Sunday, November 30, 2014

እናታችን ፋናዬና ተመስገን በዝዋይ…. (የጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ወንድም እንደፃፈው)

ከታሪኩ ደሳለኝ 
(የጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ወንድም)
ያቺ የስምጥ ሽለቆ ከተማ ይበልጥ መንደድ ከጀማመራት አንድ ወር አልፏታል:: በፍትህ መዛባት ስሜቱ የተጎዳ፣ በወገኖቹ ስቃይ መንፈሱ የታመመ፣ ሀገራቸውን ከስቃይ መታደግ በሚችሉበት እድሜያቸው በታሰሩ፣ በተሰደዱና በተገደሉ ወገኖቹ ልቡ ያዘነ፣ ለሀገሩና ለባንዲራው ያለው ፍቅር ጥልቅ የሆነ አንድ ወጣት ጋዜጠኛ በውስጧ ይዛለች፡፡ ዝዋይ፡፡
ከዚህች ከተማ ሦስት ኪሎ ሜትር ገደማ ወደሚርቀው የዝዋይ እስር ቤት ለመሄድ የአስፓልት ዱካ እንዳረፈበት በሚያሳብቀው ኮሮኮንቻማ መንገድ ማለፍ የግድ ይላል፡፡ ከረጅም ዓመታት በፊት ተሰርቶ ዛሬ አስታዋሽ ያጣው ይህ ጎዳና እስረኞችን የመጠየቁን ጉዞ አስቸጋሪ አድርጎታል፡፡ ከፀሐዩ ግለት ትይዩ ያለው የመሬቱ አቧራ በእግሩ ቆሞ ይሄዳል ብል አይበዛበበትም፡፡ ይህን አልፈን ግዞት ቤቱን እናገኛለን፡፡ የእስር ቤቱን መግቢያ ያለበሰው አቧራ ደግሞ ቅጥሩን በቁፋሮ የተገኘ ጥንታዊ ከተማ አስመስሎታል፡፡ የግቢው ገፅታ ለዕይታ በማይስቡ ነገሮች ቢከበብም፣ ተናፋቂውን ብዕረኛ ግን ደጋግሜ እንድጠይቀው ከወንድምነት የሚዘለው ጥንካሬው ይስበኛል፡፡
በአቧራውና በንዳዱ መካከል ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ከቀድሞ ይልቅ በጠነከረ ፅናቱ ስለመኖሩ ሳስብ ደስተኛ እሆናለሁ፡፡ እናታችንስ ምን ታስብ ይሆን? የማይበርድ፣ የማይዳፈንና የማይጠፋ የሀገር ፍቅር ስሜቱ ከአቧራውና ከንዳዱ በላይ መሆኑ ለእርሷ ምን ስሜት ያጋባባታል?
yetemesgen enat
እናታችንና ተሜን ሲገናኙ…
ዛሬ ቅዳሜ ህዳር 20/07 ዓ.ም ነው፡፡ እናቴ አብረዋት ከኖሩ ጎረቤቶቿ ጋር በመሆን፣ ዝዋይ እስር ቤት ከከተመ አንድ ወር ያለፈውን ተመስገንን ልታየው ተሰናድታለች፡፡ ዝዋይ ከሄደ ወዲህ አይታው አታውቅም፡፡ እንደናፈቃት ግን የፊቷ ገፅታ ይመሰክራል፡፡ እንደ ልጅነቱ ፀጉሩን ባትደባብሰውም፤ እጁን ልትነካውና በዕርጅና አንደበቷ ‹እንዴት ነህ?› ልትለው ወደዚያው እያቀናች ነው፡፡ ጠዋት ወጥተው ማታ እንደሚገቡት፣ ክፍለ-ሀገር ሰንብተው እንደሚመለሱት እንደ ጓደኞቿ ልጆች ተመስገን እንደማይመለስ የተረዳችው እናታችን ልጇ ጋር እየሄደሰች ነው፡፡
ለሊት 11፡30 ከጀሞ ኮንዶሚኒየም የተነሳችው መኪና ዝዋይ የደረሰችው ከጠዋቱ 2፡20 ላይ ነበር፡፡ አስፋልት መሰል ፍርስራሽ መንገዱን ስለለመድኩት ነው መሰለኝ ዛሬ አልሰጠኝም፡፡ ፍተሻውን አልፈን እስረኛና ጠያቂ የሚገናኘበት ቦታ ላይ ደረስን፡፡ ከነበርነው ሰዎች ይልቅ እናታችን ጉጉት እንዳደረባት ለመናገር ሁኔታዋን ማየት ብቻ በቂ ነው፡፡
እናታችን ተመስገን በልጅነቱ ከዕኩዮቹ ጋር ተጫውቶ ሲመጣ ጠብቃዋለች፣ ትምህርት ቤት ውሎ ሲመጣ ጠብቃዋለች፣ ስራ ውሎ ሲመጣ ጠብቃዋለች፤ አንዳንዴም ሲያመሽ ደውላ ‹‹አልመሸም፤ የቀረው ለነገ ይቆይህ›› ትለዋለች፤ እርሱም ሁሌ እንደሰማት ነበር፡፡ ዛሬ ግን ልጇን የምትጠብቀው ከትምህርት ቤት አልያም ከጨዋታ ወይም ከስራ አይደለም፡፡ ከእስር ቤት ውስጥ እንጂ!
እናታችን እስረኞች ከሚወጡበት በር ላይ ከተቀመጠችበት ደቂቃ ጀምሮ አይኗን አላነሳችም፡፡ በሩ ሲከፈት የወታደር ልብስ የለበሰ ወጣት ወጣ፡፡ ከወታደሩ በኋላ ተሜ እስካርፉን እንዳደረገ ተከተለ፡፡ እናቴ ከመቀመጫዋ ተነሳች፤ ዐይኗቿ እንባ አዘሉ፡፡ በዕስረኛና በጠያቂ መሀል ያለውን አጥር ተደገፈች፡፡ ሌላ ጊዜ አጥሩን መደገፍ የሚከለክሉት ወታደሮች እናታችንን ግን ጥቂት ታገሷት፡፡ ምን ያድርጉ? እነሱም እኮ እናት አላቸው፡፡ ከተመስገን ኋላ ሌላ ወታደር አለ፡፡ በሁለት ወታደሮች መካከል ሆኖ ተሜ እናቱን አያት፤ ፈገግ አለ፡፡ እየቀረበ ሲመጣ ግን ፈገግታው ከፊቱ ላይ ጠፍቶ በሀሳብ ተተካ፡፡ እናቴን በዚህ እድሜዋ አንከራተትኳት ብሎ እንዳላሰበ እርግጠኛ ነበርኩ፡፡ ከዚህ ይልቅ ስንትና ስንት እናቶች በየቦታው እየተንከራተቱና እየተሰቃዩ ስለመሆናቸው እያሰበ የተጨነቀ ይመስላል፡፡ እናትና ልጅ አንገት ለአንገት ተቃቅፈው ቆዩ፡፡ ምን አለ ባይለያዩ? እንዲሁ እንዳሉ ወደ ቤት ቢሄዱስ ምን ነበረበት?
ይሄ ግን አይሆንም፤ ይሄ ቦታ ተሜ ለሀገሩ የከፈለውን፣ እየከፈለ ያለውንና የሚከፍለውን መስዋዕትነት ማቅረቢያው ቦታ ነው፡፡ ተሜ ወደ ቤት አይሄድም፡፡
ተሜና እናቴ የተጫወቱት ብዙ ነው ፡፡ ሲገናኙ የነበረው ድባብ ጠፍቶ ሁለቱም ደስ ብሏቸዋል፡፡ ተሜ ትንሽ አይቷት ‹‹ከስተሻል›› ሲላት ፈገግ እንዳለች ‹‹አረ አልከሳሁም፤ አንተ ግን ጤናህ እንዴት ነው?››፤ ‹‹ደህና ነኝ››… እናቴ በየመሀሉ ጨዋታቸውን ገታ እያደረገች በስስት ታየዋለች፡፡ እናትና ልጅ የሆድ የሆዳቸውን እንዲያወሩ የፈቀዱት ወታደሮችም ሁለቱን በስስት የሚያዩ ይመስላሉ፡፡
ሳይታወቀን 6፡00 ሆነ፡፡ የመሰነባበቻ ጊዜ ደረሰ፡፡ እናቴ እየሳቀች አቀፈችው፤ ተሜም እየሳቀ ተሰናበታት፡፡ እንደ አመጣጡ በሁለቱ ወታደሮች መካከል ሲሄድ ከጀርባው ትክ ብላ አየችው፡፡ የሆነ ነገር ልትል የፈለገች ትመስላላች፡፡ ‹‹ተመስገን›› አለች፤ አልሰማትም፡፡ በሩን አልፎ ገባ፡፡ እሱ ፊት የደበቀችውን እንባ ማቆም አልቻለችም፡፡ በዝዋይ እስር ቤት ውስጥ ከፈገግታዋ ጋር አለቀሰች፡፡
እሁድ ህዳር 21/07 ከንጋቱ 12፡00 ሰዓት፡፡ እናቴ ልጇ እስኪፈታ አልጋ ላይ አልተኛም ብላ መሬት መተኛት ከጀመረች 1 ወር ከ17 ቀኗ ነው፡፡ የዛሬውን ለሌት እንዳለፉት ጊዜ አንዴም ተነስታ ‹አይ ልጄ› ወይም ‹እህህ….እህህ….› ሳትል በሰላም ተኝታ በማደሯ ሳልተኛ እያየኋት አደርኩ፡፡ ልክ 12፡10 ሲል ነቃች፡፡ ስታየኝ እያየኋት ነው፡፡ ‹‹ስንት ሰዓት ሆነ?›› ነገርኳት፡፡ አላመነችም፡፡ ተሜ ከታሰረ ጀምሮ እንደ ዛሬ ተኝታ አታውቅም፡፡ ተነሳች፡፡ ‹‹እስከዚህ ሰዓት ስተኛ ዝም ትላለህ?›› አለችኝ፡፡ ‹‹እንዴት ዝም አልልም?›› አልኳት፡፡ ‹ዛሬ የዓመቷ ማሪያም ነች› አለችኝ፡፡ ፊቷ ላይ ድካም አይታይባትም፡፡ … ከደቂቃዎች በኋላ የሀገር ባህል ጥበብ ቀሚስ ለብሳ አየኋት፤ አምሮባታል፡፡ የደስታ ሲቃ ይዞኝ ‹ትላንት እንዴት ነበር?› አልኳት፡፡ በፈገግታ እያየችኝ ‹‹ልጄ ጀግና ነው፤ ጀግና›› ስትል መለሰችልኝ፡፡ እኔም በመስማማት ራሴን ነቀነኩ፡፡ እናቴ በንጋት ፀሐይ ታጅባ የሀገር ባህል ልብሷን እንደለበሰች ስትሄድ በዐይኔ ተከተልኳት፡፡ ይሄ ብርታቷ እስከመቼ እንደሚቆይ እያሰብኩ ነበር፡፡
ተሜ ለሀገሩ ሲልና ሀገሩ እንድትሆን የሚመኝላትን በመፃፉ በግዞት እስር ቤት በአቧራና በንዳድ መሀል እንዲሰነብት ተፈርዶበታል፡፡ ፍትህ የነገሰባት፣ ልጆቿ የማይገደሉባትና የማይሰደዱባት ኢትዮጵያ እንደምትመጣ በተቃጠለ ስሜት እያሰበ፣ በማለዳ የወጣችውን የንጋት ፀሐይ በፈገግታ እያያት እንደሆነ ሳስብ እኔም በደስታ ተሞላው፡፡
ምንጭ ዘ-ሐበሻ

Is H&M Turning a Blind Eye to Land Grabs in Ethiopia? A TV4 Investigation


Tuesday, November 25, 2014

London man Andargachew Tsege faces death penalty in Ethiopia


“የደም ከፈን!” ኦባንግ ለስዊድኑ ባለሃብት ማስጠንቀቂያ ላኩ

የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ዋና ዳይሬክተር ኦባንግ ሜቶ ለታዋቂው የስዊድን ጨርቃጨርቅ ዓለምአቀፍ ቸርቻሪ H&M Hennes & Mauritz AB (H&M) ፕሬዚዳንትና ዋና ሥራአስኪያጅ ካርል ዮሐን ፔርሶን ከህወሃት/ኢህአዴግ ጋር ስለሚያደርገው የንግድ ውል ኩባንያቸው ሊገጥመው ስለሚችል አደጋ ማስጠንቀቂያ ልከዋል፡፡
ሰኞ በዋሽንግተን ዲሲ በተደረገ ሥነስርዓት ሚ/ር ፔርሶን የ2014 በንግድ የማያዳላ ተሸላሚ መሆናቸውን አስመልክተው በላኩት ደብዳቤ ላይ ኩባንያቸው በኢትዮጵያ ሊጀምር ያለው የንግድ ስምምነት ፍጹም አድሏዊነት የተሞላበት መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በተለያዩ የዜና ማሰራጫዎች እንደተመለከተው H&M ኩባንያ ከኢህአዴግ ጋር ለሚያደርገው ውል ለሸሪክነት የተመረጡት አምስት የአገር ውስጥ ኩባንያዎች ሶስቱ የህወሃት የግል ሃብት የሆነው የኤፈርት አባል ኩባንያዎች መሆናቸውን ኦባንግ በደብዳቤያቸው አሳውቀዋል፡፡ ሌላው ኩባንያ ደግሞ የህወሃት/ኢህአዴግ ቀኝ እጅ የሆኑትና በኢትዮጵያ ውስጥ የፈለጉትን ዓይነት ንግድ ያላንዳች የህግ ገደብ እንዲሁም ተገቢውን ግብር ሳይከፍሉ ንጹህ ትርፍ የሚያጋብሱት የሼኽ መሓመድ ሁሴን አላሙዲ ኩባንያ መሆኑን “ጥቁሩ ሰው” ኦባንግ ሜቶ አመልክተዋል፡፡ የአምስተኛው ሸሪክ ኩባንያ ማንነት እስካሁን አልታወቀም፡፡
የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ (አኢጋን) በመርህ ደረጃ ልማት፣ ዕድገት፣ የንግድ ሽርክና፣ ወዘተ የሚደግፍ መሆኑን በደብዳቤው ላይ የተመለከተ ሲሆን ችግር የሚሆነው ግን እንዲህ ያለው ሽርክና በሰብዓዊ መብትና ሌሎች የዜጎችን መብት በመርገጥ በአምባገነንነት ለተቀመጠው የህወሃት/ኢህአዴግ አገዛዝ ዕድሜ ማራዘሚያ የመሆኑ ጉዳይ እንደሆነ ኦባንግ አመልክተዋል፡፡
ለአንድ ወገን (ለአንድ ዘር/ጎሣ) ፍጹም አድሏዊ በሆነ መልኩ “የራሴ” የሚላቸውን እየጠቀመ በሥልጣን ከቆየው ህወሃት ጋር በንግድ ውል መተሳሰር በመልካም አሠራሩ ለታወቀው እንደ H&M ላለው ኩባንያ ስም ወደፊት ትልቅ ችግር እንደሚፈጥር በደብዳቤው በዝርዝር ተመልክቷል፡፡ ከዚያም ባሻገር በአፍሪካ በሴራሊዮን “የደም አልማዝ” በመውሰድ ራሳቸውን እያበለጸጉ እንዳሉት ሁሉ ከህወሃት ጋር በጨርቃጨርቅ ንግድ ሽርክና መጀመር “የደም ከፈን” እያመረቱ ማትረፍ እንደሆነ በማስጠንቀቅ ኩባንያቸው ሊደርስበት የሚችለውን አስቸጋሪ መዘዝ ኦባንግ በደብዳቤያቸው ላይ ጠቅሰው የቅድሚያ ማስጠንቀቂያ ለባለሃብቱ ሰጥተዋል፡፡
ለሚገዛው ሕዝብ ቅንጣት ታህል ሐዘኔታ የማይሰማው ህወሃት/ኢህአዴግ በፖለቲካው መስክ ፓርላማ ብሎ ባስቀመጠው መሰብሰቢያ 99.6በመቶ መቀመጫውን መቆጣጠሩን፣ አፋኝ የመያድ፣ የጸረ ሽብርተኝነት ወዘተ ሕግጋትን በማውጣት ተቃዋሚዎቼ ናቸው የሚላቸውንን ሁሉ በአሸባሪነት እየከሰሰ ለእስር፣ ለግድያ እና ለስደት እንደሚዳርግ፤ በሰብዓዊ መብት ረገጣ በተደጋጋሚ የተወነጀለ መሆኑን፣ ወዘተ ማስረጃዎችን በመጥቀስ አቶ ኦባንግ አስረድተዋል፡፡ ለማስታወስም ያህልም በኦጋዴን ክልል በጋዜጠኛነት ተሰማርተው የነበሩት ሁለት የስዊድን ጋዜጠኞች 438 ቀናት ታስረው ቢፈቱም በጸረ አሸባሪነት ሕጉ 11ዓመት ተፈርዶባቸው እንደነበር በመግለጽ የጋራ ንቅናቄው ዋና ዳይሬክተር የኢህአዴግን የጭከና አገዛዝ ሊዘነጋ የማይገባ መሆኑን ለስዊድኑ ባለሃብት አስገንዝበዋል፡፡
ኩባንያቸው ሽርክና የሚያደርግባቸው ኤፈርትና የአላሙዲን ድርጅቶች የሰራተኛ መብቶችን በመርገጥ፣ የነዋሪዎችን የመኖሪያ ቦታ በግዳጅ በመንጠቅ፣ የዜጎችን ጉልበት ያለ አግባብ በመበዝበዝ፣ በሙስና የተጨማለቀና አድሏዊ አሰራር በመከተል፣ ወዘተ ተነግሮ የማያልቅ ግፍ የፈጸሙና እስካሁንም እየፈጸሙ ያሉ በመሆናቸው በተለይ ለሴቶች “የሥራ ዕድል” ይከፍታል የተባለው የኩባንያቸው ኢንቨስትመንት በምስኪን እና ደጋፊ አልባ ኢትዮጵያውያን ደም የዓለምን ሕዝብ የዲዛይነር ጨርቃጨርቅ ሳይሆን “የደም ከፈን” ለማልበስ መዘጋጀቱ ሊያስቡበትና ሊጠነቀቁበት የሚገባ ጉዳይ መሆኑን በጥብቅ በማሳሰብ የጋራ ንቅናቄው ዋና ዳይሬክተር ኦባንግ ሜቶ ደብዳቤያቸውን አጠናቀዋል፡፡
የደብዳቤው ሙሉ ቃል ከዚህ በታች ይነበባል፡፡

 Open Letter to Mr. Karl Johan Persson, Winner of 2014 Fairness Award Faces Significant Challenges in Partnering with Autocratic and Corrupt Ethiopian Government-Controlled Businesses
Head Office
H & M Hennes & Mauritz AB
Mäster Samuelsgatan 46A
SE-106 38 Stockholm
SWEDEN
Dear Mr. Karl Johan Persson,
On behalf of the Solidarity Movement for a New Ethiopia (SMNE) and the Ethiopian people we represent, I extend my warmest congratulations regarding the upcoming event at the Historic Howard Theatre in Washington D.C. on November 24, 2014 when you will receive the 2014 Fairness Award given by the Global Fairness Initiative (GFI) along with Mr. Robert B. Zoellick, former president of the World Bank Group (2007-2012) and Ms. Nani Zulminarni, Founder of Perempuan Kepala Keluarga (PEKKA), Indonesia.
This is no small accomplishment. According to the Fairness Award website, this award honors “exceptional leaders whose work and life have opened opportunity and access for poor and marginalized communities. By honoring these outstanding individuals, GFI hopes to inspire a new generation of leaders to dedicate themselves to economic justice, fairness, and equality.”[i] As a Swedish businessman, and President and CEO of one of the largest global fashion retailers, H&M Hennes & Mauritz AB, we can see how you have combined value-based business practices with great success.
The reason for this letter is to express our deep concerns regarding a recently announced business venture H&M is planning in Ethiopia. H&M, with venture capital provided through a Swedish State-run group, Swedfund[ii], has announced a decision to invest in cotton projects within Ethiopia. Reportedly, it will involve partnering with five different companies in Ethiopia, three of which are members of the business conglomerate, EFFORT, which is essentially owned by the Tigrayan Peoples’ Liberation Front (TPLF), the controlling party of the Ethiopian Peoples’ Revolutionary Democratic Front (EPRDF). Although the EPRDF is said to be a coalition government representing four of the nine ethnic-based regions of Ethiopia, the TPLF is recognized to be in charge. In other words, Ethiopia, with 86 different ethnic groups, is ruled by an ethnic-based minority party making up only 6% of the population. This has been the case since 1991.
The fourth company is owned by Saudi Arabian-Ethiopian businessman and billionaire, Sheik Mohammed al Amoudi, who is known as the right hand of the TPLF/EPRDF government. He has profited immensely from that association and in doing so, has been complicit in violating the rights of other Ethiopians. The identity of the fifth company is not yet known.
For your information, I am the Executive Director of the SMNE, a non-violent, non-political, grassroots social justice movement of diverse Ethiopians; committed to bringing truth, justice, freedom, equality, reconciliation, accountability and respect for human and civil rights to the people of Ethiopia and beyond. The SMNE was founded to build a better future for the people and is based on the belief that the future well being of our global society rests in the hands of those among us who can put “humanity before ethnicity,” or any other distinctions that divide and dehumanize other human beings from ourselves; inspiring us to care about these “others;” not only because of the intrinsic God-given value of each life, but also because “none of us will be free until all are free.”
In regards to H&M’s business interests in Ethiopia, we want to make it clear that the SMNE strongly supports business development, partnerships, and private and foreign investment in the country, believing that if Ethiopians are going to more widely prosper and increase food security to its growing population, a strong, market-driven economy is essential; however, what exists today is crony capitalism, the exploitation of the land, national assets, and resources of Ethiopians, and a brutal crackdown on the human and civil rights of the majority.
After reviewing the stated values and goals of H&M and Swedfund, which strongly affirm economic justice, fairness, respect, ethical behavior, inclusion, embracing diversity, a commitment to the protection of human rights, a zero tolerance policy on corruption—including bribery, gifts, and favors, integrity, transparency, honesty, equality, avoidance of conflicts of interest, following the law at all times, and striving for sustainability, we are in full agreement with them.
We believe H&M and Swedfund can provide an excellent model for doing mutually beneficial business in Ethiopia. However, we want to strongly caution H&M and Swedfund that the business climate is inseparable from the complete domination of the current corrupt regime and their friends and cronies. As the winner of the Fairness Award and as a business with high ethical standards, you will face significant challenges in partnering with Ethiopian government-controlled businesses. We believe it is critically important to your long-term success to know this in advance. Companies of high repute can unwittingly damage their reputations by acts of their partners. 
For example, in December 2003, Ethiopian National Defense Forces, along with militia’s they equipped, targeted my own indigenous ethnic group, the Anuak, massacring 424 of the most educated leaders within three days. Over the next several years, nearly two thousand others were killed, many others were beaten, arrested and tortured, thousands more fled to other countries. Much of the limited infrastructure in this marginalized Gambella region of southwestern Ethiopia was destroyed. The goal was to eliminate resistance to the extraction of possible oil reserves in the region. None was found, but companies involved in that effort were complicit in turning a blind eye to what was going on.
In Sierra Leone, the same thing happened in the extraction of diamonds, creating the name, blood diamondsWe seek to warn you of the risk of association with the TPLF/EPRDF regime, known for its ruthless treatment of its people so the legacy of H&M will not be associated with the blood and suffering of the Ethiopian people as these examples point out. This is a ethnic apartheid regime that does not care about the well being of all its own people. As a result, your goal of creating a business that benefits both the people of Ethiopia and H&M; that reduces poverty, enfranchises informal communities and advances human rights and livelihoods, as stated as GFI’s mission goal, will be challenged at every juncture for those doing business in Ethiopia under the egocentric control of this regime. This will be keenly felt by those, like yourself, who has a proven track-record of high standards in regards to business practice.
The only access into the economic structures of Ethiopia comes through close association and loyalty to the TPLF/EPRDF. All others are excluded, including the majority of people of Ethiopia. The impressive double-digit economic growth figures claimed by the Ethiopian government are not only questionable, but to the degree there is growth, that growth has gone into the pockets of the TPLF/EPRDF elite. Additionally, massive amounts of illicit capital leakage have ensured little improvement in the quality of life for the people.
Working in Ethiopia will present enormous challenges to H&M. I am not simply talking about the lack of infrastructure—roads, transportation, electricity, communication technology and even running water; neither are we talking about the challenges of undeveloped land, the abundance or lack of water, navigating through a maze of unfamiliar bureaucracy, or adjusting to working in a country of many different cultures, languages and geographical differences. Instead, I am talking about a conflict of values when H&M attempts to work with a regime whose goals, objectives and practices are in complete contradiction to most every ideal espoused by H&M—despite any deceptive rhetoric you might hear to the contrary.
The Public Image of Ethiopia versus the Ethiopia known by Ethiopians:
As a social justice organization that cares for the well being of the Ethiopian people, our concern is that the partners H&M has chosen are part of an autocratic regime representing the interests of a small minority at the top, most all coming from one ethnicity which does not even represent many of their own people. In the last flawed election, the highly unpopular TPLF/EPRDF party claimed to capture 99.6% of the total vote. Only one of the 547 seats in Parliament was taken by an opposition member. That member is allowed only 3 minutes of debate on any issue. As the next national election in May of 2015 looms ahead, the ruling regime has eliminated any political space. People are denied freedom of expression, freedom of association, and freedom of assembly.
Civil society has been decimated by using a law, the Charities and Societies Proclamation[iii] (CSO) which has closed over 2,600 civic organizations within Ethiopia. Those that currently exist are arms of the regime. The CSO law includes serious criminal consequences for any who advance human rights or rights for children, for women, or for the disabled if the organization has received over 10% of its funding from foreign sources. Similarly, it outlaws conflict resolution between ethnicities or religious groups or democratic advancement under the same criteria.
All sectors of society are controlled by the ruling party. (Please see link for examples.)This includes the media, public and private institutions, the military, federal and local security and police, the justice system, the educational system, the financial system—including access to loans, access to business opportunities, customs, taxes, and government jobs. Entry into any opportunity is blocked unless the doors are opened based on ethnicity (TPLF-Tigre), party membership (EPRDF) and loyalty to the ruling party. Human rights organizations have documented the politicization of humanitarian aid and services. This all has caused significant resentment and increasing tensions between the majority and the TPLF/EPRDF. Access to the Internet is controlled and websites are blocked. Landline phones and mobile phone usage is among the lowest in all of Africa due to a fear of what communication and technology might incite within its disenfranchised and repressed population.
Ethiopian laws are used to repress resistance rather than to protect the people. For example an anti-terrorism law, enacted in 2009, has been used to criminalize dissent, leading to Ethiopia being the second highest jailer of journalists in Africa, only topped by its neighbor, Eritrea. Numbers of Ethiopia’s most courageous voices of freedom languish behind bars, many victims of torture. Think of the arrest and long detention (438 days) oftwo Swedish journalists, Martin Schibbye and Johan Persson who were sentenced under the anti-terrorism law to 11 years in prison for documenting human rights abuses.
We realize you understand the repression of information and criminalization of journalists who report the truth due to H&M’s substantial donations to Civil Rights Defenders, a non-profit to uphold the human rights of people across the world. This organization wrote a letter to Prime Minister Hailemariam Desalegn regarding the recent jailing of Zone9 bloggers. One of those bloggers, Soleyana Shimeles, who was charged in absentia, was recently a guest of the SMNE at a forum we held in Washington D.C., Breaking the Cycle of Dysfunction in Ethiopian Institutions.
The ethnic apartheid regime of TPLF/EPRDF is also well known for its widespread, serial human rights abuses, its displacement of indigenous people from their land without consultation or compensation, and their absolute impunity from the courts they control for crimes committed. For example, Ethiopia has become a destination for those wanting to lease cheap agricultural land with access to water under long-term contracts. The people who live on the land are described in some of those contracts as impedimentsto be removedLarge scale land grabs have forced hundreds of thousands of small-scale farmers, pastoralists and villagers from land occupied by their families for centuries.
Similar evictions have been forced on city-dwellers throughout the country. When they resist, people have been intimidated, harassed, beaten, raped, arrested, disappeared or killed. Many have fled to refugee camps outside the country.
The TPLF/EPRDF government promised to resettle the displaced people in a villagization project where improved services would be available, but in reality this usually meant the people would have to build their own shelters, find new sources of water—often further away, clear land and replant crops on less fertile land and not find any new or improved services. Poverty and insecurity has increased and many of these people, who used to be self-sufficient, now must depend on food aid.
Our concerns:
  1. Doing business with members of the oppressive TPLF/EPRDF party will further empower and legitimize them, undermining the struggle of the people for freedom, justice and equality.
  2. No safeguards exist, other than empty rhetoric, which will protect the people, many of the most vulnerable; neither are there safeguards in place to protect the environment, already seriously affected, from the TPLF/EPRDF’s abuses, especially in regions where the people have no voice.
  3. This is a country where there is no transparency or accountability. The justice system is controlled from the federal level to the local level by the TPLF/EPRDF. It is used to reward friends of the regime and to fine, charge or impose difficult regulations or corruption charges on individuals and businesses that do not comply or who speak unfavorably towards the regime.
  4. EFFORT businesses account for some 90% of all businesses in Ethiopia.
  5. Sheik Mohammed al Amoudi, owner of Saudi Star Farm in Gambella, is leasing indigenous land to grow rice, most of it for export to Saudi Arabia.  Heavy use of water for irrigation is having an impact down river. Human rights abuses were inflicted in order to force the local people from the land.  Much of the land was forested, leading to clearing it of valuable Shea trees and much more. An incident of violence did erupt on the farm in 2013 between workers and the local people.
  6. A new anti-corruption law is being proposed that may act similarly to the anti-terrorism law in criminalizing any behavior by officials and companies, Ethiopian or foreign, who do not conform to TPLF/EPRDF expectations. This is a regime prone to changing the rules according to their self-serving needs. There is little recourse for outside companies and investors who are in conflict with the TPLF/EPRDF. It is to the regime’s advantage to engage a major company like H&M so they may lay out the red carpet; however, you may also be expected to conform to business practices that are unacceptable to you. Doing business with members of EFFORT is comparable to doing business with an unpredictable authoritarian regime where non-compliance may bring unfair charges or decisions. You are a company with strong values and an excellent reputation. Even though H&M may be willing to risk your capital, you may need to think twice before working with the TPLF/EPRDF, which may put your good reputation at risk.
We in the SMNE, with the help of the people, hope to correct these unfavorable business conditions through meaningful reforms, the restoration of justice and through reconciliation in order to build a more inclusive society for the people of Ethiopia.
If you want to invest in Ethiopia, we would welcome you, but urge you to look for long-term, sustainable partnerships where the rights and livelihoods of the people are upheld and where H&M can bring an outstanding model of how to do ethical, inclusive and profitable business in Ethiopia. This would be a real win-win solution for all of us!
If you do choose to go forward with your present plans, we genuinely hope that honorable companies like H&M will be a force for change for the common good of the people in countries of repression like Ethiopia—for our humanity has no boundaries. That means refusing to overlook the injustice; standing strong and firm in upholding all your values to the great benefit of the voiceless.
Please feel free to contact me should you have further questions, suggestions or comments.
Sincerely yours,
Obang Metho,
Executive Director SMNE
910- 17th St. NW, Suite 419.
Washington, DC 20006 USA
Phone 202 725-1616
Email: obang@solidaritymovement.org
Website: www.solidaritymovement.org

[ii] Swedfund, owned by the Swedish state, provides risk capital, expertise and financial support for investments in the emerging markets of Africa, Asia, Latin America and Eastern Europe. Our mission is poverty reduction through sustainable business, contributing to economic and environmental development as well as a positive impact to society. Since 1979 Swedfund has been engaged as an active, responsible and long-term investor in more than 230 companies in our countries of operation.
[iii] A repressive 2009 law against civil society, the Charities and Societies Proclamation now prohibits any organization that receives more than 10% of its budget from foreign sources from (a) advancing human and democratic rights, (b) promoting equality of nations, nationalities, peoples, gender and religion, (c) promoting the rights of the disabled and children, (d) promoting conflict resolution or reconciliation and, (e) promoting the efficiency of justice and law enforcement services. This has meant the closure of most every independent civic organization. In their place, the regime has created pseudo-organizations controlled by the regime, oftentimes appearing legitimate to outsiders. The law carries harsh criminal penalties for violators. It is used for political purposes and has paralyzed civil society. In its place, look-alike pseudo-institutions have sprung up, all created and controlled by the government.
Other articles:
source (http://www.goolgule.com)

Sunday, November 23, 2014

ታሪክን ማደብዝዝም ማጥፋትም አይቻልም!

በአለማችን በተለይ አፍሪካ ዉስጥ የአገርን ብሄራዊ ኃብት የሚዘርፉ፤የህዝብን መብት የሚረግጡና አገርን እነሱ ባሰኛቸዉ አቅጣጫ ብቻ ይዘዉ የሚነጉዱ አያሌ ፈላጭ ቆራጭ መንግስታት አሉ። እነዚህ ህዝብን የሚበድሉ መንግስታት ሁሉም በጥቅሉ አምባገነን ይባሉ እንጂ በመካከላቸዉ ጎላ ብሎ የሚታይ ትልቅ ልዩነት አለ። ሀኖም የቱንም ያክል ልዩነት ቢኖርም እንደ ዘረኞቹ የወያኔ መሪዎች እንመራዋለን የሚሉትን ህዝብ የሚንቁና የኛ ነዉ የሚሉትን አገር የሚጠሉ አምባገነን መንግስታት የሉም፤ በታሪክም ኖረዉ አያዉቁም። አምባገነን መንግስታት የስልጣን ዘመናቸዉን ለማራዘምና ከስልጣን ጋር ተያይዞ የሚመጣዉን ክብር፤ ዝናና ጥቅማ ጥቅም እንዳይቋረጥ ሲሉ የሚቃወማቸዉንና ለስልጣን ዘመናቸዉ አደጋ ነዉ የሚሉትን ሁሉ ያስራሉ፤ ይደበድባሉ ወይም ይገድላሉ። እነዚህን ነገሮች የወያኔ መሪዎችም ያደርጋሉ፤ ነገር ግን በወያኔና በሌሎቹ አምባገነን አገዛዞች መካክል እጅግ በጣም ትልቅ ልዩነት አለ። ለምሳሌ ወያኔዎች ዘረኛ አምባገነኖች ናቸዉ፤ የወያኔ መሪዎች ኢትዮጵያን እንደ ጥገት ላም አንጂ እንደ አገራቸዉ አይመለከቱም። ከዚህ በተጨማሪ ኢትዮጵያን፤ ህዝቧንና ታሪኳን ይንቃሉ፤ ያንኳስሳሉ።
ባለፉት አምስትና ስድስት አመታት በግልጽ እንደተመለከትነዉ የወያኔ መሪዎች የኢትዮጵያን ገበሬ ከመሬቱ አፋናቅለዉ ለምለም መሬቱን ለባዕዳንና ለህወሓት የጦር መኮንኖች ሰጥተዋል። መሬቴንና ቤቴን አልለቅም ብሎ የተቀናቀናቸዉን ደግሞ በጅምላ ገድለዋል። በከተሞች ዉስጥም ከተሜዉን ምንም ካሳ ሳይከፍሉት ዕድሜ ልኩን ከኖረበት ቤቱ እያፈናቀሉ ከነቤተሰቡ ሜዳ ላይ ጥለዉት መሬቱን ባለኃብት ለሚሏቸዉ የወያኔ ባለሟሎች ሰጥተዋል። በአጠቃላይ የወያኔ መሪዎች በኢትዮጵያ አንድነት፤ በታሪኳና በህዝቧ ላይ እንዲህ ነዉ ተብሎ ለመናገር የሚዳግት ትልቅ በደል ፈጽመዋል። ዘረኞቹ የወያኔ መሪዎች በእናት አገራችን ላይ ያደረሱት በደል ተዘርዝሮ የሚያልቅ አይደለምና ዛሬ ወደዚያ ዝርዝር ዉስጥ አንገባም፤ ዛሬ ትኩረት የምንሰጠዉ ወያኔ ደግሞ ደጋግሞ ከዘመተባቸዉና ሙሉ ኃይሉን ካሳረፈባቸዉ የአገራችን እሴቶች አንዱ ታሪካችን ነዉና የዛሬዉ ቆይታችን በዚሁ በታሪካችን አካባቢ ይሆናል።
ታሪክ በአንድ አገር ዉስጥ እያንዳንዱ ትዉልድ ከሱ የቀደመዉ ትዉልድ በግል፤ በቡድንና በማህበረሰብ ደረጃ የተጓዘበትን መንገድ ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ካለፈዉ የምንማርበትና የወደፊቱን ጉዟችንን ለመጀመር በመረጃነት የሚያገለግለንን እዉቀት የምናገኝበት የጥበብ ድርሳን ነዉ። የማንም አገር ታሪክ ዉብ ሆኖ የሚያምርና የማያምር ሁለት ገጽታዎች አሉት፤ የማያምረንን የታሪክ ጠባሳ ወደ ኋላ ሄደን ማከም በፍጹም እንደማንችል ሁሉ የወደፊቱን ታሪካችንንም የብዙ ማህበረሰባዊ መስተጋብሮች ዉጤት ነዉና ያሰኘንን ቅርጽና ይዘት ልንሰጠዉ አንችልም። የታሪክ ዋናዉና ትልቁ ቁም ነገር የታሪኩ ባለቤት የሆነዉ ማህብረሰብ እራሱን ወደ ኋላም ወደ ፊትም የሚመለትበት መስኮት መሆኑ ነዉ። ምንም አይነት ታሪክ የሌለዉ ህብረተሰብ የለም፤ ካለም ከየት አንደመጣና ወዴት አንደሚሄድም አያዉቅም።
አገራችን ኢትዮጵያ ረጂምና ጥንታዊ ታሪክ ካላቸዉ ጥቂት አገሮች ዉስጥ አንዷ ናት። ይህ ረጂም ታሪካችን ደግሞ አንገት ቀና የሚያስደርግ የድልና የገድል ታሪክ አንደሆነ ሁሉ አንገት የሚያስደፋ የግፍና የበደል ታሪክም አለበት። የዛሬዉ ትዉልድ ኢትዮጵያዊ ካለፈዉ ታሪኩ ከበደሉም ከገድሉም ተምሮ የወደፊት አካሄዱን ከሞላጎደል መቆጣጠር የሚችል እድለኛ ትዉልድ ነዉና አባቶቹ ባቆዩለት ታሪክ ሊኮራ ይገባል። አንድ ህዝብ በታሪኩ እንዲኮራ ደግሞ ታሪኩ በተደጋጋሚ ሊነገረዉ ሊተረክለትና በጽሁም መልክትም በገፍ ሊቀርብለት ይገባል። የአገራችን የኢትዮጵያ ህዝብ ግን ለዚህ የታደለ አይደለም ፤ ምክንያቱም እንመራሀለን የሚሉት መሪዎቹ ታሪኩን የሚያንቋሽሹና የሚንቁ መሪዎች ናቸዉ።
ዘረኞቹ የወያኔ መሪዎች በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ ካደረሱትና ዛሬም በማድረስ ላይ ካሉት በደሎች አንዱና ዋነኛዉ የኢትዮጳያን ታሪክ ለባዕዳንና የታሪኩ ባለቤት ለሆነዉ የኢትዮጵያ ህዝብ አሳንሰዉና እንደ ተራ ዕቃ አቃልለዉ ማቅረባቸዉ ነዉ። የወያኔ መሪዎች አዲስ አበባን ሲቆጣጠሩ መጀመሪያ ከተናገሯቸዉ ንግግሮች አንዱ የኢትዮጵያን ህዝብ ታሪክ የመቶ አመት ታሪክ ነዉ ያሉት አስቀያሚ ንግግር ነዉ። በዚህ አባባል ላይ የጸና አቋም ካላቸዉ የወያኔ መሪዎች ዉስጥ ዛሬ በህይወት የማይገኘዉ መለስ ዜናዊና ጓደኛዉ ስብሐት ነጋ ዋና ዋናዎቹ ናቸዉ። የሚገርመዉ እነዚህ የኢትዮጵያን ታሪክ በአንድ መቶ አመት የወሰኑት ሁለት ግለሰቦች የተወለዱት የኢትዮጵያ ህዝብ የዛሬ 119 አመት በአፄ ሚኒልክ መሪነት ወራሪዉን የጣሊያን ጦር አይቀጡ ቅጣት በቀጡበት አድዋ ዉስጥ ነዉ።
ወያኔ ካለፈዉ መስከረም ወር ጀምሮ ባደበዘዘዉ ቁጥር እያሸበረቀ ያሰቸገረዉን የኢትዮጵያ ታሪክ ለማቆሸሽ ጠባሳዉ ከትዉልድ ወደ ትዉልድ የሚተላለፍ የክፋት ስራ እየሰራ ነዉ። ኢትዮጵያን የመሰለ ባለታሪክ አገር ገድሎ ለሞተዉ ዘረኛ ሰዉ ትልቅ ማዕከል በህዝብ ገንዘብ የሚያሰሩት የወያኔ መሪዎች ማስቀመጫ ቦታ ጠፋ እያሉ አያሌ ብርቅ የሆኑ የኢትዮጵያ ታሪክ መጽሀፍትን ከወመዘክር አይወጡ በችርቻሮ እየሸጡ ነዉ። እነዚህ ወያኔ የሚሸጣቸዉ መጽሐፍት የተጻፉት በተለያዪ ዘመናት ወደ ኢትዮጵያ መጥተዉ በነበሩት የእንግሊዝ፤ የፈረንሳይ፤ የጣሊያን፤ የስፔንና የጀርመን የታሪክ ጸሐፊዎች ነዉ። ከሰሞኑ ከአዲስ አበባ የሚመጡ ዜናዎች እንደሚያመለክቱት ወያኔ በዉጭ አገር የታሪክ ጸሐፊዎች የተጻፉትን የታሪክ መጽሐፍትና ተጠረዝዉ የተቀመጡ ቆየት ያሉ ጋዜጣዎችን በርካሽ ዋጋ እየቸበቸቡ የግሮሰሪ ዕቃ መጠቅለያ አድርጓቸዋል።
ይህንን አሳፋሪ የሆነ የወያኔ የመጽሐፍ ሽያጭ እንደ ተራ ወንጀል የምናልፍ ኢትዮጵያዉያን ካለን እጅግ በጣም ተሳስተናል። ዘረኞቹ የወያኔ መሪዎች የሚሰሩትን ስራ አበክረዉ የሚያዉቁ ሰዎች ናቸዉ፤ እያሰሩ ያሉት ስራ ደግሞ ግልጽ ነዉ። ዘረኞቹ የወያኔ መሪዎች የተጻፈ ታሪካችንን ብቻ ሳይሆን እያወደሙ ያሉት ባህላችንን፤ ወጋችንንና ቅርሶቻችንን ጨምር ነዉ እንዳልነበረ ያደረጉት። ለምሳሌ በብዙ የአለም አገሮች ዉስጥ ረጂም ዕድሜ ያስቆጠሩ ህንፃዎች፤ የታሪካዊ ሰዎች መኖሪያ ቤቶችና የተለያዪ የአገር ቅርሳቅርሶች ልዩ እንክብካቤ እየተደረገላቸዉ ከዘመን ወደ ዘመን እንዲተላለፉ የደረጋል። ኢትዮጵያ ወስጥ ግን ዕድሜ ለወያኔ ከፍተና ታሪካዊ እሴት ያላቸዉ ህንፃዎች በልማት ስም እንዲፈርሱ ይደረጋል። የጀግኖችን አጽም ያረፈበት የመቃብር ቦታም በግሬደር እየተደረመሰ የንግድና የችርቻሮ ቦታ ይሆናል።
ሌለዉ ወያኔ በታሪካችን ላይ የሚያደርሰዉ ጥፋት ታሪካችንን እንዳንማርና የታሪክ ተማራማሪዎቻችን በጥንታዊ ታሪካችን ላይ ምርምር እንዳያደርጉ እጅና እግራቸዉን ማሰሩ ነዉ። ለምሳሌ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ዉስጥ የሚገኛዉ የታሪክ ዲፓርትመንት የኢትዮጵያን ታሪክ ማስተማር ብቻ ሳይሆን ታሪካችንን ከተለያየ አቅጣጫ በማጥናትና ምርምር በማድረግ ለታሪካችን መበልጸግ ከፍተኛ አስተዋጽኦ የሚያደርግ ተቋም ነዉ። ሆኖም ይህ በተለያዪ መንግስታት ዉስጥ ለረጂም አመታት ትልቅ ስራ ሲሰራ የቆየዉ የታሪክ ዲፓርትመንት ዛሬ አለ ተብሎ መናገር በማይቻልበት አሳዛኝ ሁኔታ ላይ ይገኛል። ይህ ሁሉ የሚያሳየን ወያኔ የቀድሞ ታሪካችንን እያወደመ የሚቀጥለዉን ታሪካችንን ደግሞ በራሱ አቅጣጫ እያጣመመ በመጻፍ ላይ መሆኑን ነዉ።
ዘረኞቹ የወያኔ መሪዎች የኢትዮጵያን ታሪክ አስመልክቶ በአንድ በኩል የኢትዮጵያ ታሪክ የተጻፈዉ በተወሰኑ ሰዎች ከአንድ አቅጣጫ ብቻ ነዉ ሲሉ በሌላ በኩል ደግሞ የረጂሙን ዘመን የአገራችን የኢትዮጵያ ታሪክ ከአንድ ሞቶ አመታ የበለጠ ዕድሜ የለዉም እያሉ በተደጋጋሚ ተናግረዋል። ዛሬ በገፍ ለጨረታ ያቀረቧቸዉ የታሪክ መጽሐፍት ቁልጭ አድርገዉ የሚናገሩት ደግሞ ታሪካችን ከ3000 ሺ አመታት በላይ መሆኑንና የተጻፈዉም በተወሰኑ ሰዎች ብቻ ሳይሆን በተለያዪ ኢትዮጵያዉያንና የዉጭ አገር ሰዎች ጭምር መሆኑንደ ነዉ። ዛሬ ወያኔ እንደ ርካሽ ዕቃ እያወጣ የሚቸበችባቸዉ መጽሀፍት ለዚህ አሳዛኝ ዕጣ የበቁት ይህንን የወያኔ አይን ያወጣ ዉሸት ስለሚያጋልጡ ነዉ።
አገራችን ኢትዮጵያን እንወዳለን የምንል ኢትዮጵያዉያን በሙሉ ይህ በአፋችን ሁሌም የምንለዉ ቃል በተግባር የምንተረጉምበት አጋጣሚ ፊት ለፊታችን ላይ ተደቅኗል። ኢትዮጵያ አንደ ገና ዳቦ ከላይና ከታች ወያኔ ባነደደዉ ረመጥ እሳት እየተለበለበች ነዉ። ይህንን እሳት ማጥፍትና አገራችንን ከወያኔ መታደግ ካለብን ግዜዉ ነገ ሳይሆን ዛሬ ነዉ።
አያሌ ኢትዮጵያዉያን የወያኔን የመጽሐፍ ሽያጭ አስመልክቶ የወሰዱትን ቆራጥና ብልህ እርምጃ ግንቦት ሰባት የፍትህ፤ የነጻነትና፤ የዲሞክራሲ ንቅናቄ እጅግ በጣም ያደንቃል። በአዲስ አበባና በአካባቢዋ የሚገኙ አያሌ አገር ወዳድ ኢትዮጵያዉያን የአገርና የወገን ሃላፊነት ተሰምቷቸዉ ወያኔ ለጨረታ ያቀረበዉን መጽሐፍ በመግዛት የአገራቸዉን ታሪክ ለመታደግ ያደረጉት ጥረት በዋጋ ሊተመን የማይችል ትልቅ አገራዊ ስራ ነዉ። አገራችን ዛሬ ባለችበት ሁኔታ ነገ አትገኝም የሚል እምነታችን የጸና ነዉና እነዚህን የገዛችኋቸዉን መጽሀፍት በጥንቃቄ በመያዝ ሀላፊነትና የአገር አደራ ለሚሰማዉ በህዝብ የተመረጠ መንግስት አንድታስረክቡ አደራ እንላችኋለን። ከአሁን በኋላም ቢሆን የወያኔን ፀረ አገርና ፀረ ህዝብ ስራ እየተከታተላችሁ እንድታከሽፉና በሚያልፈዉ ህይወታችሁ የማያልፍ ታሪክ ሰርታችሁ ወያኔን በማሰወገዱ ዘመቻ ዉስጥ ሙሉ ተሳትፎ አንድታደርጉ አገራዊ ጥሪ እናስተላለፋለን።
source www.ginbot7.org

Saturday, November 15, 2014

Police brutally kill a mother and son in Jimma

ESAT News
November 13, 2014
Ethiopian Federal police officers stationed in Jimma, Southwest Ethiopia, have brutally   gunned down a mother and her son in the early hours of Thursday 13 November, 2014. They fired over 10 bullets after breaking into the house of the victims. The officers returned to their camp later that morning.
The residents of the area, who protested the killing, were met by another police action. According to eyewitnesses, the deceased Mrs Membere and her son, Yonas owned a hotel in Jimma town. On that fateful night, a group of Federal police officers reportedly refused to pay for the services after dinning in the hotel. Yonas reportedly said to them “are you not paying because you are servants of this government?” After leaving the hotel quietly, the police officers returned armed to gun down Yonas with five bullets in front of his own mother. They then shot his mother dead, who was pleading for her son not to be killed.
A resident of the town said to ESAT that although the residents of the town took to the streets protesting the brutal stabbing of a young man named Anwar in the town, they were returned back by police. Kennedy Mengesha, a government employee was also killed one month before by the Federal police in the town.
The residents say the actions of the federal Police forces are beyond what they can take.
ESAT’s effort to speak to police in Jimma was unsuccessful.
source ESAT  News

Saturday, November 8, 2014

እ.ኤ.አ በ1984 የተከሰተው የኢትዮጵያ ታላቁ ረኃብ፡ ህወሀት አሁንም ቢሆን ለመስረቅ እና ለመዝረፍ ፈቃድ አለው

ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም
ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ
TPLF Cash.. 1984የተከሰተውየኢትዮጵያ ታላቁ ረኃብሲታወስ፡ክፍል 2
ባለፈው ሳምንት ባቀረብኩት ትችቴ (እ.ኤ.አ በ1984 የተከሰተው የኢትዮጵያ ታላቁ ረኃብ ሲታወስ፡ ክፍል1)፣ ላለፉት በርካታ ዓመታት ረኃብን በማስመልከት ሳቀርባቸው በነበሩት ትችቶች የህዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ እና አሁን በህይወት የሌለው መሪው መለስ ዜናዊ እ.ኤ.አ ከ1991 ጀምሮ በኢትዮጵያ ውስጥ ምንም ዓይነት ረኃብ የለም በማለት ሙልጭ አድርገው በመካድ ሲያደርጉት የነበረውን ተራ ቅጥፈት በማጋለጥ በተጨባጭ መረጃዎች ላይ በመመስረት ስሞግት የቆየሁባቸውን ዋና ዋና ጭብጦች በማካተት ክለሳ ማድረጌ ይታወሳል፡፡ መለስ እና ጓደኞቹ ከዓለም አቀፍ ለጋሾች እና አበዳሪ ድርጅቶች ጋር በመሞዳሞድ ለረኃብ ስያሜ የተለያዩ የማስመሰያ እና የማደናገሪያ ስሞችን በመስጠት በኢትዮጵያ የተለያዩ ክፍሎች ከሁለት አስርት ዓመታት በላይ ተንሰራፍቶ ህዝብን ሲፈጅ እና ሲያሰቃይ የቆየውን ረኃብ በመደበቅ በሀገሪቱ ውስጥ በየትኛውም ቦታ ቢሆን እንደሌለ አድርገው በረኃብ ሲሰቃዩ በቆዩት እና በረኃቡ ምክንያት ባለቁት ወገኖቻችን ላይ ሸፍጥ ሲሰሩ ቆይተዋል፡፡ ለዚህም አጽንኦ በመስጠት በኢትዮጵያ ያለው ረኃብ የፈለገውን ያህል በማስመሰያ እና በማደናገሪያ ቃላት እና ሀረጎች ተሸፋፍኖ እና ታጅቦ ቢቀርብም ያው አሁንም ቢሆን ረኃብ ነው! በማለት ማጠቃለያ መስጠቴ የሚታወስ ነው፡፡
በዚህ በክፍል ሁለት ትችቴ ደግሞ እ.ኤ.አ ከ1984 – 85 ድረስ ህወሀት በተከሰተው በታላቁ ረኃብ ምክንያት የረኃብ ሰለባ ለሆኑት ወገኖች ነብስ ማዳኛ ለሰብአዊ እርዳታ የመጣውን እርዳታ ለጦር መሳሪያ ግዥ እና ለግል ጥቅም ለማዋል ሲያደርገው የነበረውን የዥዋዥዌ ጨዋታ ለመዳሰስ ሞክሪያለሁ፡፡ በመጀመሪያ ጊዜ እ.ኤ.አ ሜይ 2011 በሁፊንግተን ፖስት “ለመስረቅ ፈቃድ ማግኘት” በሚል ርዕስ ባቀረብኩት የመጀመሪያ ትችት ህወሀት የሰረቀ መሆኑን ከሁለት የቀድሞ የህወሀት የአመራር አባላት ጋር የተደረገን ቃለ መጠይቅ ዋቢ በማድረግ ለሰብአዊ እርዳታ ተብሎ የመጣን የእርዳታ እህል ከታለመለት ዓላማ ውጭ ህወሀት ለመሳሪያ መግዣ እና ለሌላ ለግል ጥቅሙ ያዋለ መሆኑን በማጋለጥ ትችት አቅርቤ ነበር፡፡ ይህ ቡድን እ.ኤ.አ በ1984 ጫካ በነበረበት ጊዜ የጀመረው የዓለም አቀፍ የእርዳታ ስርቆት፣ ዘረፋ እና ሙስና የማይላቀቁት መናጢ አመል ሆኖበት አሁንም እስካለንበት ጊዜ እስከ 2014 ድረስ በተለያየ እና በተወሳሰበ መልኩ ቀጥሎ ይገኛል፡፡
“አሊ ባባ”፣ መለስ እና 40 የህወሀት/ማረት (TPLF/REST) የ1984- 85 የእርዳታ እህል እና ዶላር ሌቦች እና ዘራፊዎች፣
እ.ኤ.አ በ1984 – 85 በሰሜን ኢትዮጵያ ተከስቶ በነበረው አስከፊ እና አሰቃቂ ረኃብ ምክንያት የረኃቡ ሰለባ ለሆኑ ህዝቦች በሚል ከዓለም አቀፉ ህብረተሰብ ሩብ ሚሊዮን ዶላር ተሰብስቦ ነበር፡፡ ያ ረኃብ እጅግ በጣም አስከፊ ገጽታ ያለው እና ባልተጠበቀ መልኩ የተከሰተ ነበር፡፡ እ.ኤ.አ በ1984 የትግራይን አካባቢ የጎበኘው የቢቢሲው ጋዜጠኛ ሚካኤል ቡርክ የረኃቡን አስከፊነት እንደሚከተለው ገልጾት ነበር፣ “የ20ኛው ክፍለ ዘመን የመጽሐፍ ቅዱስ ረኃብ“ እና “በመሬት ላይ ለሲኦል የቀረበ ነገር“፡፡
እ.ኤ.አ በ1984 – 85 በአማጺያን ኃይሎች እንቅስቃሴ እና በደርግ ወታደራዊ አምባገነን መንግስት የአውሮፕላን ድብደባ ምክንያት በትግራይ ክልል እና በሌሎች የሰሜን ኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች የአስቸኳይ ጊዜ እርዳታን በተለመደው የእርዳታ አሰጣጥ ሁኔታ ማቅረብ እጅግ በጣም አስቸጋሪ ነበር፡፡ በርካታ የዓለም አቀፍ መንግስታዊ ያልሆኑ ለጋሽ ድርጅቶች እርዳታውን አማጺያን ቡድኖች በተቆጣጠሯቸው አካባቢዎች በአስከፊው ረኃብ የጥቃት ሰለባ ለሆኑት ወገኖች ፈጣን በሆነ መልኩ የህይወት አድን እርዳታውን ለማድረስ ሌሎች ተለዋጭ መንገዶችን እና ዘዴዎችን ማግኘት ነበረባቸው፡፡
እንደ አማራጭ በመውሰድ በርካታዎቹ መንግስታዊ ያልሆኑ እርዳታ ሰጭ ድርጅቶች ለረኃብ ጥቃት ሰለባ ለሆኑ ወገኖች በቀላሉ ምግብ ማድረስ እንዲቻል በማሰብ በምስራቃዊ የሱዳን ጠረፍ በትግራይ ወሰን አካባቢ የማከፋፈያ ጣቢያ ከፈቱ፡፡ በሱዳን ወሰን አካባቢ በርካታ መንግስታዊ ያልሆኑ እርዳታ ሰጭ ድርጅቶች በብዛት መከማቸት እና ገንዘብ በማዋጣት እረገድ ይደረጉ በነበሩት የህዝብ ግንኙነት ጥረቶች ምክንያት ለህወሀት አመራሮች እና ለአማጺያኑ ወታደሮቻቸው ትርፋማ የሆነ የንግድ አጋጣሚ ፈጠረላቸው፡፡ አማጺያኑ እነርሱ በተቆጣጠሯቸው አካባቢዎች ጥሩ የእርዳታ ማስተላለፊያ መንገዶች እንዳሉ በማሳወቅ እና የእርዳታ እህሉንም ሆነ ሌላ ማንኛውንም ዓይነት ቁሳቁስ እነርሱ ማከፋፈል ቢችሉ ስራው የተሳካ እንደሚሆን እና ለዘለቄታው ውጤታማ እንደሚሆኑ መንግስታዊ ላልሆኑ ለጋሽ ድርጅቶች ሀሳብ አቀረቡ፡፡
የቀድሞው የህወሀት የገንዘብ ግምጃ ቤት ኃላፊ የነበሩት እንደ ገብረመድህን አርአያ እና የአማጺያኑ መስራች የነበሩት እንደ ዶ/ር አረጋዊ በርሄ ገለጻ ከሆነ የህወሀት ቁልፍ መሪዎች መለስ ዜናዊን ጨምሮ በዓለም አቀፍ የረኃብ እርዳታ ሰጭ ድርጅቶች አማካይነት በረኃቡ ሰለባ ለሆኑት ተብሎ የተመደበውን በሚሊዮን ዶላር የሚቆጠር የእርዳታ እህል የማጭበርበሪያ ስልት ነድፈው ከተያዘለት ዓላማ ውጭ ለጦር መሳሪያ መግዣ እና ለግል ጥቅማቸው አዋሉ፡፡ ገብረ መድህን እና አረጋዊ ግልጽ እንዳደረጉት መለስ እና ቁንጮ ካድሬዎቹ አንድ የማጭበርበሪያ ዕቅድ በመንደፍ የሰብአዊ እርዳታ የሚያቀርብ ድርጅት በሚል ማህበረ ረዲኤት ትግራይ/ማረት (Relief Society of Tigray/REST) ተብሎ የሚጠራ የማስመሰያ እርዳታ ሰጭ ድርጅት አቋቋሙ፡፡ ውስጡ ለቄስ ነው እና በአንድ ወቅት አሁን በህይወት የሌለው መለስ ዜናዊ እንዳለው የዚህ ድርጅት ልብ እንደ ፈጣን ሎተሪ ተፍቆ ቢታይ እንደ ስሙ እርዳታ ሰጭ ድርጅት እንዲሁም ለሰው ልጆች ክብር በፍቅር ተቃጥሎ ህይወትን ለማዳን ከልቡ የሚሰራ ርህራሄን የተላበሰ እውነተኛ ሰብአዊ ድርጅት ሳይሆን ሌባ፣ ዘራፊ እና በቅጥፈት የተሞላ የማፊያ ድርጅት ሆኖ ይገኛል፡፡ በዚያን ወቅት የህወሀት አመራሮች ማረት ከህወሀት ወታደራዊ ክንፍ ጋር ፈጽሞ ግንኙነት የሌለው እና የተለዬ ሀቀኛ የእርዳታ ሰጭ/አከፋፋይ ለጋሽ ድርጅት እንደሆነ በማስመሰል የተለያዩ ዓለም አቀፋዊ የእርዳታ ሰጭ ድርጅቶችን ለማሳመን ሌት ከቀን ጥረት አደረጉ፡፡ እውነታው እንደሚያሳየው በእርግጥ ማረት እና ህወሀት የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታዎች ናቸው፡፡
በአሁኑ ጊዜ በስደት በውጭ ሀገር የሚኖሩት ዶ/ር አረጋዊ በርሄ የህወሀትን የረቀቀ የእርዳታ ማጭበርበር ባህሪ ለቢቢሲ ጋዜጠኛ ለማርቲን ፕላውት እንዲህ በማለት ገልጸው ነበር፣
“… አንዳንድ ጊዜ የእርዳታን ገንዘብ እንደ ሁለተኛ አማራጭ በመውሰድ የጦር መሳሪያ እንገዛበት ነበር፡፡ ገንዘቡ ካለህ መካከለኛው ምስራቅ በመምጣት መሳሪያ መግዛት ትችላለህ፡፡ ስለሆነም የተወሰነውን ገንዘብ ለመሳሪያ ግዥ በማዋል እንጠቀምበት ነበር፡፡ ይህንን ማረት እየተባለ በአህጽሮ ቃል የሚጠራውን ድርጅት ታውቀዋለህ፣ ሲተነተን ማህበረ ረድኤት ትግራይ ማለት ነው፡፡ የህወሀት የሰብአዊ እርዳታ ክንፍ ነው፣ እና በማረት ስም የእርዳታ ገንዘብ ወደ ህወሀት ይመጣ ነበር፡፡ ከዚያ ይህንን የእርዳታ ገንዘብ ካገኘህ በኋላ ለእርዳታ፣ ለጦር ግንባር ወይም ደግሞ ለጦር መሳሪያ ግዥ፣ ለመድኃኒት፣ ወዘተ በሚል በጀት ታዘጋጃለህ፡፡ የእርዳታን ገንዘብ ትግሉን ለማስቀጠል እንጠቀምበት ነበር ለማለት እችላለሁ፡፡
ከዚህም በላይ በብዙ ሚሊዮን ስለሚቆጠር ዶላር ጉዳይ እንነጋገር ነበር፡፡ ለዚህ አንድ ተጨባጭነት ያለው ምሳሌ ልነግርህ እችላለሁ፡፡ እ.ኤ.አ በ1985 ትግራይ አሰቃቂ በሆነ ረኃብ በተጠቃች ጊዜ የእርዳታ ገንዘብ በማረት በኩል አድርጎ ወደ ህወሀት ይጎርፍ ነበር፡፡ ስለሆነም ከሞላ ጎደል አንድ ዓይነት ዓላማ ያላቸው እና ምንም ዓይነት ልዩነት የሌላቸው ማርክሲስት ሌኒኒስት ሊግ ትግራይ/ ማሌሊት/Marxist Leninist League of Tigrai (MLLT) እና የህወሀት አመራሮች 100 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ለተለያዩ ተግባራት እንዲውል መመደብ ነበረባቸው፡፡ በዚህም መሰረት መለስ ዜናዊ ከዚህ ገንዘብ ውስጥ 50 በመቶ የሚሆነው ለህወሀት እንቅስቃሴዎች፣ 45 በመቶ የሚሆነው ለማሌሊት ማደራጃ እና 5 በመቶ የሚሆነው ብቻ በረኃብ ሰለባ ለወደቁት ተረጅዎች መዋል አለበት የሚል ሀሳብ አቅርቦ እንደነበር አስታውሳለሁ…እነዚህን ሁለት ሰዎች (አርዓያ ገብረመድህን እና ተክለወይነ አሰፋ) አውቃቸዋለሁ፡፡ የህወሀት ተዋጊዎች ናቸው፡፡ አንዱ እራሱን ነጋዴ በማስመሰል ይቀርባል፡፡ ሁለተኛው ደግሞ ከነጋዴው ማሽላ የሚገዛ በመምሰል ይቀርባል፡፡ ሁለቱም የህወሀት ነባር ካድሬዎች ናቸው፣ እናም ነጋዴ ለመምሰል ትወና በመተወን ላይ ናቸው፡፡ እነዚህ ሁሉ ነገሮች የሚተወኑት ገንዘቡን ለማግኘት ሲባል ነው፡፡ [በፎቶግራፉ ላይ ከላይ የሚታዩት የመንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ተወካይ የነበረው ፔርቤዲ ከመካከል ሆኖ የታሰረ ረብጣ ብር ለተወካይ ተብዬዎች ሲያስታቅፍ ነበር] እናም ይህ ዜጋ መቶ በመቶ ተታሏል፡፡”
ገብረ መድህን የዓረጋዊንን ሀሳብ ትክክለኛነት አረጋግጠዋል፡፡ ገብረ መድህን (ከላይ በስዕሉ ላይ በስተግራ በኩል ሆነው ገንዘብ ሲቆጥሩ የሚታዩት) እራሳቸው በግንባር በመቅረብ በመቶዎች እና በሺዎች የሚቆጠር ዶላር ለመለስ ዜናዊ እና እንደ እባብ ተስለክላኪው እና የህወሀት የክርስትና አባት ለሆነው ለስብሀት ነጋ በወቅቱ በእጃቸው ያስረከቡ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ ሁለቱ የህወሀት አድራጊ ፈጣሪዎች መለስ እና ስብሀት የህወሀትን የገንዘብ ፍሰት ይቆጣጠሩ ነበር፡፡ ገብረመድህን የህወሀት ዋና የገንዘብ ኃላፊ ሹም የነበረ ቢሆንም መንግስታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች በእርዳታ ስም የሚመጣውን ገንዘብ ለመለስ እና ለስብሀት ካስረከበ በኋላ ስለገንዘቡ አወጣጥ እና ከጥቅም ላይ እንዴት ሆኖ እንደሚውል እንዲያውቅ አይደረግም ነበር፡፡ ያም ሆነ ይህ ገብረመድህን ገንዘቡ በትክክል ለታለመለት ዓላማ ጉዳይ ስለመዋሉ እና አለመዋሉ ጥርጣሬ ነበረው፡፡ ሆኖም ግን የጥፋተኝነት ማስረጃው (ሁለቱን የህወሀት ካድሬዎች እና ማክስ ፔርቤዲ የተባለውን ከእንግሊዝ መንግስታዊ ያልሆኑ የእርዳታ ሰጭ ድርጅቶች መካከል ታላቅ ከሆነው የክርስቲያን እርዳታ/Christian Aid ተብሎ ከሚጠራው ተወካይ እጅ እየቆጠሩ በመረከብ በወለሉ ላይ በትልቅ ቦርሳ ውስጥ በርካታ ገንዘብ ሲያጭቁ የሚያሳየው ፎቶግራፍ) በምንም ዓይነት መልኩ ማስተባበያ ሊቀርብበት የማይችል አስደንጋጭ ነገር ነው፡፡
የችግሩን ስፋት እና ጥልቀት እንዲሁም የረኃቡን አስከፊነት እና አሳሳቢነት መንግስታዊ ላልሆኑት እርዳታ ሰጭ ድርጅቶች በውሸት በትወና መልክ ለማሳየት ሲባል የህወሀት አመራሮች እጅግ ብዛት ያለውን የረኃብ ሰለባ ህዝብ ከትግራይ ወደ ሱዳን በማምጣት በኢትዮ-ሱዳን ሰሜናዊ የድንበር አካባቢዎች ላይ በአንድ ጀንበር ምሽት እንደ አሸን የፈሉ የእርዳታ መስጫ ጣቢያዎችን በማዘጋጀት የተረጅዎችን ቁጥር ከመጠን በላይ አበዙት፡፡ የተለያዩ ዘዴዎችን እና ስልቶችን በመጠቀም የህወሀት አመራሮች መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች በትግራይ ውስጥ በረኃብ ለተጠቃው ህዝብ የእርዳታ እጃቸውን እንዲሰነዝሩ ለማስቻል ዝርዝር የሆነ የገበያ ተውኔት በማዘጋጀት ለመድረክ እይታ አበቁ፡፡ ይህ የተደረገው ለእነርሱ በጣም ታማኝ የሆኑ የድርጅቱን ጥቂት የውስጥ አባላት በመምረጥ እና በማደራጀት የእህል ነጋዴ ሆነው እንዲቀርቡ እና መንግስታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች እርዳታ የማሰባሰብ ንግድን ማጧጧፍ ነበር፡፡
መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን የማታለሉ ጨዋታዎች ወይም ደግሞ የበለጠ ግልጽ ለማድረግ የምዕራቡን ዓለም መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች የረኃብ እርዳታ የማታለል ዕቅድ የተለያዩ መገለጫዎችን ያካተተ ነበር፡፡ በማጭበርበሩ የመጀመሪያ ደረጃ ላይ የህወሀት አመራሮች ሶስት ደረጃዎችን ያካተተ ሂደትን ተጠቅመዋል፡፡ በመጀመሪያው ደረጃ አንድ የህወሀት/ማረት የባለስልጣኖች ቡድን ህጋዊ የእህል ነጋዴዎች በመምሰል በርካታ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን ይቀርባሉ፣ እናም በረኃብ ለተጠቃው ህዝብ እርዳታ በፍጥነት እንዲደርስ በርካታ ብዛት ያለው እህል እንዲሸጥላቸው ይጠይቃሉ፡፡ በዚያን ጊዜ የህወሀት አታላዮች በመቶዎች የሚቆጠሩ ከባድ የጭነት ማምላለሻ መኪናዎች ያገኙ እና በጣም ሚስጥራዊ በሆነ መልኩ ከመሬት ውስጥ በተዘጋጀ ሰፊ ማጠራቀሚያ ከተለያዩ ምንጮች ያገኗቸውን የእርዳታ እህሎች መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን ጨምሮ ለእራሳቸው ተዋጊዎች መጠቀሚያ በሚል ያጭቁታል፡፡ እነዚህ በከባድ ሚስጥር ከመሬት ውስጥ ታጭቀው የሚገኙ የእህል ቁልሎች በእርግጠኝነት ዓላማው መንግስታዊ ላልሆኑ ድርጅቶች ለመሸጥ ነው፡፡ የህወሀት/ማረት እህል አዳዮች መንግስታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች ጋር እህልን ለመሸጥ ይደራደራሉ፣ ከዚያም ሽያጩን ያጠናቅቁ እና ከሽያጩ ያገኙትን በርካታ ገንዘብ ተሸክመው እህሉን ወደ ደበቁበት ቦታ ይመለሳሉ፡፡ ገብረመድህን እራሳቸው በዚህ እህል የመግዛት እና የመሸጥ ትወና ላይ የእህል ማደል ቀጥተኛ ተሳታፊ ነበሩ፡፡ ከዚህ አንጻር የእርሳቸውን ሚና እንዲህ በማለት በግልጽ አስቀምተውታል፣
የሙስሊም ነጋዴ እንድመስል የሙስልም ልብሶች እንድለብስ ይሰጡኝ ነበር፡፡ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች እኔን አያውቁኝም ምክንያቱም የእኔ ስም መሀመድ ነበር፡፡ ይኸ ስም የመቀየር የማጭበርበር ስራ የተደረገው መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን ለማታለል በህወሀት የበላይ አመራሮች የተዘየደ የማጭበርበሪያ ስልት ነበር፡፡ መንግስታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች በርካታ የሆነ ገንዘብ እቀበል ነበር፣ እናም የተቀበልኩት ገንዘብ ወዲያውኑ በህወሀት መሪዎች ይወሰድ ነበር፡፡ ከወሰዱት ገንዘብ ውስጥ በርካታውን የህወሀት አመራሮች በግል የሂሳብ ቁጥራቸው በምዕራብ አውሮፓ ባንኮች ያስቀምጡ ነበር፡፡ ከዚህ ገንዘብ ጥቂቱ ደግሞ ለመሳሪያ መግዣ ያውሉት ነበር፡፡ የአስከፊው ረኃብ የጥቃት ሰለባ የሆነው ተረጅው ህዝብ ግማሽ ኪሎ ግራም ያህል በቆሎ እንኳ አያገኝም ነበር፡፡ አንድ ጊዜ የእህል መግዛቱ ስራ ከተከናወነ በኋላ ሌላው የህወሀት/ማረት ቡድን ደግሞ የተገኘውን የእርዳታ እህል በትግራይ ውስጥ በተለያዩ ቦታዎች በመሄድ የማከፋፈሉን ስራ ይሰራል፡፡
በሁለተኛው ደረጃ የተዋቀረው የህወሀት/ማረት ባለስልጣኖች በሚስጥር ከመሬት ውስጥ ያከማቹትን የእህል ክምችት ድንገተኛ ፍተሻ በማድረግ ስራውን ያቀላጥፋሉ፡፡ ሆኖም ግን የእህል ማስቀመጫ መጋዘኑ በሌላ ማሳሳቻ ነገር ተሞልቶ ይቀመጣል፡፡ ገብረመድህን እንዲህ ብለው ነበር፣ “እዚያ ብትሄድ ግማሽ የሚሆነው የመጋዘኑ የእህል መያዣ ጆንያ በአሸዋ ተሞልቶ ነው የሚገኘው“ ገብረመድህን እንዳሉት ከሆነ የመንግስታዊ ያልሆኑ የእርዳታ ሰጭ ድርጅቶች ተወካይ ወደ መጋዘኑ ከመጣ በኋላ በችኮላ እና በዓይን ውጫዊ የገረፍ ገረፍ እይታ ብቻ በመመልከት የእራሱን መተማመኛ ይሰጣል፣ ከዚያም ክፍያ ፈጽሞ ወደ ሱዳን ተመልሶ በመሄድ ሌላ ተጨማሪ እህል ለመግዛት ዝግጅቱን ያደርጋል፡፡
በሶስተኛ ደረጃ የተመደበው አንድ ዓይነት ወይም ደግሞ ሌላ የህወሀት/ማረት ቡድን ወደ መንግስታዊ ያልሆኑ እርዳታ ሰጭ ድርጅቶች ይሄድ እና ወደተለያዩ የትግራይ አካባቢዎች በመውሰድ ለህዝቡ ማደል እንድንችል ሌላ ተጨማሪ እህል እንዲሸጥልን በማለት ሌላ የውሸት ማታለያ መጫወቻ ሜዳ በማዘጋጀት ጥያቄውን ለእርዳታ ሰጭ ደርጅቶቹ ያቀርባል፡፡ በዚህን ጊዜ ከእርዳታ ሰጭ ድርጅቶች የተገኘው አዲስ የእርዳታ እህል ወደተባለው ህዝብ እንዲሄድ አይደረግም፡፡ ይልቁንም ከመሬት ውስጥ ባለው መጋዘን ውስጥ ታጭቆ የሚገኘው እህል ወደ ሌሎች የትግራይ የተለያዩ ክፍሎች እንዲሄድ በማድረግ መንግስታዊ ላልሆኑት የእርዳታ ሰጭ ድርጅቶች ግን አዲሱ እና ከዚያ ተገዝቶ እንዲሰጥ የተባለውን እህል ያሰራጩ እና ያከፋፈሉ በማስመሰል የማታለል ስራቸውን በስፋት ይቀጥላሉ፡፡ የእርዳታ ሰጭ ድርጅቶች ነጻ በሆነ መልኩ የተሰጠው እርዳታ ወደ እርዳታ ፈላጊው ህዝብ ሄዶ በትክክል መከፋፈሉን የሚያረጋግጡበት ምንም ዓይነት መንገድ ስለሌላቸው ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ ለሚጓጓዘው  ተመሳሳይ የማደናገሪያ እህል ሁሉ ይከፍላሉ፡፡ በዚያ መልኩ የረቀቀ የማታለል ዘዴን በመጠቀም ህወሀት/ማረት ቀደም ሲል የነበራቸውን የእህል እና የአሸዋ ክምችት ብዙ ጊዜ መንግስታዊ ላልሆኑ ድርጅቶች ደጋግመው በመሸጥ በሚሊዮኖች የሚቆጠር ዶላር በገቢነት ይሰበስባሉ፡፡
ማርቲን ፕላውት ከቢቢሲ በሰሜን ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ በ1970ዎቹ ተከስቶ የነበረውን ረኃብ እ.ኤ.አ ማርች 2010 ባወጣው ዘገባው እ.ኤ.አ በ1985 የሲአይኤ መረጃ ያወጣውን ዋቢ በማድረግ እንዲህ የሚል መደምደሚያ ሰጥቶ ነበር፣ “ለተራቡት ወገኖች እርዳታ በሚል የሽምቅ ተዋጊዎች የሚያሰባስቡትን እርዳታ ዓለም በስፋት እያወቀው ሲመጣ እና የእርዳታው መጠንም እየጨመረ ሲመጣ ለእርዳታው ተብሎ የሚመጣው ሁሉ ሙሉ በሙሉ በሚባል መልኩ ለጦር መሳሪያ መግዣ ይውል ጀመር፡፡“ በ1980ዎቹ መጨረሻ አካባቢ ሮበርት ሁደክ የተባሉ በኢትዮጵያ የዩኤስ አሜሪካ ነባር ዲፕሎማት የህወሀት አባላት በዚያን ወቅት ለእርዳታ የሚሰጣቸውን እህል ለመሳሪያ መግዣ ያውሉ ነበር በማለት የተናገሩትን ቢቢሲ እንዳለ ቃላቸውን ወስዶ እንዲህ በማለት ዘግቦ ነበር፡፡ “አንድ ማክስ ፔቤርዲ የሚባል የእርዳታ ሰራተኛ በግንባር በመገኘት ለህወሀት/ማረት ባለስልጣኖች 500,000 ዶላር በኢትዮጵያ ገንዘብ ተቀይሮ እህል እንዲገዙበት በእጃቸው የሰጣቸው መሆኑን ተናግሯል“ በማለት ገልጸው ነበር፡፡
ገብረመድህን በጽሁፋቸው በዝርዝር ግልጽ እንዳደረጉት እ.ኤ.አ በ1984 – 85 ተከስቶ የነበረውን ታላቁን ረኃብ ሰበብ በማድረግ ህወሀት አብዛኛውን እርዳታ ለመሳሪያ መግዣ እና ለአመራሩ አባላት የግል ጥቅም አውለውታል የሚለው የመጀመሪያ ማስረጃ አሳማኝ ይመስላል (የገብረመድህንን ክፍል አንድ የአማርኛ ጽሁፍ እዚህ ጋ ይጫኑ፡፡ ለክፍል ሁለት ደግሞ እዚህ ይጫኑ)
የህወሀት የእርዳታ ስርቆት እና እርዳታውን ለሌላ ዓላማ ማዋል የሚለውን ፕሮፌሰር ሀሰን ሰይድ “መንግስታዊ ጥቃት በኢትዮጵያ፡ ሰብአዊ እርዳታ እና ሙስና“ (መነበብ ያለበት ጽሁፍ) በሚል ርዕስ ባዘጋጁት ዝርዝር እና ጥልቀት ባለው ጥናታዊ ጽሁፋቸው ውስጥ እንዲህ የሚል ማጠቃለያ ሰጥተዋል፣ “በጥናቴ ውስጥ የመረመርኳቸው ሰነዶች እና ያደርግኋቸው ቃለ መጠይቆች እንዲሁም የሰበሰብኳቸው የምስክርነት ማስረጃዎች እንደሚያረጋግጡት ለጋሽ እና እርዳታ ሰጭ ድርጅቶች ማህበረ ረድኤት ትግራይ/ማረት ከህወሀት ጋር የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታዎች መሆናቸውን እንደሚያውቁ የሚጠቁሙ መሆናቸው፣ እንደዚሁም ደግሞ የህወሀት እና የእርዳታ ሰጭ ድርጅቶች ሰራተኛ ለሰብአዊ እርዳታ ተብሎ የሚመጣ እርዳታ ለመሳሪያ ግዥ እና ለጦር ግንባር ዓላማ ይውል እንደነበር ያውቁ ነበር…“
በዚህ አሳፋሪ እና የወረደ ድርጊት ስህተት ውስጥ ተሳትፈው የነበሩት መቅንየለሾች ማስረጃዎችን ቆሻሻ በማለት ዘለፋ ከማቅረብ ውጭ በእውነተኛ መረጃ ላይ በተመሰረተ መልኩ አጣሪ እና እውነታ አፈላላጊ ኮሚቴ በማቋቋም ማስተባበል እና እራሳቸውን ከዚህ ከባድ እና ጠንካራ ክስ ነጻ ማድረግ ተስኗቸው ቀርቷል፡፡ እውነት በሀሰት ተቀብራ አትቀርማ! እንደዚህ ያለ ምርመራ እስከሚካሄድ ድረስ የእርዳታ ምንተፋ ስግብግብነት እና ሌብነት የማይደፈር እና ሊስተባበል የማይችል መደበኛ ዘረፋ ሆኖ የቆያል፡፡ ቦብ ጌልዶፍ እ.ኤ.አ በ1984 የሙዚቃ ባንድ በማስተባበር በአስር ሚሊዮኖች የሚቆጠር ዶላር ለእርዳታው እንዲሰበሰብ አድርጓል፣ የረኃብ እርዳታው በተሳሳተ መልኩ ለጦር መሳሪያ መግዣ ውሏል እየተባለ የሚሰማውን ውንጀላ ምክንያት በማድረግ እንዲህ ብሎ ነበር፣ “ምንም ዓይነት ገንዘብ ያለአግባብ የጠፋ ካለ የኢትዮጵያን መንግስት በህግ እጠይቃለሁ፡፡“
እ.ኤ.አ በ1980ዎቹ አጋማሽ (እንዲሁም ባለፉት 23 ዓመታት) መንግስታዊ ካልሆኑ የእርዳታ ሰጭ ድርጅቶች በአስር ሚሊዮኖች የሚሆን ለእርዳታ የተመደበ ዶላር የህወሀት አታላዮች ለራሳቸው ተራ ተስፈኝነት፣ በሚሊዮን የሚቆጠር ዶላር በብልጣብልጥነት እየዘረፉ ለግል ጥቅማቸው እና ለመሳሪያ መግዣ ያዋሉትን ሰው ዝም ብሎ በዘፈቀደ ሊያደንቅ ይችላል፡፡ እውነት ለመናገር አሊ ባባ እና የእርሱ 40 የወያኔ ሌቦች እንደዚህ ዓይነት ብልጣብልጥነት የተሞላበት የማጭበርበር ዕቅድ በመጠቀም መንግስታዊ ላልሆኑ የእርዳታ ሰጭ ድርጅቶች እራሳቸው እርዳታ ሰጭ ድርጅቶች የለገሱትን እህል እና አሸዋ የተሞላባቸውን ጆንያዎች እየደጋገሙ መሸጥ አልነበረባቸውም፡፡ የግሪክ የሌቦች አምላክ የነበረው ሄርምስ እንኳ እንደዚህ ያለ በጣም የሚያስገርም ዕንከንየለሽ የሸፍጥ ዕቅድ በማውጣት በሚሊዮኖች የሚቆጠር ዶላር ለመውሰድ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን ለማታለል እና በቀላሉ ለማሞኘት አልቻለም ነበር፡፡ የህወሀት አመራሮች “አዲስ የአፍሪካ የሌቦች ዝርያ” የሚለው ስም የሚገባቸው ነው፡፡
ማረት የህወሀት ባተሌ ፍጹም አያውቅ እረፍት፣
በኢትዮጵያ የዩናይትድ ስቴትስ የምግብ እርዳታ በሶስት የውጭ መንግስታዊ ያልሆኑ የእርዳታ ሰጭ ድርጅቶች በብቸኝነት ይተዳደራል፡፡ እነርሱም ምግብ ለተራቡ/Food for the Hungry (FH) (እራሱን የክርስቲያን ድርጅት/Christian Organization እያለ የሚጠራ እና እ.ኤ.አ ከ1971 ጀምሮ በዓለም አቀፍ ደረጃ ድሆችን በመርዳት ላይ ያለ)፣ የህጻናት አድን ድርጅት/Save the Children (እራሱን የዓለም የተቸገሩ ህጻናት ቁንጮ እርዳታ ሰጭ ድርጅት እያለ የሚጠራ)፣ የካቶሊክ እርዳታ አገልግሎት/Catholic Relief Services (CRS) (በዩናይትድ ስቴትስ ለካቶሊክ ማህበረሰብ ዓለም አቀፍ የሰብአዊ እርዳታ ድርጅት) እና ማህበረ ረድኤት ትግራይ/ማረት የሚባል አንድ የሀገር ውስጥ መንግስታዊ ያልሆነ እርዳታ ሰጭ ድርጅት ናቸው፡፡ እ.ኤ.አ በ1984 – 86 የረሀብ ሰለባ ለነበሩ ወገኖቻችን ከእርዳታ ሰጭ ድርጅቶች ቀርቦ የነበረውን የምግብ እርዳታ ያለምንም ይሉኝታ በረሀብተኞች ጉሮሮ ላይ በመቆም የተለያዩ ሸፍጦችን እና የማታለያ ዘዴዎችን እየፈበረከ ሙልጭ አድርጎ የበላ እና ለእራሱ የውንብድና ሀራራው የመሳሪያ ግዥ ያዋለ ማህበረ ረድኤት ትግራይ/ማረት የተባለው ያው ድርጅት አሁንም በ2014 በኢትዮጵያ ለተከሰተው ረሀብ ዓይን ባወጣ መልኩ እርዳታ አከፋፋይ ሆኖ ቀርቧል፡፡ የሌባ ዓይነደረቅ መልሶ ልብ ያወልቅ እንዲሉ!
እ.ኤ.አ በ2010 እና በ2014 (እንዲሁም ከ2010 በፊት) ማረት ከ1.5 ቢሊዮን ዶላር በላይ የሚሆን የምግብ እርዳታ ተቀብሎ በማከፋፈል ስራው ላይ ተሳታፊ የነበረ ብቸኛው የሀገር ውስጥ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት ነው፡፡ እ.ኤ.አ ኦገስት 15/2014 ዩኤስኤአይዲ/USAID እንዳወጣው ዘገባ ከሆነ ዩኤኤአይዲ በእራሱ ምግብ ለሰላም ጽ/ቤት/Office of Food for Peace እያለ በሚጠራው ጽ/ቤቱ በኩል እ.ኤ.አ በ2014 ለማረት እና ለሌሎች መንግስታዊ ያልሆኑ ዓለም አቀፋዊ ድርጅቶች 237 ሚሊዮን ዶላር፣ እ.ኤ.አ በ2013 ደግሞ 236 ሚሊዮን ዶላር፣ እ.ኤ.አ በ2012 ደግሞ 307 ሚሊዮን ዶላር፣ እንዲሁም እ.ኤ.አ በ2011 ሌላ 313 ሚሊዮን ዶላር እና እ.ኤ.አ በ2010 ደግሞ 452 ሚሊዮን ዶላር አድሏል፡፡
ማረት እስከ አሁንም ድረስ እራሱን “የህዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ/ህወሀት የሰብአዊ እርዳታ ክንፍ” አድርጎ ይቆጥራል፡፡ በእርግጥ ማረት እ.ኤ.አ በ2014 በሞኖፖል የያዘ መንግስታዊ ያልሆነ የሀገር ውስጥ ድርጅት እና ልክ እ.ኤ.አ በ1984 ሲያደርግ እንደነበረው ሁሉ በኢትዮጵያ ይህንን ግዙፍ የሆነ ዓለም አቀፍ እርዳታን በማጭበርበር በእራሱ የማስተላለፊያ ቱቦ ለህወሀት የሚያስተላልፍ በእርዳታ ሰጭ ድርጅት ስም የሀሰት ጭምብላ ያጠለቀ መንታፊ ድርጅት ነው፡፡ በኢትዮጵያ ውስጥ ዓለም አቀፋዊ እርዳታን ለማከፋፈል የሚወዳደሩ ሌሎች ሀገር በቀል መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች የሉም፡፡ በእርግጥ የበጎ አድራጎት እና ማህበራት አዋጅ እየተባለ የሚጠራው መንግስታዊ ተቋም በኢትዮጵያ ያሉትን ሁሉንም መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ሲያከስም (እ.ኤ.አ በ2010 አዋጁ ከወጣ በኋላ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ብዛት በሶስት ወራት ጊዜ ውስጥ ከ4,600 ወደ 1,400 ወርደዋል) ለማረት ጥሩ እድል በመፍጠር ምንም ዓይነት ተቀናቃኝ የሌለው ብቸኛው የሀገር ውስጥ ጠቅላይ ለመሆን በቅቷል፡፡
እንደ አንድ ኢትዮጵያዊ ምሁር ዘገባ ከሆነ ማረት የህወሀት የገንዘብ እና ቁሳቁስ ማስተላለፊያ ቱቦ ነው፡፡ በአሁኑ ጊዜ የህወሀት የንግድ ግዛት የመነሻ ካፒታል ከተለያዩ ምንጮች ይመጣል፡፡ አንዱ እና ዋናው የማስተላለፊያ ምንጩ የረኃብ እርዳታ የህወሀት ክንፍ የሆነው ማህበረ ረድኤት ትግራይ (ማረት) ነው፡፡ ማረት የእርዳታ ገንዘብን እና ሌሎች ቁሳቁሶችን ካልተጠበቁ እና በፈቃዳቸው ከሚሰጡ የውጭ የእርዳታ ሰጭ ድርጅቶች በመቀበል ገንዘብ እና ቁሳቁሶችን ወደ ህወሀት የገንዘብ ሳጥን ውስጥ የሚያስተላልፍ ድርጅት መሆኑ በስፋት ይታወቃል፡፡
የበጎ አድራጎት ድርጅት አዋጅ እየተባለ የሚጠራው መንግስታዊ ተቋም የሚያሳየው እውነታ አገር በቀል የሆኑ እና በሀገር ውስጥ መንቀሳቀስ የሚችሉት በህወሀት ስር ተጠቃለው የተያዙ ወይም ደግሞ ሌሎች ከህወሀት ጋር ወይም እርሱ ከሚፈልግላቸው ድርጅቶች ጋር በጋራ ለመንቀሳቀስ የሚችሉ ድርጅቶች ብቻ ናቸው፡፡ እ.ኤ.አ በ1984 ህወሀት በማረት በኩል ዓለም አቀፋዊ የሰብአዊ እርዳታን ለመሳሪያ መግዣ እና ለግል ጥቅሙ አውሏል፡፡ እ.ኤ.አ በ2014 ህወሀት ዓለም አቀፍ የሰብአዊ እርዳታን በማረት በኩል በመጠቀም አሁንም ለግል ጥቅሙ በማዋል ላይ ይገኛል፡፡ ምን ያህል! ነገሮች የበለጠ በተለዋወጡ ቁጥር የበለጠ አንድ ዓይነት እየሆኑ ይሄዳሉ!
ከመላ አፍሪካ ዩኤስኤአይዲ ትልቅ የእርዳታ ፕሮግራም ያለው በኢትዮጵያ ነው፡፡ ባለፉት 23 ዓመታት ብቻ በአስር ቢሊዮን የሚቆጠር ዶላር ከዩናይትድ ስቴትስ አሜሪካ ለህወሀት በእርዳታ ስም የተሰጠው ገንዘብ ከምን ላይ ዋለ? ለዚህ ጥያቄ የሚሰጠው መልስ እዕምሮን የሚበጠብጥ አስቸጋሪ ይሆናል! ማንም ሊያውቅ አይችልም፡፡ ዩኤስኤአይዲ/USAID እራሱ በቢሊዮን የሚቆጠር ዶላር ወደ ህወሀት የገንዘብ ካዝና ውስጥ የሚረጨው እንኳ አያውቀውም! ለዚያም ነበር የዩናይትድ ስቴትስ የመንግስት መምሪያ ጽ/ቤት ኢንስፔክተር በዘገባቸው ላይ እንዲህ የሚል መደምደሚያ የሰጡት፣ “የዩኤስኤአይዲ ኦዲት የምርመራ አገልግሎት የኢትዮጵያን የግብርና ምርታማነት ተግባራት (የኦዲት ዘገባ ቁጥር 4-6663-10-003-P (እ.ኤ.አ ማርች 30, 2010)“ በሚከተለው መልክ አስቀምጦታል፡
….የኦዲት ኢንስፔክተር [የግብርና ዘርፍ ምርታማነት] ፕሮግራም  የገበያ መር የኢኮኖሚ ዕድገት ማምጣቱን እና ገበሬዎች፣ አርብቶ አደሮች፣ እና ሌሎች በኢትዮጵያ የሚገኙት ተጠቃሚዎች ሁሉ መሻሻል እያሳዩ መሆናቸውን በጥናቱ አግኝቷል፡፡ ሆኖም ግን ያ የተገኘው ውጤት ምን ያህል እንደሆነ በአፈጻጸም አያያዝ እና የስራ አፈጻጸም ዘገባ ማቅረብ ደካማነት ምክንያት መወሰን አይቻልም፡፡ በተለይም ድርጅቱ በተለያዩ አካባቢዎች የስራውን ሂደት እና አፈጻጸሙን ለመከታተል እንዲቻል በሚል የስራ አፈጻጸም መለኪያ አመልካቾች እና ግቦችን በማስቀመጥ የሚጠቀም ቢሆንም… ለአብዛኞቹ መለኪያ አመልካቾች በዘገባ የቀረበው ውጤት ግን በግብነት ከተያዙት ጋር አልተነጻጸረም፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የቀረበው የኦዲት ዘገባ በዩኤስኤአይዲ/ኢትዮጵያ የቀረቡት  የአፈጻጸም ውጤቶች ተይዞ ከነበረው ዕቅድ ጋር መነጻጸር መቻል አለመቻላቸውን ለመወሰን አይቻልም ምክንያቱም የድርጅቱ ሰራተኞች እነዚህ ውጤቶች እንዴት እንደተገኙ መግለጽ አይችሉም ወይም ደግሞ ለእነዚያ ተገኙ ለተባሉት የስራ ውጤቶች ድጋፍ አይሰጡም፡፡ በእርግጥ የኦዲት ቡድኑ በዘገባው የቀረቡ የአፈጻጸም ውጤቶችን ተገቢነት ያላቸው እንዲሆኑ ለማድረግ ሙከራ ያደረጉ ቢሆንም ይህንን ለመስራት በድርጅቱ ወይም ደግሞ የድርጅቱ ተባባሪ አስፈጻሚዎች ሳይቻል ቀርቷል (ከገጽ 6 – 12)…
እ.ኤ.አ ኦክቶበር 2010 ሂዩማን ራይትስ ዎች የተባለው ዓለም አቀፋዊ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅት በኢትዮጵያ እርዳታ ከዓላማው ውጭ ለሌላ ጉዳይ መዋሉን አስመልከቶ መግለጫ አውጥቶ ለህዝብ ከመልቀቁ ከጥቂት ቀናት በፊት ዩኤስኤአይዲ/USAID እና የልማት እርዳታ ቡድን/Development Assistance Group (ለኢትዮጵያ እርዳታ የሚሰጡ 27ቱ የሁለትዮሽ እና በይነ መንግስታት የልማት ድርጅቶች (አንዳንድ ጊዜም በጥቅሉ ዓለም አቀፍ የድህነት ወትዋቾች/አቃጣሪዎች እየተባሉ የሚጠሩት) በኢትዮጵያ የልማት እርዳታ ላይ መጠነ ሰፊ እና ስልታዊ የሆነ ገንዘቡን ከታለመለት ዓላማ ውጭ የዋለ የለም ብለዋል፡፡ የእኛ ጥናት ስልታዊ የሆነ የእርዳታ ገንዘብ የጠፋ ወይም ደግሞ ለሌላ ዓላማ የዋለ ለመሆኑ ያገኘው ማስረጃ የለም ብለዋል፡፡ የወፍ ምስክሯ ድንቢጥ እንደሚባለው! ዳምቢሳ ሞዮ አሳማኝ በሆነ መልኩ እንደምትሞግተው ሁሉ ዓለም አቀፍ እርዳታ ለኢትዮጵያ እና ለሌሎች የአፍሪካ አገሮች ወጥመድ ሆኖ ቆይቷል፡፡ አሁንም ወጥመድ ነው፡፡ የዓለም አቀፉ የእርዳታ ምጽዋት ለኢትዮጵያ የጥገኝነት አዙሪትን፣ የተንሰራፋ ሙስናን፣ የገበያ መመሰቃቀልን፣ ስር የሰደደ ድህነት ማስፋፋትን እና ዘላለማዊ የእርዳታ ሱስ ውስጥ የሚያስገባ አደገኛ መርዝ ነው፡፡
ድህረ ጽሑፍ፣
በኢትዮጵያ ለበርካታ አስርት ዓመታት ሲከሰት በቆየው ረኃብ ላይ ጥናት በማካሄድ ዘገባ በማቅረብ ጠቃሚ አስተዋጽኦ ሲያደርጉ የቆዩ ሁለት ያልተዘመረላቸው ጀግኖች አሉ፡፡ እ.ኤ.አ በ1984 ተከስቶ ለነበረው በኢትዮጵያ ታላቁ ረኃብ 30ኛ ዓመት በሚታወስበት ዕለት እኔ በግሌ እንግሊዛዊውን ጋዜጠኛው ሚካኤል ቡርክን ከልብ ላመሰግን እወዳለሁ፡፡ ይህ ጀግና ጋዜጠኛ የኢትዮጵያን የ1984 ረኃብ በመዘገብ ሙዚቀኛ ቦብ ጌልዶፍን በማነሳሳት በቀጥታ በሚተላለፍ የእርዳታ ማሰባሰቢያ ኮንሰርት በመጠቀም ግዙፍ የሆነ ገንዘብ እንዲሰበሰብ በማድረጉ ብቻ አይደለም ሆኖም ግን በአስከፊው ረኃብ ምክንያት በመርገፍ እና በመሰቃየት ላይ የሚገኙትን የኢትዮጵያን ህዝቦች ሁኔታ ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ በማስተዋወቅ በፈጠረው ከፍተኛ የሆነ ግንዛቤ ጭምር እንጅ፡፡ እንደዚሁም ደግሞ የቢቢሲ ዘጋቢ እና በኋላም የአፍሪካ አርታኢ ሆኖ ሲሰራ የነበረውን እና እ.ኤ.አ በ1984 – 85 በተከሰተው ረኃብ ሰበብ ከምዕራቡ ዓለም ለተራቡት ወገኖቻችን የመጣውን በብዙ ሚሊዮን ዶላር የሚቆጠረውን እርዳታ በአቋራጭ ለመሳሪያ መግዣ እና ለግል ጥቅም ውሎ የነበረበትን እኩይ ምግባር ያጋለጠውን ጀግና ጋዜጠኛ ማርቲን ፕላውትን ከልብ ለማመስገን እወዳለሁ፡፡
የጋዜጠኝነትን ክቡር ሙያ በማስመልከት ታዋቂው የአሜሪካ ጸሐፊ፣ ዘጋቢ እና የፖለቲካ ተንታኝ የሚከተለውን አስፍሮ ነበር፣ “በጋዜጠኝነት ሙያ እውነታውን ከመናገር እና ሰይጣናዊ ድርጊትን ከማሳፈር እና ከማጋለጥ የበለጠ ትልቅ ህግ የለም፡፡“ እውነታን አፍርጦ በመናገር እና ሰይጣናዊ ድርጊትን በማሳፈር እና በማጋለጥ የ1984-85ን የኢትዮጵያን ታላቅ ረኃብ የዘገበ ከቡርክ እና ፕላውት ውጭ ማንም ጋዜጠኛ ይኖራል የሚል እምነት የለኝም፡፡ ኢትዮጵያዊ/ት የሆን ሁሉ እነዚህን ጀግኖች የማመስገን ዕዳ አለብን፡፡
ዓለም አቀፋዊ እርዳታ ለኢትዮጵያውያን/ት የድህነት አዙሪት ቀለበት ወጥመድ ሲሆን ለህወሀት ግን የመስረቅ እና የመዝረፍ ፈቃድ ነው!
ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር!
ጥቅምት 25 ቀን 2007 .
ምንጭ የኢትዮጵያ ሜዲያ መድረክ

Tuesday, November 4, 2014

የወያኔ ግፍ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ

November 3,2014
ዘረኛዉ ወያኔና ባለሟሎቹ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ በጋምቤላና በሸኮ መዠንገር አካባቢ የሚያካሄዱትን የማንአለብኝነት የመሬት ዝርፍያና ዜጎችን እርስ በርስ በማጋጨት ተጠቃሚ ለመሆን የሚያደርጉት አራዊታዊ ሩጫ የተነሳ ከፍተኛ ቁጥር ያለዉ ህዝብ ይህ ነዉ ተብሎ ሊነገር የማይችል እልቂት እየተፈጸመበት ነዉ። የመዠንገር ህዝብ የሞትና የህይወትን ያክል የማይወጣዉ ምርጫ ስለቀረበለት ተወልዶ ያደገበትን የአባቶቹንና የአያቶቹን አካባቢ ለቅቆ በመዉጣት እራሱን ለመከላከል ባደረገዉ እንቅስቃሴ የብዙ ንጹሃን ዜጎችና ቁጥራቸዉ ቀላል የማይባል ምስኪን ወታደሮችም ህይወት ማለፉ በይፋ እየተሰማ ነዉ። ይህንን ተከትሎ ግፈኞቹ የወያኔ መሪዎች በአካባቢዉ ብዙ ዘመን በቆዩ ብሄሰቦች መካክል ሆን ብለዉ ግጭት እንዲነሳ እያደረጉ በህዝብ መካክል ግጭትትና ዕልቂት የተነሳ በማስመሰል በአካባቢዉ ከፍተኛ ሰቆቃ በመፈፀም ላይ ይገኛሉ።
በዚህ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ በተለያዩ አካባቢዎች እየደረሰ ላለዉ መጠነ ሰፊ ግጭትና ዕልቂት ተጠያቂዉ በአካባቢዉ ለዘመናት አብሮ በመደጋገፍ የኖረዉ ህዝብ ሳይሆን የዚህ አሰቃቂ ዕልቂት ባለቤትና ጠንሳሽ ህወሓትና ዘረኛ መሪዎቹ መሆናቸዉን ለአንድም ደቂቃ ሊዘነጋ አይገባም። ይህ ግጭት ሊነሳ የቻለዉ ህወሓት የአካባቢዉን ደሃ ገበሬ ከትዉልድ መሬቱ ላይ እያፈናቀለ መሬቱን ለከፍተኛ የጦር መኮንኖቹና የኔ ለሚላቸዉ ባለሟሎቹ በማከፋፈሉ መሆኑን ይህንን ግፍ የሚሰማ ኢትዮጵያዊ ሁሉ ልብ ሊለዉ ይገባል። ህወሃት የአማራን ተወላጆች አካባቢዉ የእናንተ አይደለምና ዉጡ እያለና እያፈናቀለ በሌላ በኩል ግን በየክልሉ የአካባቢዉን ነዋሪ እያፈናቀለ የራሱን ሰዎች የመሬት ባለቤት ማድረጉ አዲስ የጀመረዉ ክስተት ሳይሆን ቆየት ያለና ስር የሰደደ የወያኔ አሰራር ነዉ።
ይህ ዛሬ በጋምቤላና በአካባቢዋ እየደረሰ ያለዉ ግፍና መከራ ለአካባቢዉ ህዝብ ብቻ የሚተዉ ነጠላ ችግር ሳይሆን በአጠቃላይ ወያኔ በአገራችን ላይ ሆን ብሎ በማድረስ ላይ ያለዉ ችግርና መከራ አካል ነዉ። በጋምቤላ ዉስጥ የፈሰሰዉና እየፈሰሰ ያለዉ የሴቶች፤ የወጣቶች፤ የአረጋዉያንና የህጸናት ደም ለሁላችንም የነጻነት ጥሪ እያቀረበልን ነዉ። ይህ የነጻነት ጥሪ ሰምተን የምናልፈዉ ወይም ነገ እንደርሳለን በለን በቀጠሮ የምናልፈዉ ጥሪ አይደለም። ጥያቄዉ የአገርና የዜጎች ህልዉና ጥያቄ ነዉና ነገ ዛሬ ሳንል አሁኑኑ ይህንን የነጸነት ጥሪ ሰምተን ምላሽ ልንሰጠዉ ይገባል።
ይህ ወያኔ በደቡብ ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ዉስጥ በንጹሃን ዜጎቻችን ህይወት ላይ እየፈጸመ ያለዉ ግፍ በአገራችን ህዝብ ላይ ሲደርስ የመጀመሪያዉ አይደለም፤ ካላቆምነዉ በቀር የመጨረሻዉ እንደማይሆንም አካሄዱ በግልጽ እያሳየን ነዉ። ወያኔ ጋምቤላ ዉስጥ ለምለም መሬት እየፈለገና ነዋሪዉን እያፈናቀለ መሬቱን ለባለሟሎቹ ማደሉን ሳይታቀብ በማንለብኝነት እንደቀጠለበት ነዉ። መሬቱን የተቀማዉ ደሃዉ የጋምቤላ ገበሬም ጫካ እየገባ ከወያኔ ጋር መተናነቁን ቀጥሏል። ትናንት በኦሮሚያ፤ በጉራፈርዳና በቤንሻንጉል አካባቢዎች በአማራ ተወላጆች ላይ የደረሰዉ ግፍና መከራ ዛሬ ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ዉስጥ በተለያዩ ብሄረሰቦች ላይ እየደረሰ ነዉ።
ግንቦት 7 የፍትህ፤ የነጻነትና የዲሞክራሲ እንቅስቃሴ ይህ ለከቱን የለቀቀ የህወሓት ዕብሪት እንዲተነፍስና በወገኖቻችን ላይ የሚደርሰዉ ግፍና ሰቆቃ እንዲቆም እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ነግ በኔ እያለ የነጻነት ትግሉን እንደቀላቀል የትግል ጥሪ ያደርጋል። ወያኔ እያደረሰ ያለዉ እስራት፤ ድብደባ፤ ግድያና ስደት የሁላችንንም ቤት እያንኳኳ ነዉና ሁላችንም እንደ አንድ ሰዉ ቆመን ወያኔንና ወያኔ የፈጠረዉን ዘረኛ ስርዐት በትግላችን መደምሰስ አለብን። በጋምቤላና በተለያዩ የአገራችን አካባቢዎች የፈሰሰዉ የንጹሃን ወገኖቻችን ደም ደመከልብ ሆኖ የማይቀረዉ ለመብታችንና ለነጻነታችን ቆመን ወያኔን ካስወገድን ብቻ ነዉ።
በህብረት እንነሳ!!!!
Source www.ginbot7.org

Sunday, November 2, 2014

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ወደ ዝዋይ እስር ቤት በለሊት ተወሰደ

በታሪኩ ደሳለኝ
(ኢ.ኤም.ኤፍ) እውቁ ጋዘጠኛ ተመስገን ደሳለኝ በጻፋቸው ጽሁፎች ምክንያት በፍርድ ቤት 3 አመት ተፈርዶበት በቅሊንጦ እስር ቤት እንዲቆይ ተደርጎ ነበር። ዛሬ የደረሰን ዘገባ እንደሚያመለክተው ደግሞ፤ ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ከቅሊንጦ ወደ ዝዋይ መወሰዱን ለማወቅ ተችሏል። ይህም በህገ መንግስቱ ላይ “አንድ እስረኛ ለቤተሰቡ ጥየቃ አመቺ እንዲሆን፤ የቅርብ ቤተሰብ ባለበት ስፍራ መታሰር አለበት” የሚለውን የእስረኛ ሰብአዊ መብት አያያዝ የጣሰ ነው። ለማንኛውን ዛሬ ከተመስገን ወንድም የደረሰውን ዘገባ ከዚህ በታች አቀናብረን አቅርበነዋል።
ጋዜጠኛ ተመስገን በፌዴራል ፖሊሶች ታጅቦ ሲወሰድ
ጋዜጠኛ ተመስገን በፌዴራል ፖሊሶች ታጅቦ ሲወሰድ
እንደለመድነው ዛሬም እኔና ሰውዓለም ታዬ የተመስገንን ስንቅ ይዘን በጠዋት ነው ቂሊንጦ እስር ቤት የደረስነው።  በመታበይ ሰማይ የደረሱት የእስር ቤቱ አስተዳደሮች በንቀት “ማን ጋር ናቹህ?” አሉን።
“ተመሰገን ደሳለኝ ጋር”
“ማን ትባላለቹም?” ነገርናቸው።
“ዞኑ ስንት ነው?”
“ዞን አንድ” አልናቸው። መታወቂያ ጠይቁንና፤ መታወቂያ ሰጠናቸው። አገለብጠው መዘገብ ላይ ከፃፉ በኋላ ወረወሩል። መታወቂያችንን አንስተን እነሱን አልፈን ገባን፡፡
ብዙዎቹ ወፌ ላላ የሚሏት ግርፋት በዚህ መንግስት መገረፋቸውን ሲነግሩንና ሲፅፉልን አንብበናል። ቂሊንጦ ደግሞ የታሰሪ ቤተሰብን በሚሸማቀቅ ሁኔታ ወፌ ላላ እሚባል ፍተሸ አላቸው። ወፌ ላላን ተፈትሽን አለፍን። ተመሰገንን ልናስጠራ ስንል እስረኝ አንደሚጠራልን ተነገረን። ስንዞር የሙስሊም መፍትሄ አፈላለጊ ኮሜቴዎች አንዱ የሆነው አቡበከር ነው። ሲያየን በፊቱ ላይ ሃዘን አየንበት። ሌላ ግዜ በፈገግታ ስላምታ የሚያስቀድመው አቡበከር በመከፋት “ተሜን ዛሬ ለሌት ዝዋይ ወሰዱት።” አለን። ትላንት ተመስገን ስንጠይቀው ስለዚህ ጉዳይ ምንም እሚያውቀው ነገር የለም፤ አልነገሩትም። ለሱ እንኳን ባይነግሩት እኛ ቤተሰብ አንደሆን እያወቁ ሊነግሩን አልፈለጉም። የያዝኩትን ስንቅ ሳየው የእናቴ ንግግር ትዝ አለኝ። “በሉ ቶሎ ሂዱ ምግቡ ሳይቀዘቅዝ አድርሱለት” ነበር ያለችው። …. እናቴ ምግቡም ይቀዘቅዛል፤ ልጅሽም የለም …. አቡበከርን አመስግነን ወጣን፡፡
አሳሬዎቹ ተሜን በተለያየ ጊዜ ሀገሩን ለቆ እንዲሰደድ ያላደረጉት ነገር የለም ከሀገር ሀገር ማዘዋወሩ ቢያቅጣቸው ካንደኛው የግዞት እስር ቤታቸው ወደሌላኛው የግዞት እስር ቤታቸው ማዘዋወሩ ላይ ግን ታስክቶላቸዋል!! ተሜን ሲወሰዱት አላየሁም፤ ግን ተሜን አውቀዋለሁ ለሀገሩ ሲል ጉዞው ቀራኒዬ ድረስ አንደሆነ፡፡ ወደ መኪናው ሲወሰዱት እስረኞቹን እያበረታታ ሲሰናበታቸው ….ፖሊሶቹን አንድ ቀን ከህዝብ ጎን እንደሚሆኑ እያሰበ… ሊነጋ ሲል እምትወጣውን ፀሐይ በተስፋ እያየ በፈገግታ ወደ ዝዋይ እንደሄደ ሳሰበው ደሰ አለኝ፡፡ በአይምሯዬ  ወደ ዝዋይ አቅጣጫ እየተመለከትኩ እንዲህ አልኩ።
ተመሰገን ደሳለኝ….
ከሀገር ወጣ ቢሉት፣ አልወጣም እዳለ
ከኛ ጎንን ሁን ሲሉት፣ ከህዝቡ እንደሆነ
ባላማው እንደፀና
እነደኮራ ሄደ፣ አንደተጀነነ!
ምንጭ  የኢትዮጵያ ሜዲያ  መድረክ