱ ነው።ህወሃት የሚፈፅመው ወንጀል ከህዝብ ዓይንና ጆሮ ተሠውሮ እንዲረሳ ይመኛል። ይሄን ምኞቱን እውን ለማድረግም ሌሎች ነፃ ሚዲያዎችን አሸባሪ ማለት ወይም ደግሞ ሌላ የተሰወረ አጀንዳ ያላቸው እያለ ማላዘንን ሥራየ ብሎ ተያይዘውታል። ከሰሞኑ አዲስ አበባ ውስጥ የሚታተሙ ስምንት የግል ህትመቶችን አሸባሪዎች በማለት ክስ መስርተዋል። አስቀድመው ፈርደው ከጨረሱ በኋላ ክስ መመሥረት የህወሃቶች የተለመደ የፍትህ ሥርዓት ነው። በአገሪቷ ታሪክ ውስጥ ለመጀመሪያ ግዜ ከመንግስት ቁጥጥር ውጪ ሁኖ የተቋቋመውን ኢሳትንም አሸባሪ እያሉ ሰሚ አልባ ጩኸት እየጮኹ ነው። የኢሳት ቴሌቭዥንና ሬዲዮንን የሚሰማም በአሸባሪነት ይከሰሳል እያሉ በየዜጎች ደጅ እየተንከላወሱ ለማስፈራራት እየሞከሩ ነው።
እኛ ግን እንዲህ እንላለን !!! አትፍሩ ! አትፍሩ ! አትፍሩ ! ኢሳትን ሰምታችኋል ብሎ የሚያስፈራሯችሁን ለዘላለሙ የማትሰሟቸው ግዜ እየመጣ ነው። የነፃነት ጎህ ቀዶ ሁላችን የፈለግነውን ሰምተን፤ ያልፈለግነውንም የምንተውበት ዘመን እሩቅ አይደለም። ግንቦት ሰባት የፍትህ የነፃነት እና የእኩልነት ንቅናቄም የተቋቋመው ዜጎች ያለማንም ጣልቃ ገብነት የወደዱትን ወስደው፤ የጠሉትን መተው የሚችሉበትን መንገድ ለማመቻቸት ነው። ዘረኞቹ በደምና አጥንት ታውረው ጭካኔን ከጀግንነት ቀላቅለው እኛ ብቻ ወንድ ባሉበት መንደር ሌላ ጀግና ኢትዮጵያዊ ወንድ ገስግሶ የሚመጣበት ዕለት እየደረሰ ነውና እንዳትፈሩ እንመክራችኋለን። ህወሃቶች ዜጎችን ከሰው በታች አድርገው ለመግዛት እንዲመኙ ያደረጋቸው እብሪት የሚተነፍስበት ዘመን እሩቅ አይሆንምና አሁንም አትፍሩ።
ህወሃቶች ከእነርሱ ቁጥጥር ውጪ ያሉ ነፃ ሚዲያዎችን እንደማይታገሱ የታወቀ ነው። ለምን ቢሉ የወንጀላቸው ብዛት፤ የክፋታቸው ጥልቀት ሳይነገር ተሠውሮ እንዲቀር ስለሚመኙ ነው። ይህን ምኞታቸውን እውን ለማድረግም ራሳቸው የሠረቱን ህግ ውልቅልቁን አውጥተው ያፈራርሱታል። ዜጎች መረጃ የማግኘት መብት አላቸው ተብሎ እነርሱ “ህገ-መንግስታችን” እያሉ በሚጠሩት ላይ በማያሻማ ሁኔታ የተቀመጠ ቢሆንም እነርሱ ግን ለራሳቸው ህግ መታመንን አልመረጡም። እንዲያውም እነርሱ ሞተንለታል የሚሉትን ህግ አፈር አስገብተው ራሳቸው ህግ ሆነው ተፈጥረዋል። እነርሱ ህግ ሁነው በመፈጠራቸውም በየዜጎች ደጅ እየተንከላወሱ ኢሳትን ብትሰሙ ወዮላችሁ እያሉ ያስፈራራሉ። ዜጎች ግን የሞኝ ዘፈናቸውን መልሰው መልሰው ለሚያላዝኑ ኢሕአዴጋዊያን ዛቻ የሚንበረከኩ አይሆኑም። አገራቸውን በተመለከተ ማንኛውንም መረጃ ለመስማት ያላቸውን ነፃነትም ለምናምንቴዎች አሳልፈው የሚሰጡ አይሆኑም።
ጎሬቤታችን ኬኒያ ከአስር በላይ የግል ቴሌቭዥን ጣቢያዎች አሏት።በርካታ በአጭር ሞገድና በኤፊኤም ሞገዶች የሚተላለፉ ሬዲዮኖችም አሏት። የኬኒያ መንግስት ለዜጎቹ ክብርና ፍቅር ስላለው የተቻለውን ያክል ነፃ ሚዲያ እንዲኖር ይጥራል። ለህዝቡ ክብርና ፍቅር የሌለው ህወሃት ግን በወረቀት ላይ በፃፈው ህግ ዜጎች መረጃ የማግኘት መብታቸው ያልተገደበ ነው ቢልም በተግባር ግን የዜጎችን መረጃ የማግኘት መብት ያፍናል። ነፃ ሚዲያ እንዳይፈጠር ለማድረግ፤ የተፈጠሩትንም ለማጥፋት ግዜውንና የአገሪቷን ሃብት በከንቱ ያባክናል። ህወሃት ከድሃ ጉሮሮ እየነጠቀ ኢሳትን ለማፈን በሚሊዮን የሚቆጠር ዶላር አባክኗል። የአገሪቷ የህግ ተቋማትም ሌቦችንና ነፍሰ ገዳዮችን መከታተል ትተው በነፃነት እንፃፍ ብለው የተነሱ ጋዜጠኞችን በማሳደድ የአገሪቷን የሥራ ሠዓትና ሃብት በከንቱ ያባክናሉ። ህወሃቶች ይሄው ናቸው። አገር፤ ወገን፤ ህዝብ የሚባል ነገር በሂሊናቸው ያልተፈጠረ፤ እነርሱ ብቻቸውን ሌላውን ተጭነው መኖር የሚፈልጉ፤ የጨካኞችና የእብሪተኞች ስብስብ መሆኑን መዘንጋት አያስፈልግም።
የተከበራችሁ ያገራችን ዜጎች !
አገራችሁን በተመለከተ መረጃ ማግኘት የዜግነት መብታችሁ መሆኑን እንዳትረሱ። ይሄም እነርሱ “ህገ-መንግስት” ብለው በሚጠሩት ላይም በግልፅ ተቀምጧል። ይሄን በህግ ደንግጎ ሲያበቃ ኢሳትንና ሌሎችን ነፃ ሚዲያዎችን መስማት አትችሉም ሲል የማውቅላችሁ እኔ ነኝና የምትሰሙትንና የምታዩትን የምመርጥላችሁ እኔ ነኝ እያለ መሆኑን አስታወሱ። ይሄ ማለት አዋቂው እኔ እንጂ እናንተማ ክፉን ከደጉ ለመለየት ገና አልደረሳችሁም ማለት መሆኑንም መገንዘብ ያስፈልጋል።መንግስት ነኝ ብሎ በአገሪቷ ጫንቃ ላይ የተቀመጠው ህወሃት-ኢሕአዴግ ህዝቡን የማያከብር ብቻ ሳይሆን ለህዝብ ያለው ንቀትም ወሰን የሌለው ሁኗል። ይሄ ዘረኛና ዘራፊ ቡድን ክብራችንን አዋርዶና አንገታችንን አስደፍቶ ሊገዛን አይገባውም። ፍርሃት ይብቃ። ህወሃት እየፈጠረ ያለው ፍራቻን መሸሸ አይገባም፤ ይሄን ፍርሃት መጋፈጥ የጀግና ተግባር ነውና ለክብራችሁና ለነፃነታችሁ ስትሉ ፍርሃቱን ተጋፈጡት እንጂ አትሽሹት።
በዚያ በጨካኞች መንደር ሁናችሁ በሠላማዊ ትግል ብቻ ለውጥ እናመጣለን ብላችሁ የተደራጃችሁ የፖለቲካ ድርጅቶችም መረጃ የማግኘት፤ መረጃ የመሰብሰብ እና የማሰራጨት መብታችሁ ነው ብለን ልንነግራችሁ አንዳዳም። በነፃ ሚዲያ መናገርም ሆነ ለማንኛውም ሚዲያ መረጃ የመስጠት ማንም የሚሰጣችሁ መብት እንዳልሆነ ታውቃላችሁ። እኛ እንደምንገምተው ኢሳትም ሆነ ሌሎች ነፃ ሚዲያዎች የእናንተም ሃብት ናቸው። ህወሃት-ኢሕአዴግ አትስሙ ወይም ደግሞ አትናገሩ ሲላችሁ ያንን የእብሪተኛ ትዕዛዝ አለመቀበላችሁን ለነፃ ሚዲያዎች መረጃ በመስጠትና ሃሳባችሁን በነፃው ሚዲያ በመግለፅ እምቢተኝነታችሁን በማሳየት ለምትመሩት ህዝብ አርአያ እንድትሆኑ ብናሳስባችሁ ደፈሩን እንደማትሉ ተስፋ እናደርጋለን። ከዚህ አንፃር ሰማያዊ ፓሪትና አንድነት ያወጡትን መግለጫ በአድናቆት የምንመለከተው መሆኑን ለማስታወቅ እንወደላን።
ለህወሃት-ኢሕአዴጎች !
ራሳችሁን ከአሸባሪ ምግባርና መዝገብ ማስፋቅ ሳትችሉ የነፃነት ፍላጎት ያላቸውን ሁሉ አሸባሪ እያላችሁ ማላዘናችሁን የምታቆሙበት ግዜ እየመጣላችሁ ነው። እናንተ ከላይ ሁናችሁ ህዝቡ ከሥር ሁኖ እናንተን ተሸክሞ ለዘላለም እንደማይኖር አበክረን ልናሳውቃችሁ እንወዳለን።በየሰው ደጅ ካድሬዎቻችሁን ልካችሁ ኢሳትን አትስሙ እያላችሁ የማስፈራራት እብሪታችሁ ረገብ የሚልበት ግዜ እየመጣላችሁ ነው። ዛሬ ህዝባችንን የእኛን ብቻ ስሙ፤ የእነርሱን አትስሙ ማለታችሁ ለህዝባችን ያላችሁን ንቀት የሚያመላክት ነው።ህዝባችንን እንደናቃችሁና እንዳዋረዳችሁ አትቀጥሉም። የነፃነትን ፍላጎት አፍናችሁ አታቆሙትም። የፍትህ ጥማታችንን በአፈሙዝ ልትገቱት አትችሉም። የእኩልነትን ጥያቄ በውሸትና በዛቻ አታዳፍኑትም። እውነት እውነት እንላችኋለን ወንጀላችሁ ሳይነገር፤ በስውር የዘረፋችሁት በአደባባይ ሳይገለጥ አይቀርም። እኛም ቀንና ማታ ለዚያ ግብ ሳናገራግር እየሰራን ነው። በአገራችን የነፃነት ጎህ ሳይቀድ ለሽፋሽፎቶቻችን እንቅልፍ፤ ለስጋችንም ዕርፍት አይሆንም። የዘረኞችና የዘራፊዎች ጀንበር ሳትጠልቅ፤ የእኩልነት ናፋቂዎች ጎህ ሳትቀድ አናርፍም። ያነገታችሁት መሣሪያ የሸንበቆ ምርኩዝ እስከ ሚሆን የጀመርነውን ትግል ዕለት ዕለት እያጎለበትነው እንቀጥላለን።
ህወሃት-ኢሕአዴጎች ሆይ ስሙ! ይሄን ህዝብ ከሚችለዉ በላይ ገፍታችኋታል። ህዝቡም ሊሸከማችሁ ከሚገባ በላይ ተሸክሟችኋል።እንዲህ ህዝባችንን መፈናፈኛ አሳጥታችሁ እና እስከ ልጅ ልጆቻችሁ ረግጣችሁ ለመግዛት ያለማችሁት ህልም በህልምነቱ ብቻ እንደሚቀር ቅንጣት ታክል ጥርጣሬ አይግባችሁ። ትግላችን ጥሩ መሠረት ይዟል። ከዚህ በኋላ ወደ ኋላ የሚመልሰን ምድራዊ ኃይል የለም።እውነት እውነት እንላችኋለን ለዘላለም ኢትዮጵያዊያንን አዋርዳችሁ የመግዛት ህልማችሁ ቅዥት መሆኑን ደግመን ልንነግራችሁ እንወዳለን።
በህወሃት-ኢሕአዴግ ውስጥ ሁናችሁ የነፃነት፤ የፍትህ እና የእኩልነት ጥያቄያችንን የምትጋሩን ወገኖቻችን እሰክ አሁን የምታደርጉት የውስጥ ትግል ፍሬ እያፈራ ነው። ፍሬውን በራሪ ወፍ እንዳይለቅመው የተለመደው ጥንቃቄ እንዳይለያችሁ ይሁን። አሁን ህዝቡ መረጃ እንዳያገኝና፤ መረጃ እንዳይሰጥ የሚሞከረው ሙከራ ህገ-መንግስት ተብየውን የሚጥስ መሆኑን ታውቃላችሁ። ይሄን ካድሬው ሁሉ እንዲገነዘበው የውስጥ ትግሉ ተጠናክሮ መቀጠል ይኖርበታል። ራሱ ያወጣውን ህገ መንግስት አፈራርሶ ከትቢያ የሚቀላቅል ቡድን በምን ሞራል ብቃት ነው ሌላውን ህገ-መንግስቱን ሊንዱ ነበር እያለ የሚከሰው ? በኢትዮጵያዊያን ላይ የተጫነው ህገ-መንግስት በህወቶች ሲፈርስ ትክክል ፤በሌላው በተግባር እንዲውል ሲጠየቅ ደግሞ ስህተት ሁኖ በአሸባሪነት የሚያስከሥሥ መሆኑን ግንዛቤ መጨበጥ ይጠቅማል።
በመጨረሻም በህወሃት-ኢሕአዴግ የጭቆና ቀንበር ሥር ለምትንገላቱ ወገኖቻችን ሆይ ! አትፍሩ። ይህን የሚያስፈራራችሁን አካል እስከ መጨረሻው የማትሰሙበት ዘመን እየመጣ ነው። አሁን ፍርሃታችሁን ግደሉት።የምትሰሙትንና የምታዩትን እኔ ነኝ የምመርጥላችሁ ከሚል እብረተኛ እጅ ራሳችሁን ለማላቀቅ የግንቦት ሰባት ንቅናቄ እያደረገ ያለውን የነፃነት፤ የፍትህና የእኩልነት ትግል ተቀላቀሉ።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!!

Saturday, January 18, 2014

የወያኔን የሚዲያ አፈና ማመከን የጊዜው አጣዳፊ ተግባር ነው

ዘረኛዉ የወያኔ አገዛዝ የአገራችንን በትረ ሥልጣን ከተቆጣጠረበት ጊዜ ጀምሮ ህዝባችን ስለራሱና ሰለአገሩ ምንም አይነት መረጃ ከአማራጭ የመገናኛ ብዙሃን ምንጮች እንዳያገኝ ያሉትን ዕድሎች በሙሉ ድርግም አድርጎ ዘግቶ ኖሮአል።
የወያኔ መሪዎችና ተሿሚዎች በየግላቸው ምንም ቁብ በማይሰጡትና ተቃዋሚዎች እንዲያከብሩት ነጋ ጠባ በሚወተውቱት የአገሪቱ ህገመንግሥት አንቀጽ 29 ዕውቅና ካገኙ የዜግች መብቶች አንዱ ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ ተፈጥሮአዊ መብት ሆኖ ሳለ እየተካሄደ ያለውን የሥልጣን ብልግናና አገሪቱን እያራቆተ ያለውን ዘረፋ በመተቸታቸው ብቻ በአንድ ወቅት እንደ አሸን ፈልተው የነበሩ የነጻ ጋዜጣ አዘጋጆችና አሳታሚዎች በሽብርተኝነት ተወንጅለው ከፊሉ ከአገር እንዲሸሽ ሌላው አፉን ዘግቶ እንዲቀመጥ አለያም የፈጠራ ክስ እየተመሰረተባቸው እስር ቤት እንዲማቅቁ ተደርገዋል። አሁንም በመደረግ ላይ ናቸው። በወያኔ ሃሳብን በነጻነት የመግለጽና የዜጎች መረጃ የማግኘት መብት አፈና የአሜሪካና የጀርመን መንግሥታት በየግላቸው የሚያስተዳድሩዋቸው የአሜሪካና የጀርመን ድምጽ ሬዲዮኖች እንኳ ከጥቃቱ ማምለጥ ስላልቻሉ እነሆ እስከዛሬ ያልተቋረጠ የማጥላላት ዘመቻ ይካሄድባቸዋል።
ዜጎች ሃሳባቸውን በነጻነት መግለጽ ከቻሉና ከየትኛውም መዲያ መረጃ የማግኘት መብታቸው ከተረጋገጠ ሥልጣን ላይ ውሎ እንደማያድር ጠንቅቆ የተረዳው የወያኔ አገዛዝ በዚህ የሚዲያ አፈና ተግባሩ በመቀጠል ከሰሞኑ የኢትዮጵያ ሳታላይት ቴለቪዥንና ሬዲዮን እንዲሁም ህዝብ አልፎ አልፎ ሃሳቡን ለመግለጽ በሚገለገልባቸው ጥቂት የአገር ውስጥ ህትመቶች ላይ የተለመደውን የጥቃት ጅራፉን ለማሳረፍ ታጥቆ ተነስቶአል። ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ላይ በመረጃና ደህንነት መሥሪያ ቤቱ ተዘጋጅቶ የህወሃት ቀድሞ ታጋዳላዮች በሚቆጣጠሩትና እንደግል ንብረታቸው በሚፈነጩባቸው የኢትዮጵያ ቴሌቪዥንና ሬዲዮ የተሰራጨው ዘገባ እንደሚያመለክተው ከአሁን ቦኋላ ማንኛዉም የመንግስት ባለስልጣን፤ የገዢዉ ፓርቲ አባላትና የተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎች ምንም አይነት ቃለመጠይቅ ለኢትዮጵያ ሳተላይት ቴለቪዥንና ሬዲዮ እንዳይሰጡ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቶአል። ማስጠንቀቂያውን ተላልፎ በተገኘ ማንም ሰው ወይም ድርጅት ላይ የአሸባሪነት ወንጀል ክስ እንደሚመሰረትበትም ዛቻና ማስፈራሪያ በተለመደው የቃላት ጋጋታ ተገልጾአል።
ይህ ከሰሞኑ የወያኔ ብሄራዊ መረጃ ደህንነትና ኮሚኒኬሽን መስሪያቤት ያወጣዉ ማስጠንቀቂያ አዘል መግለጫ የሚያሳየን ነገር ቢኖር ወያኔ ኢትዮጵያ ዉስጥ ዜጎች የሚናገሩትን ፤ የሚጽፉትን፤ የሚያነቡትንና የሚሰሙትን ብቻ ሳይሆን የሚያስቡትንና ሊደግፉት ወይም ሊቃወሙት ይችላል ተብሎ የሚጠረጠረውን ሁሉ አስቀድሞ ለመቆጣጠር ፍላጎቱ ያለው መሆኑን ነው።
ከሰሞኑ መግለጫ የተለየ ነገር ቢኖር ህዝባችንን በፍርሃት አንገት ለማስደፋት ሲባል የወያኔ ፓርላማ በሽብርተኝነት የፈረጀውን ንቅናቄያችንን ግንቦት 7ንና የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴለቪዥንን በአንድነት የመፈረጅ ስልት ይፋ መደረግ መቻሉ ብቻ ነው።
የወያኔን ቁንጮዎች ጨምሮ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ይገነዘበዋል ብለን እንደምናምነው የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴለቪዥን ኢሳት የተቋቋመው የአገራቸው ጉዳይ የሚያንገበግባቸው ቅን ዜጎች ባዋጡት የገንዘብ መዋጮና በሚሰጡት ያልተቋረጠ የእውቀትና የፋይናንስ ድጋፍ ነው። ተቋሙ ከተመሠረተበት ጊዜ ጀምሮ ላለፉት 22 አመታት በወያኔ የሚዲያ ሞኖፖሊ ተይዞ የኖረውን የአገራችንን አየር ክልል ሰንጥቆ በመግባት ህዝባችን ስለ አገሩና ስለራሱ ጉዳይ በቂ መረጃ እንዲያገኝ በመጣር ላይ ያለ ብቸኛ መገናኛ ብዙሃን ሆኖ በማገልገል ላይ የሚገኝ ነው።
ሃቁ ይሄ ሆኖ ሳለ ለምንድነዉ ታዲያ ላለፉት ሁለት አመታት ስብሀት ነጋን ጨምሮ የተለያዩ የገዢዉ ፓርቲ ቱባ ቱባ ባለስልጣናት ሳይቀሩ በተደጋጋሚ ቀርበዉ በስነ ስርኣት የተስተናገዱበትን ይህንን ሚዲያ የወያኔ ፓርላማ ቀደም ሲል በአሸባሪነት ከፈረጀው ንቅናቄያችን ግንቦት 7 ጋር መወንጀሉ ለምን ይሆን ? መልሱ ቀላል ነው። ከአገዛዙ ያልወገኑ ማናቸውም ሚዲያዎች እንደሚያደርጉት ኢሳት ስርጭቱን ከጀመረበት ጊዜ ጀምሮ ነጋ ጠባ በኢትዮጵያ ቴለቪዥንና ሬዲዮ የሚደሰኮረው ልማትና ዕድገት ተጠቃሚው ሥልጣንን የሙጥኝ ያሉ የቀድሞ ታጋዳላዮችና የቅርብ ዘመዶቻቸው እንጂ ህብረተሰቡ አለመሆኑን በግልጽ ከማጋለጥ ባለመቆጠቡ ጥርስ ውስጥ ገብቶአል። ከዚህም በተጨማር ለምዕራባዊያን ፍጆታና ድጋፍ ማግኛ በየአምስት አመቱ የሚደረገው የምርጫ ተውኔት ወቅት ስለተቃረበ ተቃዋሚዎች አጋጣሚውን ተጠቅመው በዚህ ሚዲያ ያብጠለጥሉኛል፤ የስልጣን ብልግናውንና የሙስናውን ጉዳይ ይዘከዝኩታል የሚል ፍርሃትና ስጋትም አለው። በእርግጥ ዝክዘካው በይስሙላ ምርጫው ላይ ምንም ለውጥ እንደማያመጣ እኛ የጉዳዩ ባለቤቶች ቀርተን ምዕራባዊያን ለጋሾችም አያጡትም። ሆኖም ግን ወያኔ ፈርቶአል ተረብሾአል። ስለዚህም ኢሳትና አሁን በአክራሪ ድርጅቶች ልሳንነት የተፈረጁት የአገር ውስጥ ህትመቶች ከምርጫው በፊት መጥፋት ይኖርባቸዋል። ያ ካልሆነ በመላው አገሪቱ የሰፈነው የሥልጣን ብልግናና የሃብት ዘረፋ የፈጠረው የኑሮ ውድነት ያስመረራቸው ሚሊዮኖች የመጪውን ምርጫ ውጤት አስታከው ሆ ብለው አደባባይ ሊወጡና የአገዛዙን የሥልጣን እድሜ ለማሳጠር ተቃዋሚዎች ለሚያካሄዱት ትግል መሳሪያ ሊሆኑ ይችላሉ ተብሎ ተፈርቶአል። ግንቦት 7 የፍትህ የነጻነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ከብዙ የወያኔ ጥቃትና አፈና ተርፈው አገር ውስጥ በመታተም ላይ በሚገኙ 8 መጽሄቶች እና ለኢትዮጵያዊያን ብቸኛ የመረጃ ምንጭ ሆኖ በማገልገል ላይ በሚገኘው የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴለቪዥንና ሬዲዮ ላይ የተጀመረውን አዲሱን ዘመቻ በቸልታ አይመለከተውም።
መረጃ ሃይል ነውና አገራችን ውስጥ ፍትህ እንዲሰፍን፡ በመልካም አስተዳደር እጦት ሥር እየሰደደ የመጣው ድህነት እንዲቀረፍና ሰላምና መረጋጋት እንዲፈጠር የሚሻ ዜጋ ሁሉ ወያኔ በሚዲያ ላይ የጀመረውን ጥቃት ለማስቆም ከጎናችን እንዲሰለፍ ግንቦት 7 የትግል ጥሪውን ያቀርባል።
ወያኔ በመረጃና ደህንነት መሥሪያቤቱ አማካይነት ያስተላለፈው የሰሞኑ ማስፈራሪያና ማስጠንቀቂያ በተለይም በሰላማዊና ህጋዊ ትግል ወያኔን መቀየር ይቻላል በማለት አገር ውስጥ የሚንቀሳቀሱትን የፖለቲካና የስቪክ ድርጅቶች መተንፈሻ ለማሳጣት ሆን ተብሎ የተቀነባበረ መሆኑን ህዝባችን እንዲረዳና በህዝባዊ እምቢተኝነት ሴራውን ለማክሸፍ መነሳት ጊዜው ግድ የሚል የወቅቱ አንገብጋቢ የትግል ጥሪ መሆኑን ግንቦት 7 የፍትህና የነጻነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ያስገነዝባል።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!!

Friday, January 17, 2014

በትግራይ ክልል የአፅቢ ወንበርታ የተነሳው ህዝባዊ ዓመፅ ቆመ፤ መንግስት ካሳ ሊከፍል ነው

ህዝብ ተበትኗል፣ መንግስት ካሳ ይከፍላል፣ የታሰሩ አይፈቱም
አብርሃ ደስታ

የአፅቢ ወንበርታ ወረዳ (ጣብያ ሩባፈለግ፣ ቁሸት ሕኖይቶ) ህዝብ የከፈተው ዓመፅ ዛሬ (ዓርብ 09/05/06 ዓም ከምሽቱ አስራ ሁለት ሰዓት ከአስር ደቂቃ (12:10) ላይ ቆሟል። ህዝብ ወደየቤቱ ተመልሷል። የፀጥታ ሃይሎች ግን ከአከባቢው አልራቁም።
አስተዳዳሪዎች ህዝቡን በፌደራል ፖሊስ አስከብበው ሲያስፈራሩት የዋሉ ሲሆን የህዝቡን ጥያቄ (ካሳ የመክፈሉ ጉዳይ) ለመመለስ ተስማምተዋል። ስለዚህ ህዝቡ በጠየቀው መሰረት መንግስት ተገቢውን ካሳ ይከፍላል። የታሰሩት የአከባቢው ኗሪዎች ግን አይፈቱም። ህዝቡ “የታሰሩትን ይፈቱልን” ብሎ ሲጠይቅ “እርምጃ እንወስድባችኋለን፣ ማንም መጥቶ አያድናችሁም” የሚል ማስፈራርያ ደርሷቸዋል። ስለዚህ መንግስት ጥያቄ በማንሳታቸው ምክንያት የታሰሩትን ዜጎች ለመልቀቅ ዝግጁ አይደለም።
የመንግስት አካላት ህዝቡን ካሳ ለመክፈል ሲስማሙ የህዝቡን ጥያቄ ትክክለኛነት ተቀብለውና አምነው እንደሆነ አቅርበዋል። ጥያቄው ያነሱት ዜጎች ከእስር ለመፍታት ግን ፍቃደኛ አይደሉም። በትግራይ ዜጎች መብታቸው ሲጠይቁ ለእስር ይዳረጋሉ። የአፅቢ ወንበርታ ጠያቂዎች ምሳሌ ናቸው። ታሳሪዎች የዛሬን ጨምሮ ስምንት ናቸው።
ጥያቄ የጠየቀ ዜጋ ለምን ይታሰራል? ጥያቄ የመጠየቅ መብት የለውም? መንግስት የህዝብን ጥያቄ በአግባቡ ከመመለስ ይልቅ ለምን ወደ ሃይል እርምጃ ይሄዳል? አምባገነኖች በራስ የመተማመን ባህሪ ስለሌላቸው ለሁሉም ሃይል መጠቀም ይወዳሉ።
ምንጭ ዘ-ሐበሻ

Thursday, January 16, 2014

የኢትዮጵያን ታሪክ ጥላሸት የመቀባት አባዜ

ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም
ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ
በአሁኑ ጊዜ በኢትዮጵያ ያለው ገዥው አካል በ19ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የኢትዮጵያ ንጉስ የነበሩት የዳግማዊ አጼ ምኒልክ መቶኛ የሙት ዓመት በዚህ በያዝነው ዓመት (በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር) እየተከበረ ባለበት ወቅት ሙሉ ጊዜውን በመስጠት ንጉሱ የሰሩትን ታላቅ ስራ ሁሉ በማጣጣል እና ጥላሸት በመቀባት ዘመቻ ላይ በመጠመድ ታሪክ የማጠልሸት ድራማውን በመተወን ላይ ይገኛል፡፡ የታሪክ ማጠልሸት ዘመቻው በዋናነት እየተከናወነ ያለው ለገዥው አካል ቅርበት ባላቸው ታማኝ ሎሌዎች፣ የጥቅም ተጋሪዎች እና የእራሳቸው ስብዕና በሌላቸው አሻንጉሊቶች አማካይነት ነው፡፡ ገዥው አካል ሲያስነጥሰው መሃረብ ይዘው በሚቀርቡ አጎብዳጆቹ አማካይነት የጥላቻ መርዛማ ቃላትን፣ የሚቆጠቁጡ ባዶ ዲስኮሮችን እና እርባናየለሽ ምዕናባዊ ስዕል በአዕምሮው ላይ እየፈጠረ አጼ ምኒልክ የግዛት ማስፋፋት ጥማታቸውን ለማርካት ሲሉ በዜጎች ላይ የጭካኔ ተግባራትን እንደፈጸሙ በማስመሰል ለምንም የማይጠቅሙ እርባናየለሽ እና ተራ አሉባልታዎችን በማሰራጨት ላይ ይገኛል፡፡
የገዥው አካል ድንጉላ አገልጋዮች በማናቸውም የማህበራዊ መገናኛ ዘዴዎች በመሰማራት ታሪካዊ ቅጥፈቶችን፣ አሳሳች ዘገባዎችን፣ የሀሰት ታሪክ ፈጠራዎችን፣ ሆን ተብሎ በሀሰት ላይ የተመሰረቱ መረጃዎችን እና ነጭ ውሸቶችን እንደ በቀቀን እየደጋገሙ በማሰራጨት ላይ ይገኛሉ፡፡ የዕኩይ ዓላማው አራማጆች በታላቁ የኢትዮጵያ መሪ ላይ ግነታዊ ኩምክና በመስራት፣ በማዋረድ እና እውነተኛውን ስብዕናቸውን ጥላሸት በመቀባት የስሜት ፕሮፓጋንዳ ዘመቻ ውስጥ በመዘፈቅ ጌቶቻቸውን ለማስደሰት በታለመ ዕኩይ ምግባር ላይ ተጠምደው ይገኛሉ፡፡ የታላቁ መሪ ነብስ ከስጋቸው ከተለየች ከአንድ መቶ ዓመታት የጊዜ ቆይታ በኋላ የተቀበረን ጉዳይ በማንሳት ታላቁን መሪ ሰይጣናዊ ስብዕና እንደነበራቸው ለማስመሰል በማሰብ የዕኩይ ምግባር ጎተራዎቹ የቻሉትን ያህል ጥረት ለማድረግ ሞክረዋል፡፡ አቶ መለስ ዜናዊ በህይወት ከተለዩ ሁለት ዓመታት እንኳን ሳይሞላቸው የዕኩይ ምግባራት ቋቶቹ የኢትዮጵያ አዳኝ መልዓክ ሊያደርጓቸው ይፈልጋሉ፡፡
በአሁኑ ጊዜ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ላይ በተከፈተው የገፍ ወይም የኃይል የፕሮፓጋንዳ ዘመቻ ወይም ደግሞ የአጼ ምኒልክን የሙት መንፈስ ደጋግመው በማንሳት ፍጹም ጥላቻ እና የጥላቻ አመለካከት እንዲንሰራፋ በገዥው አካል ስልታዊ እና የተቀነባበረ ዘመቻ የማካሄድ አመክንዮ ለማንም ቢሆን ሊደንቅ አይገባም፡፡ ሀቁ አንድ እና አንድ ብቻ ነው፡፡ የኸውም የምኒልክን ስም ጥላሸት በመቀባት (ሰይጣናዊ ስብዕና በመስጠት) በሚሽከረከር ጉዳይ ላይ ብቻ የሚቆም ጉዳይ አይደለም፡፡ ነገር ግን በቅርቡ በህይወት የተለዩትን የገዥውን አካል የአለቆች ሁሉ አለቃ (Capo di tutti capi) አቶ መለስ ዜናዊን በመላዕክነት ቀብቶ ለማቅረብ የታቀደ ዕኩይ ምግባር ነው፡፡
ዳግማዊ ምኒልክን ጥላሸት የሚቀቡ ሙትመንፈሶች፣ 
በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ላይ እየተካሄደ ያለው ከፍተኛ ጥላሸት የመቀባት የፕሮፓጋንዳ ዘመቻ ያነጣጠረው የኢትዮጵያን ታሪክ በመፋቅ በአቶ መለስ ዜናዊ የመላዕክነት የህይወት ታሪክ (የመላዕክነት ትረካ) በመተካት የታላቋን ሀገር ትክክለኛ ታሪክ እንደገና ለመጻፍ፣ አዛብቶ ለመጻፍ፣ ገልብጦ ለመጻፍ፣ አወዛግቦ ለመጻፍ፣ በመቀባባት የሚያምር አስመስሎ ለማቅረብ እና እውነተኛውን ታሪክ ለማስወገድ በመደረግ ላይ ያለ ከንቱ ሙከራ ነው፡፡ የአጼ ምኒልክን ታሪክ በመሰረዝ የዘመናችን የ”አፍሪካ ታላቁ መሪ” በማለት የመለስ ዜናዊን ታሪክ ለመጻፍ ይፈልጋሉ፡፡ በሀሰት እምነት ላይ በመመስረት መለስ “አዲሱ የአፍሪካ መሪ ዝርያ“፣ መለስ “የዴሞክራሲያዊ ልማታዊ መንግስት ቀያሽ”፣ መለስ “በዓለም አቀፋዊ የሙቀት እና የአየር ጸባይ ለውጥ የአፍሪካ ጠበቃ”፣ መለስ “ከጂ-8 እና ጂ-20 መሪዎች ጋር በመሆን ክርናቸውን የሚያሳዩ አፍሪካዊ መሪ”፣ መለስ “የቻይና-አፍሪካ የትብብር መድረክ የቤጂንግ ከፍተኛ ዲፕሎማሲያዊ ጉባኤ ሊቀመንበር”፣ መለስ የሶማሌ ጅሃዲስቶች እና አሸባሪዎች አስወጋጅ”… ተብለው ከእውነተኛ ስብዕናቸው ውጭ በሆነ መልኩ እንዲመለክባቸው ይፍልጋሉ፡፡
የታላቁን መሪ የዳግማዊ ምኒልክን ስብዕና ጥላሸት በመቀባት አቶ መለስን ቅብዓ መልዓክ (የተቀባ መልዓክ) ለማድረግ ይፈልጋሉ፡፡ ለመሆኑ አጼ ምኒልክን ጥላሸት የሚቀቧቸው ለምንድን ነው? ምክንያቱም አጼ ምኒልክ በአመራር ጥበባቸው እና በትግላቸው ግጭትን በመፍጠር ሲናቆሩ ከነበሩት ባላባቶች፣ ለስልጣን ብቻ ከሚቋምጡ ከተለያዩ አካባቢያዊ ንጉሶች፣ ከተለያዩ ልዕልቶች የቅምጥል የአገዛዝ ስርዓት፣ እና ከጎጣዊ ምስለኔዎች የተበታተነ አገዛዝ በማላቀቅ ዘመናዊቷን የአፍሪካ ብሄር ታላቋን ኢትዮጵያን በመመስረታቸው ብቻ ነው፡፡ የዕኩይ ምግባር አራማጆች አጼ ምኒልክን ጥላሸት ይቀቧቸዋል፣ ምክንያቱም ምኒልክ ታላቆቹን የአውሮፓ ኢምፔሪያሊስት ኃያላን በጦር ሜዳ ውሎ በማሸነፍ አንጸባራቂ ድል በመቀዳጀት የኢትዮጵያን ዘለቄታዊ ነጻነት ያጎናጸፉ እና የሀገሪቱን ሉዓላዊነት ያስከበሩ ጀግና መሪ በመሆናቸው ነው፡፡ ጥላሸት ይቀቧቸዋል ምክንያቱም ምኒልክ እውነተኛ የአፍሪካ መሪ በመሆናቸው ነው፡፡ የአጼ ምኒልክን ስም በማጥፋት እና ለኢትዮጵያ ህዝብ ያበረከቱትን የውርስ ትሩፋታቸውን በማንቋሸሽ ለአቶ መለስ ክብር ለመስጠት እና ከእርሳቸው የሚገኘውን ውርስ ብጹዕ/ቅዱስ ለማድረግ ይፈልጋሉ፡፡
ገዥው አካል የአጼ ምኒልክን ታሪክ በእራሱ ታሪክ ለመተካት ይፈልጋል፡፡ አጼ ምኒልክ የባቡር ሀዲድ በመዘርጋት የመጀመሪያው አፍሪካዊ መሪ ነበሩ፡፡ ይህንን አንጸባራቂ ታሪክ በመለወጥ አቶ መለስ ረዥም፣ ቆንጆ እና ቀላል የባቡር ሀዲድ ሲስተም በኢትዮጵያ ለማምጣት የመጀመሪያው መሪ ነበሩ በማለት የታሪክ ባለቤትነት ሽሚያን ለማጎናጸፍ ይፈልጋሉ፡፡ አጼ ምኒልክ የስልክ እና የቴሌግራፍ አገልግሎትን በአፍሪካ አህጉር በማስተዋወቅ የመጀመሪያው አፍሪካዊ መሪ ነበሩ፡፡ እ.ኤ.አ በ1889 አሌክሳንደር ግራህም ቤል “የድምጽ መነጋገሪያ መሳሪያ” የፓተንት ዕውቅና ካገኙበት 13 ዓመታት በኋላ እና በአጼ ምኒልክ ቤተመንግስት የመጀመሪያው የስልክ መስመር በተዘረጋበት ጊዜ በቴክኖሎጂው ሁኔታ ጭንቀት ውስጥ ገብተው የነበሩት የቤተክህነት ሰዎች ይህ የሰይጣን ስራ ነው በማለት ንጉሱ እንዲያስወግዱት በጠየቋቸው ጊዜ አጼ ምኒልክ ለቴክኖሎጂው ጠቀሜታ ካላቸው ጽኑ እምነት አኳያ ሳያስወግዱት ቀርተዋል፡፡ በአስርት ዓመታት ጊዜ ውስጥ አጼ ምኒልክ አዲስ አበባን በምስራቅ ኢትዮጵያ ከምትገኘው የሀረር ከተማ ጋር የሚያገናኝ የስልክ መስመር በመዘርጋት መርቀው ከፈቱ፡፡ ያንን አንጸባራቂ ታሪክ ወደ ጎን በማለት የአሁኖቹ ገዥዎች በኢትዮጵያ ዘመናዊ የመገናኛ ቴክኖሎጂ ሲስተምን በኢትዮጵያ ያመጡ አቶ መለስ ዜናዊ እንደሆኑ አድርገው ያቀርባሉ፡፡ እውነታው ግን በተገላቢጦሽ  በአፍሪካ የስልክ እና የቴሌግራፍ መስመር በመዘርጋት ግንባርቀደም የነበረችው ኢትዮጵያ በአሁኑ ጊዜ ከአፍሪካ በመጥፎ የተንቀሳቃሽ ስልክ እና የኢንተርኔት አግልግሎት አጠቃቀም ሳቢያ በመጨረሻው እረድፍ ላይ ትገኛለች፡፡ ባለፈው ሳምንት የዎል ስትሪት መጽሄት/Wall Street Journal እንደዘገበው በኢትዮጵያ ውስጥ አርሶ አደሮች የተንቀሳቃሽ ስልኮች ቢይዙም “ችግሩ የግንኙነት መስመር ለማግኘት ብዙ ማይሎችን (ኪሎሜትሮችን)መጓዝ ይጠበቅባቸዋል፡፡“ በማለት የችግሩን አሳሳቢነት አመላክቷል፡፡ ኢትዮጵያ በመጥፎ የኢንተርኔት አገልግሎት አጠቃቀም ከአፍሪካ ከመጨረሻዎቹ ሀገሮች በሁለተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡
የዘመኑ ገዥዎቻችን አጼ ምኒልክ የሴቶችን ጡት ቆርጠው የሚጥሉ ጨካኝ ንጉስ እንደሆኑ አድርገው ታሪክን አዛብተው ለመጻፍ ይፈልጋሉ፡፡ ጨካኝነት ከተነሳ ዘንድ ከአቶ መለስ ዜናዊ የበለጠ ጨካኝ እና አረመኔ ይኖራልን? አቶ መለስ እራሳቸው እ.ኤ.አ በ2005 በተደረገው ሀገራዊ ምርጫ መጭበርበር ምክንያት ተቃውሟቸውን ለመግለጽ በወጡ ያልታጠቁ ሰላማዊ ዜጎች ላይ ለአነጣጥሮ ተኳሽ ጦራቸው ትዕዛዝ በመስጠት በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች እንዲገደሉ አድርገዋል፡፡ ይህንን እልቂት አስመልክቶ በእራሳቸው በአቶ መለስ ልዩ ትዕዛዝ ጉዳዩን እንዲያጣራ የተሰየመው የአጣሪ ኮሚሽን ምርመራውን አካሂዶ ባቀረበው ዘገባ መሰረት በአቶ መለስ ቀጥታ ትዕዛዝ እና ቁጥጥር አማካይነት የፖሊስ እና የደህንነት ኃይሎች በዕቅድ ተይዞ እና ሆን ተብሎ ታስቦበት 193 ሰላማዊ ሰዎች እንዲገደሉ እና ሌሎች 763 ሰዎች ደግሞ ከባድ ቁስለኛ እንዲሆኑ ተደርጓል፡፡ እ.ኤ.አ በ2004 አቶ መለስ እራሳቸው ለታጣቂዎቻቸው ትዕዛዝ በመስጠት በምዕራብ ኢትዮጵያ በጋምቤላ 400 ሰላማዊ ዜጎች እንዲያልቁ አድርገዋል፡፡ ኦጋዴን እየተባለ በሚጠራው አካባቢ የተካሄደውን የአየር ድብደባ እና መንደሮችን በማቃጠል የጥቃት ሰለባ ያደረገው ወንጀል  የተፈጸመው በአቶ መለስ ስልጣን ልዩ ትዕዛዝ ነበር፡፡ በአቶ መለስ ትዕዛዝ በኦጋዴን ታጣቂ ኃይሎች ሴቶችን አስገድደው ደፍረዋል፣ መንደሮችን አቃጥለዋል፣ ህዝቡን በሽብር ቆፍን ውስጥ ለመሸበብ ሲባል “የመቀጣጫ ግድያዎችን” ማለትም በህዝብ ፊት በአደባባይ በስቅላት እንዲሁም ጭንቅላትን ቆርጦ የመጣል ወንጀሎች እንዲፈጸሙ ተደርጓል፡፡ የተባበሩት መንግስታት የሂዩማን ራይትስ ዎች ተሟጋች ዳይሬክተር/United Nations Advocacy Director for Human Rights Watch ስቴቭ ክራውሻው በኦጋዴን አካባቢ  በሰላማዊ ዜጎች ላይ የተፈጸመውን ወንጀል “ትንሿ ዳርፉር” በማለት አመሳስለው ገልጸውታል፡፡
ገዥዎቻችን አጼ ምኒልክን የኦሮሞ ህዝቦች ጠላት እንደሆኑ አድርገው ታሪክን በመበረዝ የታሪክ ድሪቶ አቀነባብረው እንደገና የጎደፈ ታሪክ ለመጻፍ ይታትራሉ፡፡ አቶ መለስ በህይወት ቢኖሩ ኖሮ እሳቸው እና የዕኩይ ምግባር አጋሮቻቸው በኦሮሞ ህዝብ ላይ እስከ አሁን ድረስ ያልተነገረውን እና ለመናገር የሚዘገንነውን በሰው ልጆች ላይ የፈጸሙትን ወንጀል ወደ ፍትህ አደባባይ በማቅረብ እንዲታይ ለማድረግ ከበቂ በላይ መረጃዎች አሉ፡፡ እ.ኤ.አ በ2012 ፍሪደም ሀውስ/Freedom House የተባለው ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅት ባቀረበው ዘገባ መሰረት አቶ መለስ እና አገዛዛቸው በኦሮሞ ህዝብ ላይ ሰፊ የሆነ የአድልኦ እና የጭቆና መረብ በመዘርጋት ተግባራት ላይ ተጠምደው ቆይተዋል፡፡ አቶ መለስ የኦሮሞ ነጻነት ግንባርን እንቅስቃሴ በመገደብ ብዛት ያላቸው ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ የሚጠረጠሩ የድርጅቱን አባላት እና መሪዎችን ከህግ አግባብ ውጭ በቁጥጥር ስር በማዋል በማጎሪያ እስርቤት አስገብተው ሲያሰቃዩ ቆይተዋል፣ አሁንም በመሰቃየት ላይ ይገኛሉ፡፡ እ.ኤ.አ በ2001 የቀድሞው የኢትዮጵያ ፕሬዚዳንት የነበሩት ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ስልጣናቸውን ሲለቁ እንደተናገሩት “ወደ 25,000 የሚሆኑ የኦሮሞ ህዝቦች ከኦሮሞ ህዝቦች ነጻነት ግንባር ጋር በተያያዘ የገዥው አካል ክስ ምክንያት በተለያዩ የኦሮሚያ አካባቢዎች እና በአዲስ አበባ ከተማ እስር ቤቶች ታስረው በመማቀቅ ላይ ነበሩ፡፡” በማለት ይፋ አድርገዋል፡፡ የመለስ የትግል ጓድ እና የቀድሞው የመከላከያ ሚኒስትር የነበሩት አቶ ስዬ አብርሃ በሚያስገርም ሁኔታ እንደተመለከቱት “ቃሊቲ እስር ቤት ኦሮምኛ ይናገራል፣ በዚሁ ግቢ በአንድ በመቶዎች የሚቆጠሩ እስረኞችን በሚይዝ ካምፕ ውስጥ 99 በመቶ የሚሆኑት እስረኞች ኦሮሞዎች ናቸው፡፡ አብዛኞቹ እስረኞች ደግሞ የታሰሩበት ምክንያት ምን እንደሆነ አያውቁም፣ ሆኖም ግን የኦሮሞ ነጻነት ግንባር ተጠርጣሪ በመባል ዓመታትን በእስር ቤት በማስቆጠር ላይ ይገኛሉ፡፡“ በማለት ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል፡፡
እ.ኤ.አ በ2006 ጂሃዲስቶች (አሸባሪዎች) የሶማሌን አገር ወረዋታል እና የሶማሌ መንግስት ጣልቃ ገብቸ ጂሃዲስቶችን እንዳስወጣለት “ጋብዞኛል” በሚል ተንኮልን ያዘለ ሰበብ ምክንያት አቶ መለስ በሶማሌ አገር ላይ ወረራ አካሂደዋል፡፡ አቶ መለስ በቴሌቪዥን ቀርበው እንዲህ ብለዋል፣ “የአገራችንን ሉዓዋላዊነት ለማስከበር እና በእስልምና ፍርድ ቤቶች ህብረት እና በሌሎች ጸረ ኢትዮጵያ ኃይሎች በመታገዝ የሚያደርሷቸውን ተደጋጋሚ አደጋዎች ለመግታት ሲባል የኢትዮጵያ የመከላከያ ሰራዊት ወዳልፈለገው ጦርነት እንዲገባ ተገድዷል፡፡“ በተመሳሳይ መልኩ በዴሴምበር 27 2006 የአቶ መለስ ሰራዊት እና ታንኮች የሞቃዲሾን ከተማ ወረሩ፡፡ እ.ኤ.አ በኦገስት 2007 የአቶ መለስ ሰራዊት በሶማሌ ውስጥ የሚያደርገው እንቅስቃሴ ተገታ፣ በሰው ህይወት ላይ የደረሰው ኪሳራ አስደንጋጭ ነበር፡፡ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ንጹሃን የሶማሌ ዜጎች ህይወት የተቀጠፈ ሲሆን ከ870,000 በላይ የሚሆኑት ዜጎች ደግሞ ሞቃዲሾን ለቀው ለመሰደድ ተገደዋል፡፡ በ2006 በሞቃዲሾ ከተማ ወደ 1.2 ሚሊዮን ገደማ የሚሆን ህዝብ ነበር፡፡ ከአቶ መለስ የሶማሌ ወረራ በኋላ ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች “ከአፍሪካ በጣም አስቀያሚ አስከፊ የሰብአዊ መብት ሁኔታ ያለበት“ በማለት የሶማሌን የሰብአዊ መብት አያያዝ በተጨባጭ ገልጸውታል፡፡
አጼ ምኒልክ ከአውሮፓውያን ወራሪ ኃይሎች ጋር የመከላከል ጦርነትን በማካሄድ በድል አድራጊነት ተወጥተዋል፡፡ አጼ ሚኒልክ የአውሮፓ ኃያል ከሚባል አገር ጋር ጦርነት በማድረግ በጦር ሜዳ ድል አድርገው ወራሪው ኃይል በመጣበት እግሩ ጓዙን ጠቅልሎ እንደ ውሻ ጅራቱን በእግሮቹ መካከል ወትፎ እንዲመለስ በማድረግ በአፍሪካ ታሪክ የመጀመሪያው መሪ መሆናቸው የሚካድ ጉዳይ አይደለም፡፡ አጼ ምኒልክ ወራሪውን የኢጣልያንን ጦር አምባላጌ እና መቀሌ ላይ ድል አድርገዋል፡፡ እንዲሁም እ.ኤ.አ በ1896 አድዋ ላይ ወሳኙን ፍልሚያ በማድረግ የአድዋን ጦርነት በድል አድራጊነት ተወጥተዋል፡፡ “ኋላቀር አፍሪካውያን ጥቁሮች” ወታደሮች  ኃያሉን የአውሮፓ ኢምፔሪያሊስት የጦር ኃይል ያሸንፋል የሚል እምነት በማንም አውሮፓዊ የተገመተ አልነበረም፡፡ አጼ ምኒልክ በዘመናዊ መሳሪያ ትጥቅ፣ በስልት እና በቁሳቁስ አቅርቦት በዘመኑ በጣም የተጎዱ መሪ ቢሆኑም ቅሉ የብሩህ አዕምሮ ባለቤት እና ወታደራዊ ስልት የሚያውቁ በመሆናቸው ውጊያውን በማካሄድ ጦርነቱን አሸንፈው በአንጸባራቂ ድል በመታጀብ የነጮችን የበላይነት እና አይበገሬነት ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ በማስወገድ ለጥቁር ህዝቦች በአጠቃላይ ለአፍሪካውያን ደግሞ በተለይ የኩራት ፈርጥ ለመሆን በቅተዋል፡፡ ብዙ የአውሮፓ ኃያላን አገሮች አጼ ምኒልክን በማታለል እና በማጭበርበር ከኢትዮጵያ ግዛት ቆርሰው በመውሰድ ኢትዮጵያን ቅኝ ተገዥ ለማድረግ ከፍተኛ ጥረት አድርገዋል፡፡ እ.ኤ.አ በ1889 አጼ ምኒልክ  በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል የሚገኙ ግዛቶችን አስመልክቶ ከኢጣሊያ መንግስት ጋር የውጫሌ ስምምነትን አጸደቁ፡፡ በውል ስምምነት ሰነዱ የኢጣሊያንኛው ትርጉም ከኢትዮጵያ የአማርኛ ትርጉም ጋር የማይመሳሰል መሆኑን አጼ ምኒልክ እንደተገነዘቡ እና ኢትዮጵያ በኢጣሊያን ጠባቂነት የሚለውን ሀረግ ሲመለከቱ የውል ስምምነቱን በማውገዝ አፈረሱት፡፡
የገዥው አካል አፈቀላጤዎች አቶ መለስ ኢትዮጵያ የአህጉሩ ታላቅ አገር እንድትሆን ጥረት ያደረጉ እና የአህጉራዊ እና ዓለም አቀፋዊ መሪ እንደሆኑ በማድነቅ እና ስብዕናቸውን ከፍ ከፍ በማድረግ የአሁኑን የኢትዮጵያ ታሪክ ደልዘው በእርሳቸው ተተክቶ እንዲጻፍ ነው በመዋተት ላይ የሚገኙት፡፡ አቶ መለስ የኢትዮጵያን የግዛት አንድነት እና ሉዓላዊነት ያስከበሩ መሪ እንደሆኑ አድርገው ለማሳየት ይፈልጋሉ፡፡ እውነታው ግን የተገላቢጦሹን ያመላክታል፡፡ እ.ኤ.አ ከ1998-1999 ድረስ የባድሜን የግዛት ወሰን ለማስከበር በተካሄደው የኢትዮጵያ እና የኤርትራ ጦርነት የአቶ መለስ ጦር የ80,000 ኢትዮጵያውያንን ህይወት ያለምንም ወታደራዊ ስልት በጭዳነት ለመስዋዕትነት ዳርጎ ወታደራዊ ድልን ተቀዳጅቶ ነበር፡፡ በወገኖቻችን የህይወት እና ንብረት መስዋዕትነት የተገኘውን ድል ሰራዊቱ ገና አጣጥሞ ሳይጠግብ የኢትዮጵያው መሪ አቶ መለስ ከመቅጽበት በመገለባበጥ ባድሜን በዓለም አቀፋዊ የስምምነት ውል በማስቀየድ ለኤርትራ መንግስት ቡራኬ ብለዋል፡፡ በምንም ዓይነት መልኩ በየትኛውም አገር አንድ ወታደራዊ ኃይል እጅግ ከባድ መስዋዕትነትን ከፍሎ ያገኘውን አንጸባራቂ ድል ለተሸናፊው ጠላቱ በፈቃደኝነት መልሶ የሰጠበት የጦርነት ታሪክ የለም፣ ተመዝግቦም አያውቅም፡፡ እ.ኤ.አ በ1991 ወታደራዊውን አምባገነን ደርግን በትጥቅ ትግል ካስወገዱ በኋላ በአሜሪካ መንግስት አደራዳሪነት የሽግግር ስምምነቱ በሚፈረምበት ወቅት እኒሁ የኢትዮጵያው መሪ አቶ መለስ በኤርትራ የወሰን ግዛት ዳርቻ ላይ የምትገኘውን ከቀይ ባህር ጋር በመግቢያ እና በመውጫነት ለኢትዮጵያ ህዝብ የባህር በር በመሆን አገልግሎት የምትሰጠውን የአሰብን ወደብ ወደ ኢትዮጵያ ግዛት እንድትካለል የቀረበውን ሀሳብ አልቀበልም በማለት አሁንም በድጋሜ ለኤርትራ መንግስት ቡራኬ በመስጠት ይደልዎ ብለዋል፡፡ አቶ መለስ የኢትዮጵያን ግዛት ለባዕድ ኃይል በመስጠት ታላቋን አገር ወደብአልባ በማድረግ በፈጸሙት የአገር ክህደት ወንጀል ብቸኛው ተጠያቂ ናቸው፡፡ አሁንም ተከታታይነት ያለውን የትራጄዲ ድራማ በመቀጠል በሚስጥር በተደረጉ ስምምነቶች የይስሙላው ፓርላማ ለስሙ እንኳ መከረበት ሳይባል ምንም ሳይታሰብበት በጥድፊያ እኒሁ የኢትዮጵያው “መሪ” አሁንም የኢትዮጵያ አንጡራ ግዛት የሆነውን መሬት ለሱዳን መንግስት እንደ የገና ስጦታ የእጅ መንሻ ቡራኬ አድርገውታል፡፡ እኒሁ የኢትዮጵያው መሪ አቶ መለስ በድብቅ እና ታማኝነት በጎደለው መልኩ የአገሪቱን እጅግ በጣም ለም የሆነውን በሚሊዮኖች ሄክታር የሚቆጠር መሬት ዕዳቸውን እንኳ ውል ባለው መልክ ለመክፈል ለማይችሉ የአየር ባየር ጭልፊት ነጋዴዎች አሁንም ለእጅ መንሻ አቅርበዋል፡፡
አጼ ምኒልክ የኢትዮጵያን አንድነት በማጠናከር ዘመናዊ የመንግስት መዋቅር ዘርግተዋል፡፡ አቶ መለስ ግን ምዕናባዊ ዘመናዊነትን አምጥተዋል፡፡ አቶ መለስ ያለሐኪሞች እና መድኃኒት ሆስፒታል ገንብተዋል፡፡ በአንድ ወቅት ሐኪሞች አያስፈልጉንም በማለት በይፋ ተናግረዋል፡፡ ብቃት ያላቸው የዩኒቭርስቲ መምህራን እና ፕሮፌሰሮች፣ መጻህፍት፣ ቤተ መጻህፍት፣ ወይም ዘመናዊ ቴክኖሎጂ ሳይኖር ዩኒቨርስቲዎችን ገንብተዋል፡፡ የመጸዳጃ ሲስተም የሌላቸውን ህንጻዎች ገንብተዋል፡፡ አጼ ምኒልክ ኢትዮጵያን የምዕራቡ ዓለም ስልጣኔ ትሩፋት ተቋዳሽ እንድትሆን አድርገዋል፡፡ አቶ መለስ “ልማታዊ መንግስት” የሚል እርባናየለሽ ህልዮት ከምስራቅ ኢስያ ሀገራት አምባገነኖች ኮርጀው በማምጣት ኢትዮጵያን ወደ ኋላ መልሰዋታል፡፡ እ.ኤ.አ በ1991 ስልጣን ከያዙ በኋላ አቶ መለስ ዘመናዊውን የኢትዮጵያ መንግስት አወቃቀር በማፈራረስ ወዲያውኑ አገሪቱን ክልል እየተባለ በሚጠራው ወይም የአፓርታይድ አይነት ባንቱስታንስ ወይም ክልሊስታንስ የተባለ የመከፋፈል ተልዕኮውን አጠናቀቀ፡፡ አቶ መለስ በሀሰት ላይ በመመስረት ባለሁለት አሀዝ የኢኮኖሚ ዕድገት አስመዝግበናል፣ እና “ኢትዮጵያ ነዳጅ ወደ ውጭ ከማይልኩ የሰብ ሰሀራ አፍሪካ አገሮች መካከል ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት የምታስመዘግብ አገር ናት” በማለት በሸፍጥ ለማሳመን በመወትወት ላይ ይገኛሉ፡፡ እውነታው ግን ኢትዮጵያ በዓለም ከሚገኙ የመጨረሻዎቹ ደኃ አገሮች ከመጨረሻው በሁለተኛ ደረጃ ላይ የምትገኝ አገር መሆኗን “ኢትዮጵያ ለምንድን ነው ደኃ የሆነችው?” በማለት ቀደም ሲል ባዘጋጀሁት ትችቴ ላይ በግልጽ አስቀምጨዋለሁ፡፡
አጼ ምኒልክ የኢትዮጵያ “ህዳሴ” መሪ ነበሩ፡፡ አገራቸውን ለማጠናከር እና ዘመናዊ ለማድረግ ወሳኝ የሚባሉ እርምጃዎችን ወስደዋል፡፡ ለዘመናዊ ቴክኖሎጂ ልዩ ትኩረት በመስጠት ለአገራቸው አዲስ ዓይነት የግንኙነት ስርዓት እንዲዘረጋ  አድርገዋል፡፡ አጼ ምኒልክ አገራቸው ኢትዮጵያ የስልክ እና የቴሌግራፍ እንዲሁም ዘመናዊ የፖስታ አገልግሎት ተጠቃሚ እንደትሆን አድርገዋል፡፡ አጼ ምኒልክ የኤሌክትሪክ አገልግሎት በአዲስ አበባ ከተማ እንዲጀመር አድርገዋል፡፡ የመጀመሪያዋን በሞተር ኃይል የምትንቀሳቀስ አውቶሞቢል ወደ ሀገራቸው ያስገቡ አጼ ምኒልክ ናቸው፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የማሪያ ቴሬዛ ገንዘብን የማይመች የገንዘብ መገበያያን በዚያን ዘመን በዓለም ገበያ ላይ በመገበያያነት አገልግሎት ስራ ላይ ይውሉ በነበሩ በመዳብ የወርቅ ቁራጭ የገንዘብ ሳንቲሞች በመተካት ዘመናዊ የገንዘብ ግብይትን በኢትዮጵያ አስጀምረዋል፡፡ አጼ ምኒልክ ከምንም ከማንም በላይ የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት ቅድሚያ ይሰጡ ነበር፡፡ አጼ ምኒልክ እ.ኤ.አ በ1894 ከጅቡቲ እስከ አዲስ አበባ የሚዘልቅ የባቡ ሀዲድ መስመር ለመዘርጋት ከፈረንሳይ መንግስት ጋር የስምምነት ውል ፈረሙ፡፡ በተመሳሳይ ዓመት የአውሮፓ ኃያላን አገሮች አፍሪካን እንደ ቅርጫ ስጋ የሚከፋፍለውን የአውሮፓ ቅኝገዥዎች የበርሊን ጉባኤን  አካሄዱ፡፡ በዚያን ጊዜ ፈረንሳዮች የነበራቸውን ኃይል በመተማመን ከባቡር ሀዲዱ ጋር በተያያዘ መልኩ የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት ለመዳፈር ሲሞክሩ አገር ወዳዱ መሪ ፈረንሳዮችን ጭጭ እንዲሉ አድርገው በ1906 የአገራቸውን ሉዓላዊነት ካስጠበቁ በኋላ ነው ቀዝቀዝ ማለት የጀመሩት ሐዲዱም መሰራት የቀጠለው ፡፡ እንግዲህ እንዲህ የነበረውን አንጸባራቂ ታሪክ በአሁኑ ጊዜ በኢትዮጵያ ያለው ገዥው አካል የውሸት የአቶ መለስን ትረካ በማጉላት የህዳሴው መሪ፣ በአፍሪካ ታሪክ እስከ አሁን ድረስ ታይቶ የማይታወቅ የኤሌክትሪክ ኃይል ግድብ ገንቢ፣ የድልድዮች ገንቢ፣ የመንገዶች እና የባቡር ሀዲዶች…  በማለት ታሪክን አዛብቶ ሸውራራ ታሪክ ለመጻፍ እየተውተረተረነው ያለው፡፡
አጼ ምኒልክ የፊውዳል መንግስታት የበላይ የነበሩ መሪ ነበሩ፡፡ በወቅቱ በአገር ውስጥ እና በዓለም አቀፍ ደረጃ በጣም አስቸጋሪ ሁኔታ በነበረበት ጊዜ ማድረግ የሚፈልጉትን ማድረግ የሚችሉ አፍሪካዊ መሪ ነበሩ፡፡ በእግዚአብሄር በአላህ ፈቃድ አንዲት የተባበረች እና የተከበረች ኢትዮጵያን ለተተኪው ትውልድ አውርሰው አልፈዋል፡፡ የአቶ መለስ ጠንካራው የውርሳቸው ትሩፋት በአፍሪካ የመጀመሪያውን ፈላጭ ቆራጭ አምባገነናዊ አገዛዝ ማውረሳቸው ነው፡፡ በሁፊንግተን ፖስት ትችቴ/Huffington Post Commentary በግልጽ እንዳስቀመጥኩት “ዴሞክራሲ የህዝብ፣ በህዝብ፣ ለህዝብ የቆመ የመንግስት አስተዳደር ከሆነ የማፊያ አገዛዝ/thugocracy ደግሞ (የወሮ በላ) የሌቦች፣ ለሌቦች በሌቦች የቆመ የወሮ በላ መንግስት አስተዳደር ነው፡፡“ በግልጽ አባባል የማፊያ አገዛዝ የሚሽከረከረው በወሮበላ ሌቦች እና በዘራፊዎች ነው፡፡ በማፊያ የአገዛዝ ስርዓት የፖለቲካ ስልጣንን ሙዝዝ ብሎ መያዝ እና እንደ መዥገር መጣበቅ ዋናው ተግባሩ ሲሆን ገዥው አካል የህዝብን ገንዘብ በመዝረፍ እና ለብዙሀኑ ህዝብ ህልውና የቆሙትን መሰረታዊ አገልግሎቶች ውሱን ሀብቶች በመቀራመት ግላዊ ሀብትን ለማጋባስ ነው፡፡
የአቶ መለስ የማፊያ (የወሮ በላ) አገዛዝ በሰነድ ብቻ ተመዝግቦ የሚያዝ ሳይሆን በቀድሞው የመከላከያ የትግል ጓደኛቸው ጭምር የአይን ምስክርነት የተሰጠበት ጉዳይ ነው፡፡ ገና ከጫካ ትግል ሲጀምሩ አቶ መለስ እና የትግል ጓዶቻቸው የሌቦች አስተዳደራዊ ስርዓት ነበር የዘረጉት፡፡ እ.ኤ.አ በ1980ዎቹ የመጀመሪያ ዓመታት ለረሀብ ሰለባ ለወደቀው የትግራይ ህዝብ እርዳታ ተብሎ ከእርዳታ ሰጭ ድርጅቶች የተላከውን ከ10 ሚሊዮን ዶላር በላይ የሚሆን ገንዘብ ከተሰጠበት ዓላማ ውጭ አማጺው ቡድን ለጦር መሳሪያ መግዣ እና እራሳቸውን ማበልጸጊያ አድርገውታል፡፡ በቅርብ እየወጡ ያሉ ዘገባዎች እንደሚያመላክቱት ከግማሽ በላይ የሚሆነው የአገሪቱ ኢኮኖሚ በአቶ መለስ ባለስልጣኖች፣ ደጋፊዎች፣ ሎሌዎች፣ ጓደኞች፣ የስራ ባልደረቦች እና ሌሎች ቁጥጥር ስር ተቀፍድዶ ይገኛል፡፡ ሙስናን በሚመለከት የዓለም ባንክ “ሙስናን በኢትዮጵያ መመርመር” በሚል ርዕስ የተወሰኑ አገሮችን ባናሙናነት ወስዶ በማጥናት ባወጣው ባለ500 ገጽ የግኝት ዘገባ መሰረት ሙስና እና የህዝብን ሀብት መዝረፍ በኢትዮጵያ ዋና መገለጫ ሆኗል በማለት ደምድሟል፡፡ ዘራፊነት አና ሙስና የአቶ መለስ የመጨረሻው ውርሳቸው ነው፡፡
አጼ ምኒልክን መጥላት ይወዳሉ፣
ጥላቻ የነብሳችን የመጨረሻው የበሽታ ምልክት ነው፡፡ ጥላቻ ኢምክንያታዊ ነው ወይም አመክንዮ የለውም፡፡ በጥላቻ ላይ የተጻፉ በርካታ ሳይንሳዊ ጽሁፎች እንደሚያመለክቱት  በጥላቻ የተመረዙት ምንጊዜም ይጠላሉ ምክንያቱም ይፈራሉ፣ ደህንነት አይሰማቸውም፣ ምቀኞች ናቸው፣ ወይም ደግሞ እራሳቸውን ይጠላሉ ምክንያቱም የጥላቻቸው መነሻ እና መድረሻ እነዚሁ በጥላቻ የተሞሉት ግብዞች ናቸውና፡፡ ከሁሉም በላይ በጥላቻ የተሞሉት ወገኖች እራሳቸውን ይጠላሉ ምክንያቱም ብቁነት የጎደላቸው፣ ኃይልየለሽነት፣ ተስፋቢስነት፣ እና የእረዳትየለሽነት ስሜት የተጠናወታቸው ነው፡፡
ማንዴላ እንዲህ ብለው ነበር፣ “ሰው በቆዳው ቀለም፣ ወይም ደግሞ በማንነቱ፣ ወይም በኃይማኖቱ ምክንያት ብቻ ማንም ማንንም ሊጠላ አልተወለደም፡፡ ሰዎች መጥላትን መማር አለባቸው፣“ በአሁኑ ጊዜ በኢትዮጵያ በስልጣን ላይ ያሉትን የገዥው አካል ኃላፊዎች ሁኔታ  በማስብበት ጊዜ በማንዴላ ፍልስፍናዊ ግምገማ ላይ አምነት ማጣት ይቃጣኛል፡፡  ማንዴላ እንዲህ በማለትም አክለዋል፣ “መጥላትን የሚማሩ ከሆነ ፍቅርን ሊማሩም ይችላሉ፣ ምክንያቱም ፍቅር ከተቃራኒው የበለጠ በሰው ልጅ ልብ ውስጥ የመስረጽ ተፈጥሯዊ ባህሪ አለውና፡፡“ ተቃራኒውን በተጨባጭ የሚያመላክቱ በርካታ መረጃዎች ቢኖሩም የማንዴላ መርሆዎች በስልጣን ላይ ባሉት ባለስልጣኖች ሁሉ ሊተገበሩ እንደሚችሉ ጽኑ እምነት አለኝ፡፡
በመርህ እና በተግባርም እንደሚታየው በጋንዲ መርሆዎች መሰረት ለመኖር ጥረት ማድረግ አለብን፣ “ኃጢያተኛውን ሳይሆን ኃጢያቱን እንጥላ፣“ በጥላቻ የተመረዙትን የምንጠላ ከሆነ የእነርሱ የመስታወት ነጸብራቅ እንሆናለን፣ እራሳችንም የምንጠላቸውን እንሆናለን፣ እንደ ሰው ስብዕና አቶ መለስን እና መሰሎቻቸውን የምንጠላ ከሆነ እነርሱኑ ሆን ማለት ነው፡፡ የምንጠላ ከሆነ ምግባራቸውን እንጅ እንደ ሰው እራሳቸውን መሆን የለበትም፡፡
ጥላቻ ጠንካራ ኃይል ነው፡፡ በናዚዝስቶች የተሰራጨው ጥላቻ አገሮችን በጠቅላላ እንዲጠፉ አድርጓል፡፡ በሩዋንዳ የተከሰተው ጥላቻ የሚሊዮኖችን ሩዋንዳውያን ህይወት ቀጥፏል፡፡ በዳርፉር የተቆሰቆሰው ጥላቻ በሚሊዮን የሚቆጠሩ የሱዳን ዜጎችን ህይወት አጥፍቷል፡፡ በአሁኑ ጊዜ በተከሰተው የኃይማኖት ጥላቻ በናይጄሪያ እና በመካከለኛው አፍሪካ ሬፑብሊክ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች በመሞት ላይ ይገኛሉ፡፡ በምንም ዓይነት መንገድ ወደ ጥላቻ መግባት የለብንም፡፡
በዓለም ላይ ሁለት ዓይነት ህዝቦች እንዳሉ አምናለሁ፡፡ “ጎረቤትህን እንደ እራስህ ውደድ“ የሚለውን ወርቃማ ህግ የሚከተሉ ህዝቦች አሉ፡፡ ሌሎች ደግሞ “የመዳብ ህግ” እያልኩ በምጠራው “ጎረቤትህን እንደ እራስህ ጥላ“ እያሉ የሚኖሩ ህዝቦች አሉ፡፡ በጥላቻ የተሞሉ ሰዎች የእራሳቸውን እረዳትየለሽነት፣ የደህንነት እጦት ስሜት፣ የጥፋተኝነት ስሜት እና በጥላቻቸው መሳሪያነት ድርጊቶችን በመለወጥ አሸናፊነትን የሚጎናጸፉ ይመስላቸዋል፡፡ ሌሎችን በመጥላት የራሳቸውን የበታችነት ስሜት እና የእራስን ዋጋ ዝቅ አድርጎ የማየት ችግራቸውን በማስወገድ እራሳቸውን ከፍ ያደረጉ ይመስላቸዋል፡፡ አጼ ምኒልክን የሚጠሉ ሰዎች በእርግጥ አይጠሏቸውም፣ እራሳቸውን የሚጠሉ እና ምኒልክን ለመሆን የሚያስቡ ምኒልክ የሚያደርጓቸውን ነገሮች ሁሉ ተምሳሌት ለማድረግ የሚጥሩ ናቸው፡፡
በአሁኑ ጌዜ በኢትዮጵያ በስልጣን ላይ ላሉት ሁሉ አዝንላቸዋለሁ፡፡ በእርግጥ በጣም አዝንላቸዋለሁ፡፡ እነዚህ በጥላቻ የተሞሉት ወገኖች የኢትዮጵያን ታላላቅ መሪዎች እና የኢትዮጵያን ታሪክ ጥላሸት በመቀባት በቅርቡ በህይወት የተለዩትን መሪያቸውን እና የሁለት አስርት ዓመታት ኃጢያታቸውን በማስሰረይ ብጹ የሚያደርጓቸው ይመስላቸዋል፡፡ የአጼ ምኒልክን እና የቀዳማዊ ኃይለስላሴን በጎ ተግባራት ጥላሸት በመቀባት የአቶ መለስን ስብዕና የሚገነቡ ይመስላቸዋል፡፡ የአጼ ምኒልክን ሐውልት ከህዝባዊ ቦታዎች በማራቅ እና የአቶ መለስን እርካሽ ወረቀት ፎቶግራፎች በየመንገዶች ላይ በመለጠፍ አቶ መለስን ወደ መልዓክነት ያቀረቧቸው ይመስላቸዋል፡፡ አቶ መለስ የአጼ ኃይለስላሴ ሀውልት ከንክሩማህ ቀጥሎ በአፍሪካ ህብረት ቅጥር ግቢ ውስጥ እንዳይቆም ሽንጣቸውን ገትረው ተከራክረዋል፡፡ ሆኖም ግን ንክሩማህ እራሳቸው የአጼ ኃይለስላሴ ያልተጠቆጠበ ጥረት ባይኖር ኖሮ የአፍሪካ ድርጅት እውን መሆን አይችልም ነበር በማለት ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል፡፡
በአሁኑ ጊዜ በኢትዮጵያ ያሉት ባለስልጣኖች የጥላቻቸው ባህሪ እና አተገባበር ነጻብራቅ ረዘም ያለ ጊዜ የቆየ ቢሆንም ለዚህ ምክንያታዊ መግለጫ አላገኘሁለትም፡፡ ብዙ ሰዎች በፍርሀት እና በጭንቀት ላይ ያሉ ሰለ ወደፊት ምንይመጣል አያሉ ነው ምክንያቱም በቀጣይነት የሚከሰተው ሁኔታ የማይታወቅ እና ለመተንበይም አስቸጋሪ የሆነበት ሁኔታ ሰለሆነ ነው፡፡ ያለፈውን ጊዜ፣ የጥንት 19ኛውን ክፍለ ዘመን ኢትዮጵያ የሚፈሩትን ሰዎች በትክክል ለመረዳት አልችልም፡፡ በሞያዬ ካለኝ ልምድ አንጻር ያለፈውን ጊዜ የሚፈሩ እና የሚሸበሩ ወንጀለኞ ይሄዉም በፊት በፈፀሙት ወንጀል የሚያዙ ሰለሚመስላቸውና  ሰለሚፈሩ ነው:: በስልጣን ላይ ያሉ አምባገነኖች ስልጣናቸውን ከህግ አግባብ ውጭ በመጠቀም የሰላማዊ ዜጎችን መብት የጣሱ እና የደፈጠጡበትን ወንጀል ለመደበቅ ሲሉ ጥላቻን በማራመድ እና ከፋፍሎ መግዛትን አጀንዳቸው አድርገው ይይዙታል ከሚል መደምደሚያ ላይ ደርሻለሁ፡፡ በኢትዮጵያውያን ልዩ ልዩ ጎሳዎች ላይ ጥልቅ ጥላቻና እና ፍርሀትን በመፍጠር ለፈጸሟቸው እኩይ ተግባራት ተጠያቂ እንዳይሆኑ እና ኃላፊነትን እንዳይወስዱ የጥላቻ መንፈስን እንደ መርህ በመያዝ ያራምዳሉ፡፡ በህዝቦች መካከል ጥላቻን በመዝራትም በኢኮኖሚያዊ ችግሮች ምክንያት ተወጥረው ያሉትን ዜጎች ሀሳቦች ለማስቀየሻ ይጠቀሙበታል፡፡
በጥላቻ የተሞላን ሰው እንደ እራስህ ውደድ፣
ወርቃማው ህግ እንዲህ ይላል፣ “ጎረቤትህን እንደ እራስህ ውደድ፡፡“ እኔ ደግሞ እንዲህ እላለሁ፣ “የሚጠላህን እንደ እራስህ ውድ፡፡“ ከመጥላት ይልቅ መውድደ የተሻለ ነገር ነው፡፡ ጥላቻ ወርዋሪውን ተመልሶ እንደሚጎዳ ቦንብ ነው፡፡ መጀመሪያ ከሚወረውረው ሰው እጅ ይወጣል ተመልሶ ግን በጥላቻ የተሞላውን ሰው እራሱን ይጎዳዋል፡፡ የማንዴላን አባባል በመዋስ፣ ጥላቻ የነብስ መርዝ ነው፡፡ በጥላቻ የተሞሉት በሚጠሉበት ጊዜ መርዝን ይጠጣሉ እናም የሚጠሏቸው እንዲሞቱ ይጠብቃሉ፡፡ በስልጣን ላይ ያሉ ሁሉ ጥላቻን ማራመድ እንዳለባቸው ልዩ ምክር የሚሰጥ ለየት ያለ የፍልስፍና ዓይነትም አለ፡፡ ጥላቻ ሁልጊዜ የተጠላውን ሰው የተወደደ እና የተከበረ ስብዕና ያለው እንዲሆን ያደርገዋል፡፡ በአሁኑ ጊዜ በኢትዮጵያ በስልጣን ላይ ተቆናጥጠው ያሉ ወገኖች በዱሮዋ ደቡብ አፍሪካ ከነበሩት የአፓርታይድ መሰል የመንፈስ ጓዶቻቸው ትምህርቶችን ሊማሩ ይገባል፡፡ የአፓርታይድ ጌቶች የማንዴላን ስብዕና፣ አመራር እና ክብር ለበርካታ አስርት ዓመታት ለማዋረድ ፈለጉ፡፡ ማንዴላ አሸባሪ እና ኮሙኒስት ናቸው በማለት ማንኛውንም ዓይነት የፕሮፓጋንዳ ዘመቻ ከፈቱባቸው፡፡ ይንንም ምክንያት በማድረግ ማንዴላ በእስር ቤት በቆዩባቸው ጊዚያት ሁሉ ምንም ዓይነት የፎቶግራፍ ምስላቸው እንዳይወጣ አደረጉ፡፡ ሆኖም ግን ያልታሰቡ አጋጣሚዎች ተከሰቱ፡፡ በሂደት ጊዜ እያለፈ እና የጸረ አፓርታይድ ንቅናቄው እየተጠናከረ ሲሄድ ማንዴላን አሳንሶ የማየት አባዚያቸው የማንዴላን የመላዕክነት ደረጃ ከፍ እያደረገ ወደ ዓለም አቀፋዊ ተምሳሌነት እንዲሸጋገሩ እገዛ አደረገላቸው፡፡ ከዚህ ሊወሰድ የሚችለው ታላቅ ቁምነገር የአጼ ምኒልክን እና የአጼ ኃይለስላሴን ስብዕና ዝቅ ለማድረግ ጥረት ባደረጉ ቁጥር እነዚህ መሪዎች በኢትዮጵያ የወጣቶች ትውልድ የአስተሳሰብ አድማስ ዘንድ የበለጠ ክብር እና ሞገስን እየተቀዳጁ ታዋቂ እየሆኑ ይሄዳሉ፡፡ በእነዚህ መሪዎች ላይ የማያቋርጥ እና ዘለቄታዊ ያለው የማዋረድ ዘመቻ ባደረጉ ቁጥር የቀድሞው ትውልድ ጉዳዩን የበለጠ እንዲገመግመው እና አቋሙን እንዲያጠናክር ያደርገዋል፡፡
ፍቅር ከጥላቻ በላይ ዘልቆ መሄድን ይጠይቃል፡፡ ዶ/ር ማርቲን ሉተር ኪንግ እና ማንዴላ በሰዎች እና በህብረተሰብ ክፍሎች ዘንድ ፍቅር ያለውን የማይበገር የአሸናፊነት ኃይል፣ እንዲሁም ፍቅር በዘር፣ በጎሳ እና በኃይማኖት የተዘራን የጥላቻ ካንሰር የመፈወስ ችሎታ እንዳለው በግልጽ አስተምረውናል፡፡ ማንዴላ ለመጥላት እና በቀልን ለመፈጸም ምክንያት አላቸው፡፡ ለ27 ዓመታት የማንዴላ ስም የእስረኛ ቁጥር 46664 ነበር፡፡ እ.ኤ.አ በፌብሯሪ 1990 ጧት ከእስር ቤት ተለቅቀው ከእስር ቤቱ በር ሲወጡ ከሚሊዮን ዶላር ዋጋ በላይ የሚያወጣውን ፈገግታቸውን አሳይተዋል፡፡ ለ27 ዓመታት ከቤተሰቦቻቸው ነጥለው በእስር ቤት ውስጥ ባማቀቋቸው የአፓርታይድ ጌቶች ላይ ምንም ዓይነት የጥላቻ ስሜት አላሳዩም፡፡ ማንዴላ ታላቅ ትምህርት አስተምረውን አልፈዋል፣ እንዲህ በማለት፣ “እየተራመድኩ ወደ በሩ በምቃረብበት ጊዜ ይህ ሁኔታ ወደ ነጻነት እየመራኝ እንደሆነ አስብ ነበር፡፡ የበቀልተኝነት ስሜቴን እና ጥላቻዬን እዚያው እስር ቤት ጥዬው ካልወጣሁ እዚያው እስር ቤት እንዳለሁ እቆጥረዋለሁ፡፡“ በማለት የጥላቻን መጥፎነት በግልጽ ተናግረዋል፡፡ ማንዴላ ፍጹም የጥላቻ እስረኛ አልነበሩም፡፡ እስረኛው የአፓርታይድ ጥላቻ ነበር፣ እናም አስረኞቹ የአፓርታይድ አለቆች እና ጌቶች ነበሩ፡፡ ማንዴላ ከእስር ቤት በመውጣት በጥላቻ ሰንሰለት ከአፓርታይድ ግንብ ጋር የታሰሩትን እውነተኞቹን የአፓርታይድ እስረኞች ከጥላቻ፣ ከፍርሀት፣ እና ከበቀልተኝነት ነጻ ለማውጣት ተንቀሳቅሰዋል፡፡
በአሁኑ ጊዜ በኢትዮጵያ በስልጣን ላይ ያሉት ገዥዎች በጥላቻቸው የሚቀጥሉ ከሆነ በደቡብ አፍሪካ አፓርታይድ በስልጣን ላይ በነበረበት ጊዜ የደረሰው ዕጣ ፈንታ የሚደርስባቸው መሆኑን መገንዘብ ይኖርባቸዋል፡፡ በአፓርታይድ የአገዛዝ ዘመን ጊዜ “ነጻዎቹ” ነጮች እውነተኛው የማይቀረው የብዙሀን አገዛዝ በሚመጣበት ጊዜ ለብዙ ጊዜ በጭቆና ቀንበር አስረው ሲያማቅቋቸው የነበሩት ጥቁር አፍሪካውያኖች ምን ሊያደርጓቸው እንደሚችሉ ሌት እና ቀን ያሰላስሉ ነበር፡፡ በጥቁር አፍሪካውያን ላይ የነበራቸው ጥላቻ እንቅልፍየለሽ ሌሊቶችን ብቻ እንዲያሳልፉ አላደረጓቸውም፣ ሆኖም ግን ልቦቻቸው፣ አዕምሯቸው እና ነብሳቸው እንዲሁም ስብዕናዎቻቸውም ጭምር እንዲሰበሩ አደረጋቸው እንጅ፡፡ ሙት መንፈሶች አደረጓቸው፣ ነጻ ሆነው ባሏቸው ኃብቶቻቸው ለመደሰት ባለመቻል የቁም ሙት አደረጓቸው፣ እንዲሁም በኤሌክትሪክ እና በእስር ቤት የሽቦ አጥር ታጥረው የእራሳቸው ጎረቤቶች የእስር ቤት በሮች ሆኑባቸው፡፡ በእርግጥ በጦር ካምፕ የሚኖሩ ህዝቦች ሆኑ፡፡
ምንጊዜም የተሻለ መንገድ አለ፡፡ የጥላቻ ትችት ከማቅረባችን በፊት እውነተኛውን ነገር ለማወቅ የበለጠ ጽናት ሊኖረን ይገባል፡፡ ስለዳግማዊ አጼ ምኒልክ፣ ስለ አጼ ኃይለስላሴ፣ ስለ ኮሎኔል መንግስቱ ኃይለማርያም እና ስለ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ እውነኛውን ነገር ማቅረብ ይኖርብናል፡፡ እነርሱን መጥላት ሳይሆን ከስህተቶቻቸው እንማር፣ እኛ በህይወት ያለነው የእነርሱን ስህተት መድገም የለብንም፡፡ ጥላሸት በመቀባት ላይ ላለመሰማራት ከእነርሱ ስህተት እንማር፣ ነገር ግን የእርቅን መንገድ በመፈለግ የእነርሱን ስህተቶች እናርም፡፡ ከኢትዮጵያ ወጣቱ ትውልድ ጋር ህብረት በመፍጠር ማንም ወንድ ወይም ሴት በማንነቱ/ቷ፣ በዘሩ/ሯ ሳይሆን ሰው በመሆኑ/ኗ፣ አፍሪካዊ/ት እና ኢትዮጵያዊ/ት በመሆናቸው ብቻ በመመልከት አዲሲቷን ፍቅር የነገሰባት ኢትዮጵያ ለመገንባት እንነሳ፡፡ ማንም ወንድ ወይም ሴት ባለው/ላት ስልጣን በመመካት ባልታጠቁ ዜጎች እና በሰላማዊ ሰዎች ላይ የጦር እልቂት ሊያዝዝ/ልታዝዝ የማይችሉበት እና ይህ ዓይነቱ አስተሳሰብም ሊወገድ የሚችልበት ነጻ ህሊናን በመፍጠር አዲሲቷን ፍቅር የነገሰባት ኢትዮጵያ ለመገንባት እንነሳ፡፡ በእያንዳንዱ/ዷ ግለሰብ የጎሳ፣ የእምነት ወይም የቋንቋ ልዩነት ሳንፈጥር በአንድነት በመሆን የእያንዳንዱ/ዷ ዜጋ መብት እና ክብር የሚጠበቅበትን ህብረተሰብ ለመፍጠር እንነሳ፡፡ በዚህ ዓይነት ሁኔታ ነው የወደፊቱን ብሩህ ዘመን ለመፍጠር የምንችለው፡፡ ለብዙ ጊዜ በመቆየት በጊዜ ደመና ተሸፍኖ የደበዘዘውን ነገር ቆፍሮ በማውጣት እና ጥላሸት በመቀባት አይደለም ፍቅር የነገሰበትን የወደፊቱን ትውልድ መገንባት የምንችለው፡፡
በጥላቻ ንግግር አንዘን ወይም ደግሞ አንቆጣ፡፡ ምንም ዓይነት እርባና የለውም፡፡ ይልቁንም ጥላሸት የመቀባት ዘመቻውን በሰከነ መልክ እናጋልጥ፡፡ መላዕክ ለማድረግ የሚደረገው ጥረት ስህተት እና ውሸት መሆኑን እና የኢትዮጵያን ታሪክ ጥላሸት ለመቀበት እና ለመበረዝ የሚደረገውን መዋተት እናጋልጥ፡፡ ከጥላቻ አራማጆች ጋር በማበር እራሳችንን ወደ ጭቃ እና የሚያጣብቅ ቆሻሻ ውስጥ አንጣል፡፡ እንዲህ የሚሉትን የጆርጅ በርናርድ ሻውን ምክሮችን በፍጹም መርሳት የለብንም፣ “ከብዙ ጊዜ በፊት ከአሳማ ጋር ማጥ ዉስጥ ላለመታገል ትምህርት አግኝቻለሁ፣ ለመታገል ከሞከርክ ቆሻሻ ትሆናለህ፣ አሳማው ግን ማጡን የነብሱን ያህል ይወደዋል፡፡“ ጥላቻን ሙያ አርገው ከሚኖሩ ሰዎች ጋር የጥላቻ ቃላትን መለዋወጥ ከአሳማ ጋር በጭቃ ማጥ ውስጥ የነጻ ትግል ውድድርን እንደማድረግ ይቆጠራል፡፡ 
ጥላቻን ወደ ፍቅር መለወጥ
በጥላቻ መንፈስ የተሞሉት ወገኖች ይጥሉ እና ይዋሹ፡፡ ስለዚያ ጉዳይ የምናደርገው አንዳች ነገር የለም፡፡ በእራሳችን የሀይል ንፍቀ ክበብ ውስጥ ያለን ልዩ ችሎታ እራሳችንን ከጥላቻ ወደ ፍቅር ከመቀየር ላይ ነው፡፡ በእርግጥም አሉታዊ ኃይሎችን ወደ አዎንታዊ ኃይሎች የመቀየር ችሎታ አለን፡፡ ከጥላቻ ወደ ፍቅር ለመቀየር እንችላለን፣ ይህን የምናደርገው ግን ነገሩ ቀላል ስለሆነ አይደለም ይልቁንም የበለጠ ከባድ ስለሆነ እንጅ፡፡ ፍቅር በግለሰብ ደረጃም ይሁን፣ በሌሎችም ይሁን፣ በማህበረሰቡ ወይም በአጠቃላይ በህዝቡ ላይ ይሁን ለተግባራዊነቱ ታላቅ ስራ መስራትን ይጠይቃል፡፡
ከማህተመ ጋንዲ እና “እውነተኛው ኃይል”/Satyagraha ከሚሉት አቀራረባቸው እስቲ ትምህርት እንቅሰም፡፡ ጋንዲ እንዲህ በማለት ገለጻ አድርገዋል፣ “እውነት/satya ፍቅርን በማጎናጸፍ የመንፈስ ጽናትን ይወልዳል፣ እናም ከኃይል ጋር ተመሳሳይ በመሆን ያገለግላል፡፡“ ዓላማው በጥላቻ የተሞላው/ችው እንዳያስገድድ/እንዳታስገድድ በማድረግ ሀሳባቸውን ለማስለውጥ ነው፡፡ በተግባራዊነት ሁኔታው ስንመለከተው ዓላማው በጥላቻ የተሞላውን/ችውን ጥላቻ ማራመድ የእራሱን/ሷን ልብ፣ አዕምሮ እና ነብሳቸውን የሚጎዳቸው መሆኑን በማሳመን እንዲቀየሩ ለማድረግ ነው፡፡ ከማንኛውም ጉዳትን ከሚያመጡ ነገሮች ሁሉ የሚጠብቁን እራስን፣ ማህበረሰቡን እና አገርን መውደድ ነው፡፡ በጥላቻ ከተሞሉት ወገኖች ፍቅር የተሞሉ ወገኖችን ለማፍራት እውነተኛውን ኃይል/Satyagraha በተግባር እናውል፡፡
ከዶ/ር ማርቲን ሉተር ኪንግ የምንማራቸው በርካታ ቁምነገሮች አሉ፣ እንዲህም በማለት ያስተምሩናል፣ “ጨለማን ጨለማ አያስወግደውም፣ ብርሃን ብቻ ነው ያንን ማድረግ የሚችለው፡፡ ጥላቻን ጥላቻ ሊያስወግደው አይችልም፣ ፍቅር ብቻ ነው ያንን ማድረግ የሚችል፡፡“ ብለዋል፡፡ እንዲህ በማለትም አስተምረዋል፣ “ይቅርታ የማድረግ ችሎታችንን ማሳደግና ማጠናከር ይኖርብናል፡፡ ይቅርታ የማያደርግ/የማታደርግ ሰው ለማፍቀር ኃይል የለውም/የላትም፡፡ በመጥፎነታችንም ላይ ጥሩ ነገሮችም አሉ፡፡ በመጥፎ ነገሮቻችን ላይም  ጥሩ ነገሮች አሉ፡፡ ይህንን ሁኔታ ባወቅን ጊዜ ጠላቶቻችንን ከመጥላት በመጠኑም ቢሆን እንታቀባለን፡፡“ ይቅርታ አድራጊነት እና እርቅ ብቸኞች የጥላቻ ፈውስ እና መድኃኒቶች ናቸው፡፡
ከዘመናችን ታላቅ ቀልድ አዋቂ ከቻርለስ ቻፕሊን እንኳ ትምህርት መቅሰም ይኖርብናል፡፡ እንዲህም ይለናል፣ “የሰው ልጅ ጥላቻ ያልፋል፣ እና አምባገነኖችም ይሞታሉ፣ እናም ከህዝቦች የነጠቁት ስልጣን ተመልሶ በህዝቡ እጅ ይገባል፡፡ ስለሆነም የሰው ልጅ ሟች እስከሆነ ድረስ ነጻነት ከናካቴው ሊጠፋ አይችልም፡፡“ ነጻነት በጥላቻ ከተሞሉት የሰው ዘሮች ሁሉ የበለጠ እድሜ አለው፡፡ በጎሳ ማንነት መፈረጅን እርግፍ አድርገን እንተው እና ሰው በመሆናችን ብቻ በኢትዮጵያዊነታችን እና በአፍሪካዊነታችን እንኩራ፡፡
በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ በስልጣን ላይ ላሉ የማስተላለፈው መልዕክት፣
በኢትዮጵያ በስልጣን ላይ ሆነው ጥላቻን ለሚያራግቡት አጭር መልዕክት አለኝ፡፡ በአሁኑ ጊዜ የምትቆሰቁሱት የዘር እና የጎሳ ጥላቻ ፍላጻ በአንድ ወቅት ተመልሶ እራሳችሁ ላይ ይሰካል፡፡ በአሁኑ ጊዜ የአጼ ምኒልክን ክብር እና ዝና ለማንቋሸሽ በታለመ ዕኩይ ምግባር ጡት ቆራጭ አረመኔ ነበሩ በማለት በመሳለቅ እና በማፌዝ ላይ ትገኛላችሁ፡፡ በአሁኑ ጊዜ አጼ ምኒልክን እንዲጠሉ የሚሰበክላቸው ሰዎች ነገ ደግሞ አቶ መለስን እንዲጠሉ የማይሰበክበት ምክንያት አይኖርም፡፡ የእናንተ ታላቁ ባለራዕይ መሪ አቶ መለስ በኦጋዴን፣ በጋምቤላ፣ በአዲስ አበባ እና በሌሎችም ቦታዎች በንጹሃን ዜጎች ላይ በፈጸሟቸው የጅምላ እልቂቶች ሳቢያ በድንጋይ እና በእብነበረድ በተቀረጹ ሃውልቶች ላይ ሆነው ሁለተኛው ሮዶልፍ ግራዛኒ በመባል የሚታወሱበት ጊዜ እሩቅ አይሆንም፡፡ ዛሬ ጓደኞች ብላችሁ የያዛችኋቸው ሰዎች ነገ ቀንደኛ ጠላቶቻችሁ ሆነው ይቀርባሉ፡፡ ዛሬ የእናንተ ጠላቶች አድርጋችሁ ጥላሸት የምትቀቧቸው ሰዎች ነገ ጽዋው ሞልቶ እጣ ፈንታችሁ ደርሶ የዘራችሁትን የምታጭዱበት ጊዜ ሲመጣ የእናንተ ጓደኞች ሆነው ይቀርባሉ፡፡
ዳግማዊ አጼ ምኒልክ መልዓክ ወይም ጭራቅ አልነበሩም፡፡ ሰይጣን ወይም ደግሞ እግዚአብሄርም አልነበሩም፡፡ የተቀሩት የአፍሪካ አገሮች በኃአውሮፓ ኢምፔሪያሊስት ኃይሎች ሲቆራረሱ፣ መጫወቻ ሲሆኑ፣ ሲነሱ ሲጣሉ፣ ሲበጠሱ ሲቀጠሉ፣ ሲሸጡ እና ሲለወጡ እንዲሁም ሲጋዙ በነበረበት ጊዜ አጼ ምኒልክ ደግሞ ኢትዮጵያን ሲያጠናክሩ እና ሲያዘምኑ የነበሩ የተከበሩ አፍሪካዊ ንጉስ ነበሩ፡፡ ዳግማዊ አጼ ምኒሊክ በአንድ መለኪያ ብች ይገምገሙ፣ በእውነት! የታሪክ ሰዎች እውነታውን መናገር አለባቸው፣ እና ሁሉንም እውነታዎች፣ ሌላ ምንም ነገር ሳይሆን ስለምኒልክ ያለውን እውነታ ብቻ፡፡ ለአጼ ምኒልክ 100ኛ ሙት ዓመት መታሰቢያ ሲባል እ.ኤ.አ በ1909 በኒዮርክ ታይምስ ባሮን ዲ ጃርልስበርግ የተባለ የቤልጄም አሳሽ ለዳግማዊ አጼ ምኒልክ ምስክርነት ለጋዜጣው ቃል በመስጠት የተዘገበውን በከፊል ምስከርነት እውነታ መረጃ  እንደሚከተለው አቅርቤዋለሁ፡፡ ይህ ታሪካዊ የምስክርነት መረጃ ዳግማዊ አጼ ምኒልክን ከሰሯቸው ስራዎች አንጻር በትክክለኛው የታሪክ ሚዛን ላይ በማስቀመጥ እንዲገመገሙ ያስችላል የሚል ጽኑ እምነት አለ፡፡
ዳግማዊ አጼ ምኒልክ የዘውድ ስልጣኑን ለመቆናጠጥ ትግል ማድረግ ከጀመሩበት ከ20 ዓመታት በኋላ አቢሲኒያን ከከፊል የኋላቀርነት አገዛዝ በማውጣት ወደ አውሮፓውያን የንጉሳዊ ህገመንግስት የአገዛዝ ስርዓት ምሳሌነት አሸጋግረዋታል… እራሳቸውን ነጻ እና በእራስ የሚተማመኑ አድርገው የሚቆጥሩት ዘ እምነገደ የይሁዳ አንበሳ ስዩመ እግዚአብሔር የኢትዮጵያ ንጉሰ ነገስት ዘ ኢትዮጵያ የኢጣሊያንን የቅኝ ግዛትነት ፍላጎት አምባ ጋሪማ ላይ ጦርነት ገጥመው በአሸናፊነት እንዳንኮታኮቱት… አጼ ምኒልክ ከአጼ ዮሀንስ ህልፈተ ህይወት በኋላ እ.ኤ.አ ኖቬምበር 4 1889 የኢትዮጵያ ንጉሰ ነገስት ሆነው ሲሰየሙ የአቢሲኒያን መንግስት ከመሰረቱት የአካባቢያዊ መንግስታት በሙሉ ቅቡልነት አልነበራቸውም፡፡ ከብዙ ድካም እና ትግል በኋላ ነው እነዚህን የአካባቢ ገዥዎች እና ንጉስነታቸውን አንቀበልም ያሉትን አማጺ ገዥዎች በማሳመን እና በኃይል በማንበርከክ በመጨረሻ ስኬታማ ለመሆን የበቁት… ከዚያ በኋላ የአጼ ምኒልክ ዋና ዓላማ የነበረው የአውሮፓን ስልጣኔ ወደ አገራቸው ማስገባት ነበር፡፡ ንጉሱ የፊውዳሉን ህግ በማፈራረስ በእርግጥም በግዛታቸው እስከ አሁንም ድረስ ጨርሶ እንዳልጠፋ እና ባሮችን ነጻ በማውጣት የባሪያ ንግድን በማጥፋት በግዛታቸው በሙሉ ከክፍያ ነጻ የሆነ የትምህርት ስርዓትን ዘርግተዋል፡፡ በዚህም መሰረት እንደማንኛውም የአውሮፓ ሀገር ሁሉ በቀጣዮቹ ትውልዶች ትምህርት በመላ የአቢሲኒያ ግዛት ውስጥ የሚስፋፋ ይሆናል፡፡
ምኒልክ በመላ አፍሪካ በስልጣን ላይ ካሉ መሪዎች ሁሉ ልዩ ባህሪ ያላቸው ናቸው፡፡ እንደ የዲፕሎማሲ ሰው፣ እንደ ገንዘብ ኃላፊ፣ እንደ ወታደር ከሌሎች ወንድማዊ ንጉሶች የቅርበ መረጃዎችን በመውሰድ በእራሳቸው አካሄድ እንደሚመስላቸው የሚተረጉሙ ንጉስ ናቸው፡፡ እንደ ወታደር እና እንደ የዲፕሎማሲ ሰው የኢጣሊያኖችን በአቢሲኒያ መሸነፍ ለንጉሱ እንደ መልካም አጋጣሚ ምን ያህል ጠቃሚ የሆኑ ንጉስ መሆናቸውን አሳይተዋል፡፡ በቅርብ ዓመታት ደግሞ የገንዘብ ብልህ ጥንቁቅ  አያያዝ ምኒልክን ልዩ ያደርጋቸዋል፡፡ ስለገንዘብ እንደ ወጣትም፣ የዙፋን ስልጣናቸውን ከመያዛቸው እና በዙፋኑ ላይ ከተቀመጡም በኋላ በፓሪስ የስቶክ ገበያ ትንበያን/Paris Bourse ላይ ተሳትፎ ማድረጋቸው መልካም ተፈጥሯዊ ችሎታ ያላቸው መሆኑን ያመላክታል፡፡ እነዚህ ጠቃሚ ትንበያዎች የነበሩ ሲሆን ምኒልክ የዙፋን ስልጣኑን ከያዙ በኋላ ለመቋረጥ ችለዋል… የገንዘብ አሰራር ስርዓታቸውን በማስፋት እስከ ዩናይትድ ስቴትስ አሜሪካ ድረስ በማስፋት በአሜሪካ የባቡር ሀዲድ ካምፓኒዎች ላይ ትልቅ የድርሻ ባለቤት ለመሆን በቅተዋል፡፡ ከአሜሪካ የሴኪዩሪቲ ሰርቲፊኬቶች እና ከፈረንሳይ እና ከቤልጄም ባለሀብቶች ጋር ከ25 ሚሊዮን ዶላር ያላነሰ መዋዕለ ንዋይ በስራ ላይ እንዲውል አድርገው ነበር፡፡
በጣም የሚያስገርመው የአቢሲኒያው ደብዛዛ ንጉስ በሁሉም ነገሮች ላይ ያላቸው ሁለገብ እውቀት ነው፡፡ በጣም ምጡቅ የቋንቋ ችሎታ የነበራቸው ሲሆኑ ፈረንሳይኛ፣ እንግሊዝኛ እና ጣሊያንኛ ቋንቋዎችን አቀላጥፈው መናገር ይችላሉ፡፡ አብዛኛውን ጊዜ ለመንግስታዊ ስራቸው ሙሉ ጊዜ ሰጥተው የሚሰሩ ሲሆን በአውሮፓ የሚዘጋጁ ጽሁፎችንም የመከታተል ዕድል ስላላቸው እና በትኩረት ስለሚከታተሉ አዲስ መጽሀፍ በወጣ ቁጥር ስለደራሲው ሲጠየቅ አዲስ አይሆኑም፡፡ ባዲሳባ ቤተመንግስት በሰዎቻቸው በሚታወቁበት መጽሀፍትን በማሰባሰብ ስራቸው እውቅና እንዲሰጣቸው ሲባል በተዘጋጀው ስብሰባ ላይ በተገኙበት ዕለት በቤተ መጻህፍታቸው ከ20 ሺህ ያላነሱ ጥራዞች መገኘታቸው ልዩ ኩራት እንዲሰማቸው አድርጓል፡፡ የምኒልክ መጻህፍትን የማሰባሰብ የትርፍ ጊዜ ስራ በጥንት የአፍሪካ እና የኢስያ ስልጣኔዎች ዘመንም የሚደረግ ነበር፡፡
በአጼ ምኒልክ ላይ የጥላቻ ዘመቻ ከሚያደርጉት ወገኖች ጋር የማቀርበው መደራደርያ 
በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ላይ የጥላቻ ዘመቻ ስለማሰራጨት ጉዳይ የማቀርበው መደራደርያ አለኝ ፡
በአጼ ምኒልክ ስብዕና ላይ የምታደርጓቸውን ውሸቶችና  ቅጥፈቶች  የምታቆሙ ከሆነ እኔም ስለአቶ መለስ የምናገራቸውን እውነቶች መናገርአቆማለሁ!
ጥር 7 ቀን 2006 .
 ምንጭ የኢትዮጵያ ሜዲያ መድረክ