Saturday, April 26, 2014

የዘረኞች ነውር በድሬዳዋ

ድሬዳዋ የኢትዮጵያዊያን ከተማ ነበረች። ኢትዮጵያዊያን የጎሳቸውን አጥር አፍርሰው በኢትዮጵያዊነታቸው ብቻ ለረዥም ዘመን አብረው በድሬዳዋ ኑረዋል። በዚህ ሁኔታ የሚኖረው ህዝብ አብሮ ስቆ ፤አብሮ ተደስቶ፤ ያለው ለሌለው አካፍሎና ተቻችሎ መኖርን የሚያውቅ ነበር። ዛሬ ግን ያች ቀድሞ የምናውቃት ድሬዳዋ ተረት ሁናለች። ሁሉ ስቆና ተደስቶ የሚኖርባት ከተማ ሳትሆን በየወቅቱ በእሳት እንድትጋይ ሁና ብዙዎች እንባቸውን በመዳፋቸው የሚያፍሱባት ከተማ ሁናለች። ብዙዎች የንግድ ሥፍራቸው ተቀነባብሮ በተነሳ እሳት በመጋየቱ ባዶ እጃቸውን ቀርተዋል። ልጆቻቸውም ድሃ አደግ እንዲሆኑ ሁኗል። ይባስ ብሎ ንብረቶቻቸውን ከእሳት ቃጠሎ ለመከላከል እሳቱን ለማጥፋት የተነሱ ዜጎች በአሸባሪነት ተከሰው ህወሃቶች “ ፍርድ ቤት” ብለው ወደ ሚጠሩት ሥፍራ እንዲቀርቡ ሁኗል።
ገ/መድህን ገ/መስቀል፤ ቢኒያም ጌታቸው፤ መቻል አብራር፤ ምትኩ ውብየ፤ ኢዮብ ገብሬ፤ ሃቢብ ሸምሱ፤ ለዒላ ዓሊ ፍትህን በማያውቀው በህወሃት ፍርድ ቤት ቀርበዋል። ከእነዚህ ውስጥ ከገ/መድህን ገ/መስቀል በቀር ሌሎቹ የዋስ መብት ተነፍጓቸው ወሂኒ እንዲቆዩ ተደርጓል። ገ/መድህን ገ/መስቀል በምን ሁኔታ ከሌሎቹ ተለይቶ “ነፃ ሰው” ሊባል እንደቻለ የሚያውቅ የለም። ብዙ ሰዎች ግን በትግራይ ተወላጅነቱ አፍቃሬ ህወሃት ” ተደርጎ እንዲታይ ለማድረግ ነው ይላሉ። ህወሃት በልዩ አፈና የራሱ ዋሻ ያደረገውን የትግራይ ህዝብ ከሌላው ኢትዮጵያዊ ወገኑ ለማቆራረጥ እንዲህ አይነት ያፈጠጠና ያገጠጠ የዘር መድልዎ ሲያደርግ የመጀመሪያው አይደለም። ድህረ ምርጫ 97 ከአዲስ አበባ ከተማ ተግዘው ወደተለያየ ማጎሪያ ከተላኩት በርካታ ሺዎች ውስጥ የትግራይ ተወላጆችን መርጦ “እናንተ ነፃ ናችሁና ወደ ቤታችሁ ሂዱ” ብሎ እንዳሰናበተ የማያውቅ የለም። የዘረኞቹ ቁንጮ መለስ ዜናዊ በህይወት በነበረበት ወቅት ሲደረግ የነበረውና ከህልፈቱም ቦኋላ ቀጥሎ ያለው የህወሃት የዘረኝነት መገለጫ አንዱ መንገድ ይሄው ነው። በትግራይ ወጣቶች የህወት መስዋዕትነት ለስልጣን በቅተው እራሳቸውን ያነገሱ የህወሃት መሪዎች ትግሬን ነፃ ማውጣት ማለት ከሌላው ወገኑ ጋር ውሎ አድሮ ደም የሚያቃባ አድልአዊነት እንዲህ በአደባባይ መፈጸም ነው ብለው ያምናሉ። እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል እንዳለቺው እንስሳ ለህወሃቶች እንዲህ አይነት ዘረኝነት ወደፊት ሊፈጥር የሚችለው አደጋ አይታያቸውም ወይም ስለርሱ ማሰብ አይፈልጉም። ።ከአማራና ከአፋር የሚዋሰኑትን ለም ቦታዎችንና በበከርሰ ምድር ማዕድን የከበሩ ሥፍራዎችን ቀምተው ወደ ክልላቸው ሲጠቀልሉና ነዋሪውን በማፈናቀል የቀድሞ ታጋዮቻቸውን ሲያሰፍሩባቸው አልሰቀጠጣቸውም። ወያኔ የራሱ ዋሻ አድርጎ በሚቆጥረው የትግራይ ክልል ውስጥ እያደረሰ ያለው ስቃይና መከራ የክልሉን ግንብ ጥሶ በመላው አለም በመሰማት ላይ ባለበት በአሁኑ ወቅት በተለያየ የአገሪቱ ክፍል ተበትኖ የሚኖረውን ጥቂት የትግራይ ተወላጅ ተጠቃሚ በማድረግ የትግሬ ነጻ አውጪ ለመምሰል የሚደረገው ጥረት በትግራይ ህዝብ ዘንድ ሳይቀር እየተወገዘ ነው። ዘረኞቹን የህወሃት መሪዎች እረፍት የነሳውና እንዲቅበዘበዙ እያደረገ ያለውም የዚህ ዘረኛ አላማቸው የራሴ ነው በሚሉት የቀድሞ ምሽጋቸው ሳይቀር እየታወቀ መምጣቱ ነው።
ዛሬ ከትግራይ ጀምሮ በመላው አገሪቱ ማለት ይቻላል የወያኔን ዘረኝነትና ዘረፋ የሚቃወሙ ሁሉ ሥልጣንን በተቆጣጠሩ በእነዚህ ዘረኞች እጅ የመከራ ፅዋቸውን እየተጎነጩ ነው። የአሬና አመራርና አባላት ብቻ ሳይሆን በቤተሰቦቻቸው ጭምር ላይ ትግራይ ውስጥ እየተፈጸመ ያለው ግፍ የሚያረጋግጠው ይህንኑ ሃቅ ነው። የታገልነውና የደም መስዋዕትነት የከፈልነው እናንት ጥቂት ዘረኞችንና ቤተሰቦቻችሁን በራሳችን ላይ ለማንገስ አልነበረም እያሉ ያሉ እንደነ አቶ አሰግድ ገብረስላሴ ያሉት ልጆቻቸው ጭምር በጎዳና እየተደበደቡ እስር ቤት ሲወርወሩ ነፍሳቸውንና ስጋቸውን ለህወሃት መሪዎች ያስረከቡት ጥቂት የትግራይ ተወላጆች ግን ከዘረፋ በተገኘ ሃብት ቢጠሩዋቸው የማይሰሙ ዲታ ሆነዋል። በልማትና እድገት ሥም በጋምቤላ ድሆችን ከኖሩበት መሬት አፈናቀለው እና ሜዳ ላይ በትነው መሬት ከተቀራመቱት ባዕዳን በቁጥር የሚበልጡት የዘረኞቹ ጋሻ ጃግሬ የሆኑ ትግሬዎች ናቸው። በአዲስ አበባ በዜጎች ደምና አጥንት ላይ የተገነቡ የትላልቆቹ ህንፃ ባለቤቶች የፋሽስቱ የህወሃት አባላት ናቸው። የአገሪቷን የንግድ ማዕከል ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ ተቆጣጥረው በዚያች አገር የሚዘባነኑት እነዚሁ በትግራይ ሥም የሚነግዱ ቡድኖች መሆናቸውን ህዝቡ የሚያውቀው እውነት ነው።ለትግራይ ነፃ አውጪዎች ሲባል የመከራውን ፅዋ በመጎንጨት ላይ ያለው ህዝብ ቁጣ የዶፍ ዝናብ ሊጥል የተዘጋጀ ሰማይን ይመስላል።ያ ቁጣ የፈነዳ ግዜ የሚያቆመው ምዳራዊ ኃይል እንደሌለ በሚቾት የደነዘዘው የህወሃት አመራር የተገነዘበው አይመስልም።
ስለዚህ ዘረኛና ወንጀለኛ ቡድን እጅግ የሚያሳዝነው ሌላው ነገር 23 አመት ሙሉ የአገሪቱን በትረ ሥልጣን እንዳሻው እያሽከረከረም ቢሆን ከመንደርተኝነት ስሜት ሊላቀቅ አለመቻሉ ነው። ዛሬም እንደትናንቱ ትግራይን መደበቂያ ዋሻ ፤ ዞሮ ዞሮ መግቢያ ለማድረግ የማይፈነቅለው ድንጋይ የለም። ቅድሜ ወያኔ የአገሪቱ ህዝብና መንግሥት ንብረት የነበሩ ንግድ ድርጅቶችን በመውረስ የደለበና ዛሬ በአገሪቱ ብቸኛ የሥራ ተቋራጭ፤ ዕቃ አቅራቢና አገልግሎት ስጪ የሆነው ኢፌርት በስም የትግራይ ህዝብ በተግባር ግን የህወሃት ባለሥልጣኖች የገቢ ምንጭ መሆኑን ያልተረዳ የለም።መመኪያ ዋሻየ ከሚለው የትግራይ ህዝብ መነጠሉን እየተረዳ የመጣው ይሄ ፋሽስታዊ አስተሳሰብ ያለው ነውረኛ ቡድን ሰሞኑን ሌላ አሳፋሪ ድርጊት እየፈፀመ ነው። ”ከትግራይ ህዝብ ጋር መታረቅ” የሚል ዜማ ይዞ ብቅ ብሏል። ህወሃት የነፃ አውጪ ስሙን እንኳን ሳይቀይር የ80 ሚሊዮን ህዝብ ገዢ እኔ ነኝ ብሎ ድርቅ ማለቱን እናውቃለን። ስማችሁን ቀይሩና አገሪቷን ግዙ ቢባሉም በጀ አላሉም። ይሄን ስም ይዘው በትግራይ ህዝብ ላይ ተንጠላጥለው አገሪቷን ሲዘርፉ ኖሩ። በዚህም ዘረፋ ትናንት ወደ ሥልጣን ሲመጡ ሲሙኒ እክሳቸው ውስጥ ያልነበራቸው ዛሬ በዓለማችን ከሚታወቁ ሃብታሞች ተርታ ለመግባት ችለዋል። መሪያቸው የነበረው መለስ ዜናዊ 3 ቢሊየን ዶላር ባለቤት በመሆን ከዓለም ሃብታም መሪዎች ተርታ ስሙ የሚነሳ ሁኗል። ሌሎችም እንደየአቅማቸው በሚሊየን የሚቆጠር ንብረት ዘርፈው ኢንቨስተሮች እኛ ነን ብለዋል። በትግራይ ነጣ አውጪነት ሥም ተደራጅተው የብዙ ንፁሃን ዜጎችን ደም አፍሰው፤ ብዙዎችን ለስደት ዳርገው፤ የብዙ ዜጎችን ቤተሰብ በትነው ሲያበቁ የትግራይን ህዝብ ይቅርታ እንጠይቅ ተባብለው ትግራይ ወርደዋል። ይሄን የሰማ ሌላው ህዝብ ሊሰማው የሚችለውን ቁጣ የትግራይ ህዝብ ያጣዋል ብለን አናስብም።ሌላው በተበደለ፤ ሌላው በተገፋ፤ ሌላው ጦሙን ባደረ፤ ሌላው ለስደት በተዳረገ የትግራይ ህዝብ ይቅርታ የሚጠየቅበት ምክንያት ምን እንደሆነ ግልፅ አይደለም። ለማንኛውም የትግራይ ህዝብ የህወሃት ዋሻና መደበቂያ አልሆንም ብሎ እንቅስቃሴ ጀምሮአል። ይሄ እጅግ የሚደገፍና ግዜው የሚጠይቀው የሞራል ግዴታም ነው። በትግራይ ሥም ተደራጅተው “ለትግሬ ብለን” እያሉ የንፁሃንን ደም ሲያፈሱ እና ቤተሰብ እየበተኑ ሜዳ ላይ ሲጥሉ እያዩ ዝም ማለት የግፉ ተባባሪ ያደርጋል እንጂ ከደሙ የሚያነፃ አይሆንም። ለዚህም ነው የትግራይ ህዝብ ወያኔ በስሙ መነገዱን እንዲያቆም ጠመንጃ ይዞ እስከመፋለም የተነሳው። የትግራይ ህዝብ ዲሞክራሲያዊ ድርጅት /ደሚት/ የትግል አላማ ይህንን ወያኔ የፈጠረውን ጥላቻ የመስበር ተልዕኮ ያለው ነው። የትግራይ መሬትና የትግራይ ህዝብ ከእንግዲህ የወንጀለኛው ህወሃት መደበቂያ ዋሻ አይሆንም።
ህወሃት ከህዝብና ከአገር ለመታረቅ ከፈለገ በትግራይ ሥም ላለፉት 23 አመታት ለፈጸመው ወንጀል ይቅርታ ፍለጋ ትግራይ መንደሮች ድረስ መዝለቅ አይጠበቅበትም። ከትግራይ ውጪ ተጀምሮ ትግራይን ባጥለቀለቀው ኢፍትሃዊነት፤ ግፍና መከራ ጸጸት ከተሰማው ሥልጣን ለመልቀቅ መዘጋጀትና ለኢትዮጵያዊያን ለማስረከብ በመወሰን እዚያው ምንሊክ ቤተመንግሥት ሆኖ አዋጅ ማስነገር ይችላል። ለዚህ ዝግጁነት ተግባራዊ እርምጃ ለምሳሌ የታሰሩትን የፖለቲካ እስረኞች፤ ጋዜጠኞች፤ የሃይማኖት መሪዎችን መልቀቅ፤ የሥልጣን ማስጠበቂያ አድርጎ በዘረኝነት መስፈርት የገነባውን የአፈና ተቋማት ማፍረስ፤ ህዝብ ሃሳቡን በነጻነት የሚገልጽበትንና መሪዎቹን በነጻነት የሚመርጥበትን ዕድል በመፍቀድ ማረጋገጥ ይችላል።
ይህ እስካልሆነ ድረስ ከአደዋ ወይም ከሸሬ የወያኔን ዕድሜ የሚያራዝም ይቅርታ ጨርሶ የሚታሰብ አይደለም። በ23 አመት የሥልጣን ዘመን የተገኘው ዘረፋ አልበቃ ብሎ ሥልጣን ላይ ለመንጠልጠል መንከላወስ ውጤቱ ሁሉንም ማጣት ነው።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!!
source www.ginbot7.org

Friday, April 25, 2014

ከሰማያዊ ፓርቲ የሰልፍ አስተባባሪ ኮሚቴ በየሃይማኖታችሁ ጣልቃ ለተገባባችሁ ኢትዮጵያውያን በሙሉ የተደረገ ጥሪ!

ቀን 18/08/ 2006 ዓ.ም
ውድ ሃይማኖታችሁ ላይ ጣልቃ እየተገባባችሁ ያላችሁ ኢትዮጵያውያን በሙሉ፡- ሰማያዊ ፓርቲ ኢትዮጵያውያን በነጻነት የፈለጉትን ሃይማኖት እንዲከተሉ፣ የፈለጉትን እምነት እንዲይዙ ባለው የጸና አቋም ገዥው ፓርቲ በሙስሊሙና በኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ላይ እያደረገ ያለውን ጣልቃ ገብነት ሲቃወም ቆይቷል፡፡ የሙስሊሙ ማህበረሰብ ገዥው ፓርቲ በሐይማኖቱ ጣልቃ መግባቱን ተቃውሞ የሚያደርገውን ፍጹም ሰላማዊ እንቅስቃሴ በማድነቅ ገዥው ፓርቲ ከህገ ወጥ ተግባሩ እጁን እንዲሰበስብ ምክር ከመለገስ አልፎ በሰላማዊ ሰልፍም ድምጹን አሰምቷል፡፡ በተጨማሪም የሙስሊሙን መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት ላይ የተወሰደው ህገ ወጥ እርምጃ እና በእስር ላይ እየደረሰባቸው ያለውን ስቃይም በጽኑ ሲቃወም ቆይቷል፡፡ ወደፊትም በዚሁ አቋሙ እንደሚቀጥል ይገልጻል፡፡

በተመሳሳይ በክርስቲያኖች በተለይም በኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታዮች ያለውን ጣልቃ ገብነትም በተመሳሳይ ሲቃወም ቆይቷል፡፡ ለአብነት ያህል በዋልድባ ገዳም ላይ የተወሰደውን ህገ ወጥ ተግባር በግልጽ ተቃውሟል፡፡ በአሁኑ ወቅትም ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታዮች በተለይም በማህበረ ቅዱሳን ላይ ጫና እየተደረገ እንደሚገኝ መረጃዎች እየጠቆሙ ነው፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ በማህበሩ ላይ ሊደረግ የታሰበው ሴራ እየተከታተለ ይገኛል፡፡ በኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስትያንም ሆነ በማህበሩ ላይ እየተደረገ ያለውን ጫናም በጽኑ ይቃወማል፡፡
ውድ የሁለቱም እምነት ተከታዮች፡- ሰማያዊ ፓርቲ ህወሓት/ኢህአዴግ የሚያደርገውን ጫና እና ጣልቃ ገብነት በጽኑ እየተቃወመ፣ ማንኛውም በሐይማኖታችሁ ላይ የሚደረግን ጫና በግልጽ እንድትቃወሙ ጥሪ ያቀርባል፡፡ የሁለቱም የእምነት መጽሃፍቶች በአንዳችን ላይ የሚደርሰው ግፍ በሌላኛው ላይም እንዳይሆን መፈለግ እንዳለብን እንደሚገልጹት የእናንተ ብቻ ሳይሆን ሌሎች ላይ የሚደረገውን ጣልቃ ገብነትና ጫናም በመቃወም ለመርህ እንድትቆሙ ማሳሰብ ይፈልጋል፡፡
ሃይማኖት ለአንድ ማህበረሰብ ማንነት መሰረት እንደመሆኑ በአገር ግንባታ ቀላል የማይባል ሚና እንዳለው እናምናለን፡፡ ኢትዮጵያውያን ሐይማኖታች ሳይገድበን ተረዳድተን፣ ተባብረንና ተፈቃቅረን ኖረናል፡፡ ለዚህ አብሮ መኖርና መቻቻልም ሃይማኖታችን የራሱ የሆነ ሚና እንዳለው እናምናለን፡፡ ገዥው ፓርቲ በአሁኑ ወቅት በተለያዩ ሃይማኖቶች መካከል ብቻ ሳይሆን አንድ ሐይማኖት ውስጥ የሚገኙትን የአገራችን ዜጎች በጠላትና በወዳጅነት በመከፋፈል ኢትዮጵያውያን እርስ በእርሳቸው እንዲጠራጠሩ፣ ግጭት ውስጥ እንዲገቡና ሃይማኖታቸውን በነጻነት እንዳይከተሉ እያደረገ ነው፡፡ ይህም ለቀጣይ የአገራችን ሁኔታ አሉታዊ አስተዋጽኦው የጎላ በመሆኑ ፓርቲያችን በጽናት ይቃወማል፡፡
ሰማያዊ ፓርቲ በዚህ ጽኑ አቋሙ አግባብ ያልሆኑ የተለያዩ ስሞች ተሰትቶታል፡፡ አመራሮቹና አባላቱም ታስረዋል፡፡ ተደብድበዋል፡፡ ከተነጠቁት መብቶች መካከል ይህን የእምነት ነጻነት መብት እንዲከበር የሚጠይቁ ጥያቄ ባነሳበት በአሁኑ ወቅት እንኳ ከ50 በላይ የፓርቲው አመራሮችና አባላት ማጎሪያ ቤት ውስጥ ይገኛሉ፡፡ የኢትዮጵያውያን መብት ይከበር ዘንድ የሚከፈለውን ዋጋ ለመክፈልም ቁርጠኛ መሆናችንን መግለጽ እንወዳለን፡፡
ገዥው ፓርቲ በሃይማኖታችን ላይ ጣልቃ በመግባት የዜጎቻችን አንዱንና ዋነኛውን መብት ቀምቷል፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ ይህን የኢትዮጵያውያን መብት ለማስመለስ ሚያዝያ 19 ሰላማዊ ሰልፍ ጠርቷል፡፡ በመሆኑም ይህን የተቀማችሁትን መብት ለማስመለስ በዚህ ሰላማዊ ሰልፍ እንድትሳተፉ ጥሪውን ያቀርብላችኋል፡፡
ኑ ራሳችን ነጻ በማውጣት የአገራችን እጣ ፋንታ እንወስን!
ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ይኑር!
ምንጭ ዘ-ሐበሻ

Thursday, April 24, 2014

AN URGENT APPEAL – From Mesfin Wolde-Mariam

The UN Human Rights Commission
The African Union Human Rights Commission
The International Red Cross
Amnesty International
Human Rights Watch
And
All Men and Women of GOOD WILL
Reeyot Alemu
Reeyot Alemu
Reeyot Alemu is a budding Ethiopianpoet, essayist, and journalist. There are not many Ethiopians of her caliber inside the country. She has been languishing in the famous Ethiopian Prison in Qalliti for almost three years. She was charged of terrorism, a crime she totally abhors. She was sentenced first for eighteen years but later reduced to three.
With the exception of her mother and father, she is not allowed to communicate with anyone, including her sisters, brothers as well as her fiancée.
Reeyot, although constantly in agonizing pain and in need of help, is held in solitary confinement with a very old and sickly foreign woman who herself requires assistance.
Reeyot is suffering from some growth in her breasts. The prison authorities have been reluctant to take her to hospital for medical checkup, even when her parents were prepared to pay the bill. When she became seriously ill she was allowed to see a doctor as a result of which she was taken to the hospital and operated upon. But no sooner had the surgeon finished the operation than she was immediately taken back to prison even before she had fully recovered from the Anastasia.
She now suffers from a relapse on the operated breast and similar growth in her other breast. The prison authorities still demonstrate their reluctance to provide medical treatment even at the expense of her parents.
May God provide the necessary courage to all those institutions and organizations to cry out effectively for this young lady who is suffering at the hands of insensitive prison administration.
source ethioforum.org
posted on April 24 ,2014

Friday, April 11, 2014

በኢትዮጵያ የመብቶች ትግሎች ሁሉ ህወሓትን ከሥልጣን ወደ ማስወገድ አቅጣጫ ያመራሉ!!!

April 10, 2014
የሙስሊም መፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴ መሪዎች የክስ ሂደት በበርካታ አሳዛኝ ጉዳዮች የታጀቡ ቢሆኑም የሚሰጡት ትምህርት ግን ከፍተኛ ነው። እነዚህ ወገኖቻችን “ችሎት” በተሰኘው የአገዛዙ የድራማ መድረግ በመገኘት ፍትህን ለመግደል ካባ ለብሰው “ዳኞች” ተብለው ለተኮፈሱ የአገዛዙ ተላላኪ ካድሬዎች እና ለመላው ኢትዮጵያ ሕዝብ ያደረጓቸው ጠንከር ያሉ ንግግሮች ካድሬ “ዳኞችን” አሳፍረዋል፤ ኢትዮጵያዊያንን ግን አኩርተዋል። እኚህ ወገኖቻችን ከወያኔ ችሎት ፍትህ ይገኛል የሚል ብዥታ ባይኖራቸውም መድረኩን መልዕክት ለማስተላለፊያነት ተጠቅመውበታል። በዚሁ መድረክ በአገዛዙ እጅ ከወደቁበት ጊዜ ጀምሮ እየደረባቸው ስላለው ሰቆቃ ሲናገሩ አድማጮች ሊቆጣጥሩት የማይችሉት ሐዘንና እልህ ውስጥ እንዲገቡ አድርጓቸዋል።
ወያኔ እንዲህ ዓይነቱ ጭካኔ የሚፈጽመው በሙስሊም መሪዎች ላይ ብቻ አይደለም። የህግ እውቅና የተሰጣቸው መብቶቻቸው እንዲከበርላቸው በጠየቁ ወገኖቻችን ሁሉ ተመሳሳይ ሰቆቃ ሲፈጸም ኖሯል፤ አሁን እየተፈጸመ ነው። “ኑሮ ከበደን” ያሉ ወጣቶች ተደብድበዋል። “የእርሻ መሬት አጣን” ያሉ ገበሬዎች ከያዙት ቁራሽ መሬት ተፈናቅለዋል፣ ተግዘዋል፣ ከነልጆቻቸው ለጎዳና ኑሮ ተዳርገዋል። በሀረር እና በአዲስ አበባ ከተሞች እንደታየው “ነግደን እንኑር” ባሉ ነጋዴዎች ላይ ከአቅም በላይ ከሆነ ግብር ጀምሮ በንብረታቸው ላይ እሳት እስከመልቀቅ የደረሰ አረመኔዓዊ ድርጊት ተፈጽሟል።
በዓለም ዓቀፍ የሰብዓዊ መብቶች ድንጋጌ አንቀጽ 18 መሠረት እያንዳንዱ ሰው በግሉም ሆነ በጋራ የፈለገውን ሃይማኖት የመከተልና የማስተማር፤ ያልፈለገውን ደግሞ የመተው መብት አለው። ስለሆነም የሙስሊም መፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት ተግባራት በዓለም ዓቀፍ የሰብዓዊ መብቶች ድንጋጌ እውቅና ለተሰጣቸው መብቶቻቸው መከበር ያደረጉት ትግል ነው። ለወጉ ያህል “ሕገ መንግሥት” ተብሎ በሚጠራው ኢትዮጵያዊያንን ለመክሰሻነት ብቻ በሥራ ላይ በሚወለው ሰነድ ውስጥ የተካተቱ ቢሆንም ዓለምዓቀፍ እውቅና ያገኙ መብቶች ኢትዮጵያ ውስጥ ተረግጠዋል። ለእነዚህ መብቶች መከበር በጽናት የቆሙ የኢትዮጵያ ውድ ልጆች ከተራ የመንደር ካድሬና ጆሮ ጠቢ እስከ እስከ ከፍተኛው እርከን ባለ ባለሥልጣኖች ተዋክበዋል፤ ሰቆቃ ተፈጽሞባቸዋል።
ሙስሊሙ ማኅበረሰብ ለእምነት መብቶቹ መከበር እስካሁን ያደረገው ተጋድሎ የሚደነቅ ነው። የተቀናጁ እንቅስቃሴዎቹ፣ ተምሳሌታዊ የተቃውሞ ምልክቶች አጠቃቀሙ የሚያበረታታ ነው። ክርስቲያኑ ከዚህ የሚማራቸው በርካታ ቁም ነገሮች አሉ።
ከሙስሊም እንቅስቃሴና ወያኔ ይህንን እንቅስቃሴ ለማፈን እየሰዳቸው ካሉ እርምጃዎች የምንረዳው አንድ ትልቅ ሐቅ የቱን ያህል ጨዋና የሰለጠነ ቢሆን ወያኔ የሕዝብ ድምጽ ለማዳመጥ ፍላጎት የሌለው መሆኑን ነው። ሙስሊም ወገኖቻችን ጥያቄዎቻቸውን በሚያስገርም ቁጥብ ሥነሥርዓት (ዲሲፕሊን) ቢያቀርቡም ከወያኔ የተሰጠው ምላሽ ግን አፈና፣ ረገጣ፣ ቶርቸር እና ከእስከዛሬዎቹ ይበልጥ አፋኝ የሆኑ ደንቦችና ድንጋጌዎችን ነው። ሌሎች የኅብረተሰብ ክፍሎች ያደረጓቸው ትግሎችም እንደዚሁ ወደ ባሱ የመብት ጥሰቶች እያመሩ ነው። ከዚህ የምንማረው ነገር ትግሉ ውጤታማ እንዲሆን ስትራቴጂዎችን መፈተሽ እንደሚያስፈልግ ነው።
እንደሚታወቀው፤ ሰብዓዊ መብቶች እርስ በርሳቸው የተቆራኙ፤ እርስ በርሳቸውም የሚደጋገፉ ናቸው። አንዱ የመብት ዓይነት ሲጓደል፤ ሌላውም አብሮ ይጓደላል። ለምላሴ የመናገር መብት ተገፎ እያለ የማምለክ መብት ሊፋፋ አይችልም፤ ወይም ደግሞ ፍትሃዊ ዳኝነት የማግኘት መብት ተጥሶ እያለ የማምለክ መብትን የሚያስከብር ተቋም ሊኖር አይችልም።
ለመብቶች መከበር የሚደረጉ ትግሎች፤ በተለይም ደግሞ የሙስሊም ወገኖቻችን ትግል የደረሰበት ደረጃ በአንክሮ ሲጤን ስትራቴጂን በተመለከተ በጥልቀት ልናስብባቸው የሚገቡ በርካታ ጉዳዮች መኖራቸውን እንገነዘባለን። ለጊዜው ሁለት ነገሮች ላይ አጽንዖት ሰጥተን እናልፋለን።
  1. ከላይ እንደተገለፀው የመብት ትግሎች ሁሉ መደጋገፍ ይኖርባቸዋል። ቀደም ሲል በባህርዳር፣ በኋላም በአዲስ አበባ በሴቶች ዓለም ዓቀፍ ቀን አሁን ደግሞ በደሴ ውስጥ እንደታየው የመብት ጥያቄዎች ሁሉ ተደጋግፈው መነሳት ይኖርባቸዋል። ይህ የመደጋገፍ ልምድ የሁለቱ ትላልቅ ሃይማኖቶች ተከታዮች ለየእምነቶቻቸው ነፃነት በሚያደርጉት ትግል ውስጥ መኖር ይኖርበታል። የሙስሊሞች የመብት ጥያቄዎች የክርስቲያኖችም፤ የክርስቲያኖች ደግሞ የሙስሊሞችም መሆን ይኖርበታል።
  2. በሥልጣን ላይ ያለው የህወሓት አገዛዝ አንዱንም የመብት ጥያቄ መመለስ የማይችል መሆኑ ግልጽ መሆን ይኖርበታል። በኢትዮጵያ ተጨባጭ ሁኔታ የመብት ጥያቄዎች ግብ ወያኔን ከሥልጣን ከማባረር ያነሰ መሆን አይችሉም። ስለሆነም የመብት ማስከበር ትግል ስናካሂድ ይህን አልመን እና ለዚህም ተዘጋጅተን መሆን ይኖርበታል። ይህ ደግሞ ከፍተኛ የስነልቦና፣ የድርጅትና የስልት ዝግጅት ይጠይቃል።
ግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ሰብዓዊ መብቶችን ለማስከበር ህወሓት ከሥልጣን መወገድ ይኖርበታል ብሎ ያምናል። ወያኔ በሥልጣን ላይ እስካለ ድረስ መገለል፣ መረገጥ፣ መጋዝ፣ መሰደድ፣ መደብደብ፣ የማይቀርልን በመሆኑ ሥቃያችንን ለመቀነስ ወያኔን ማስወገድ ይኖርብናል ብሎ ግንቦት 7 በጽኑ ያምናል። ከዚህ በተጨማሪ በተለያዩ መንገዶችና ምክንያቶች የምናደርጋቸው ትግሎች ወደ አንድ አቅጣጫ ያመራሉ ብሎ ያምናል። ትግሎቻችን ዞሮ ዞሮ ህወሓትን ከሥልጣን ወደ ማስወገድ ማምራታቸው ግልጽ ስለሆነ ለዚህ የሚያስፈልገውን ስነልቦናዊና ቁሳዊ ዝግጅቾችን እናድርግ ይላል።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!
 source www.ginbot7.org

Saturday, April 5, 2014

ያልዘሩትን ማጨድ ከቶ አይቻልም!!

April 4, 2014
የወያኔ መንግስት የኢትዮጵያን ብሄር ብሄረሰቦች አጋጭቶ በመካከላቸው ጥርጣሬና መፈራራት አንግሶና የታሪክ ጠባሳዎችን እንደ አዲስ በመጓጐጥ እያደማ ከፋፍሎ ለመግዛት ካለመታከት ያደረጋቸው ሙከራዎች ገና ፍሬ ባያፈሩም ቁጥቋጦዎቹ መብቀል ጀምረዋል። እዚህም እዚያም በካድሬዎች የውስጥ ለውስጥ ተልእኮ የሚለኮሱ እሳቶች መብለጭለጭ ጀምረዋል። ሌላው ቀርቶ በአንድ ብሄረሰብ መሃል ሳይቀር በከባቢ ልዩነቶች ብቻ መናቆሮችና መጋደሎች እያስተዋልን ነው። ሰሞኑን በጉጂና በቦረና ኦሮሞዎች መካከል የወያኔ ሎሌዎች በሚያበረታቱት አተካሮ የብዙ ወገኖቻችን ህይወት ጠፍቷል። ሰዎች ከኑሮአቸው ተፈናቅለዋል። ወያኔ እንደኳስ ጨዋታ ተመልካች ዳር ሆኖ ይመለከታል፣ ያጨብጭባል።
ሰሞኑን ባህርዳር ከተማ ውስጥ በተካሄደ የስፖርት ውድድር ላይ አሳፋሪ ክስተት ነበር። ለሰሚው የሚቀፍ ብልግና የተቀላቀለበት ስድብና ቁርቋሶ አይተናል። ከበስተጀርባ ሆነው ይህንን ለፍቅር ብቻ ሊውል የሚገባ የስፖርት ዝግጅት መርዝ ረጭተውበታል። ከዚህ ላቅ ያሉ የተንኮል ድግሶችም ተደግሰው ህዝብ ውስጥ በወያኔ ከተነዙ የመርዝ ቢልቃቶች ውስጥ ስራ ላይ ሳይውሉ ቀርተዋል።
ይህ በታሪካችን ታይቶ የማይታወቅ ዘር የሚዘራው ወያኔ ያልተከፋፈለ ህዝብ አይገዛልኝም በሚል ፍልስፍና እንደሆነ በተደጋጋሚ እያየን ነው። ሶማሌ ክልል ውስጥ በተቋቋሙ ልዩ ፖሊስ በሚል ስያሜ በሚጠሩ የመንግስት ሃይሎች ጥቃት ቁጥሩ እጅግ በርካታ የሆነ የኦሮሞ ማህበረሰብ ከኖረበት መሬት ተጠራርጎ እንዲወጣ ተደርጓል። ብዙዎቹ ተገድለዋል። ብዙ ደም መቃበት ተፈጥሯል። በየክልሉ ምስኪን የአማራ ገበሬዎችን መሬት ንብረት በመንጠቅ አከባቢውን ለቀው እንዲሄዱ አድርገዋል። መሄጃ የለንም ያሉትንም ቀጥቅጠው እንደገደሏቸው ሰሞኑን ከጅባትና ሜጫ አካባቢ ያሉ መረጃዎችን አይተናል።
እነዚህ በየቦታው የሚብለጨለጩ እሳቶች በዚህ ከቀጠሉ ሁላችንም ወደ ሚያቃጥልና የሚለበልብ የሰደድ እሳት ማደጉ አይቀርም። የወያኔ ባለሟሎች ካለምንም ይሉኝታና ማሰላሰል ይህንን እሳት እያራገቡ ይገኛሉ።
ይህንን አደገኛ አዝማሚያ በንጭጩ ማስወገድ የሚችለው ራሱ ህዝቡና የኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ የነጻነት ሃይሎች ድምጽና ህብረት እንጂ የወያኔ መንግስት አይደለም። ስለዚህ ህዝቡ በተለይም ወጣቶች ከዚህ ወጥመድ ሰብረው እንዲወጡ ግንቦት 7 የነጻነት፣ የፍትህና የዲሞክራሲ ንቅናቄ አጥብቆ ያሳስባል። ተመሳሳይ ተንኮሎችንም ማጋለጡን ይቀጥላል። የብሄርሰብ ልሂቃንም ይህንን መርዝ እንዲቋቋሙ፣ ይልቁንም ወያኔ እንዳይመቸው ይበልጥ መቀራረብና ፈተናውን በጋራ እንድንቋቋም ጥሪያችን በድጋሜ እናቀርባለን።
ያልተዘራ አይታጨድም። ወያኔ የዘራልን መርዝ የሚያፈራው መርዝን እንጂ ሌላ አይደለም። ልዩነቶቻችን እንደዘመኑ በሰለጠነ ዲሞክራሲያዊ መንገድ እንጂ በተያዘው መንገድ ማስወገድ አይቻልም።
ዞሮ ዞሮ በዚህ ሳይጣናዊ የወያኔ መሰሪ ሴራ ለምትፈስ ለእያንዳንዶ የደም ጠብታ ተጠያቂው የወያኔ ጉጅሌ መሆኑን አጥብቀን እናሳስባለን። በመሆኑም ለመከፋፈል ከመመቻቸት ይልቅ አንድነታችን በማጥበቅ የነጻነት ሃይሎችን በመቀላቀል ራሳችን እና የሀገራችንን ህልውና ከዚህ ከወያኔ የመከፋፈል መርዝ እንታደግ።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!!
source www.ginbot7.org