Wednesday, July 31, 2013

ለፍትሕ፣ ለዴሞክራሲ፣ ለልማት፣ ለአገርና ለሕዝብ በሀቅ፣ ከልብ፣ በእምነት፣ በትጋትና በተግባር እየሠራን ነው የምትሉ ባለሥልጣናት እጃችሁን አውጡ

31 JULY 2013 ተጻፈ በ  
አገራችን ኢትዮጵያ ከድህነት የተላቀቀች፣ ያደገችና የበለፀገች፣ ፍትሕና ዴሞክራሲ የነገሠባት አገር ሆና ለማየት የማይፈልግ ሀቀኛ ኢትዮጵያዊ የለም፡፡ ሁሉም ዜጋ ትፈልጋለህ ወይ ቢባል አዎን ይላል፡፡ ማልልኝ ቢባልም ‹‹ሙት!›› ይላል፡፡
በተለይ ባለሥልጣናት ይፈልጋሉ ወይ? እነሱም ይምላሉ ወይ? ቢባል አዎን ይፈልጋሉ አዎን ይምላሉ ተብሎ ብቻ የሚመለስ ሳይሆን፣ በፓርላማ ሕዝብ ፊት በአደባባይ አዎን ብለው ቃል ገብተዋል፤ ምለዋል፡፡

ጥያቄው የቃልና የመሀላ ብቻ ሳይሆን የተግባር ነው፡፡ በቃልማ ሕገ መንግሥቱም ያስገድዳል፡፡ እስቲ ለፍትሕ፣ ለሰብዓዊ መብት፣ ለዴሞክራሲ፣ ለልማት፣ ለአገር፣ ለሕዝብ በሀቅ፣ ከልብ፣ በእምነት፣ በትጋትና በተግባር እየሠራን ነን የምትሉ ባለሥልጣናት እጃችሁን አውጡ፡፡

በአንድ በኩል የአገር ሀብት የሚዳብርበት፣ አገር የሚለማበትና ድህነት የሚጠፋበት ሁኔታ ቢያጋጥም፣ በሌላ በኩል ደግሞ ጉቦ፣ የቪላና የተሽከርካሪ ጥቅማ ጥቅም የምታገኙበት ሁኔታ ቢኖርና ለመምረጥ መስቀለኛ መንገድ ቢያጋጥማችሁ የትኛውን ትመርጣላችሁ? የአገርና የሕዝብ ልማትን ወደ ጎን ገፍቶ የግል ጥቅምን ማካበት? ወይስ የግል ጥቅምን በመግፋት የአገርንና የሕዝብ ጥቅም ማስቀደም? እስቲ ከልብ የአገርና የሕዝብ ልማት የምታስቀድሙ እጃችሁን አውጡ፡፡ በተግባር ነው እያልን ያለነው፡፡

ሕዝብ ፍትሕ እያጣ መሆኑን ብታውቁና ማስረጃ ቢቀርብላችሁ፣ ሕግ የሚጣሰውና ፍትሕ እየታጣ ያለው ኔትወርክ በዘረጉ ወንጀለኞችና በባለገንዘቦች መሆኑን ብታውቁ ለፍትሕና ለዴሞክራሲ ብላችሁ ከሕዝብና ጎን ትቆማላችሁ? ወይስ ከአደገኞች፣ ከወንጀለኞች፣ ከባለገንዘቦችና ከባለኔትወርኮች ጋር ከምንጣላና ከምንጠቃ ብላችሁ ፍትሕና ዴሞክራሲን ትረግጣላችሁ? እስቲ እጃችሁን አውጡ፡፡

ይህንን አጀንዳ ያነሳነው በአጋጣሚ ወይም የተሻለ በማጣታችን አይደለም፡፡ አንገብጋቢ አጀንዳ ስለሆነብን ነው፡፡

ጠረጴዛው ላይ ትክክለኛ ማስረጃ ተደርድሮለት ማየት፣ ማወቅና መወሰን የማይፈልግ ባለሥልጣን እየታዘብን ነን፡፡ በሕገ መንግሥቱና በሕጎች መሠረት አገርንና ሕዝብን ከመምራት ይልቅ፣ ግለሰቦችን በመፍራትና ለእነሱ ተገዥ በመሆን የሚርበተበት ኃላፊ እየታዘብን ነን፡፡

በመገናኛ ብዙኃን ስለሚሰጥ መግለጫ አይደለም እያወራን ያለነው፡፡ ሙሰኛንና ኪራይ ሰብሳቢነትን የማያወግዝ ባለሥልጣን የለም፡፡ ስለአገርና ስለሕዝብ የማይናገር ሹም የለም፡፡ ሌት ተቀን ስለመሥራት የማይናገር ኃላፊ የለም፡፡ ስለ ሕገ መንግሥት የበላይነት የማይደሰኩር አለቃ የለም፡፡

በተግባር ግን አቶ እከሌን በመፍራት፣ የእከሊትን በመስማት፣ በግል ግንኙነት በመገዛት የአገርንና የሕዝብ ጥቅምና ክብር የሚረግጥ ባለሥልጣን እየታዘብን ነው፡፡ ከበስተጀርባ የሚሠራውና በአደባባይ የሚናገረው የሚጋጭበት ባለሥልጣን አለ፡፡ በአደባባይ ሙስናን ለማጥፋት አንገቴን እሰጣለሁ ብሎ እየፎከረ በተግባር ግን ሙሰኛውን እንዳትነኩት ብሎ ከለላ የሚሰጥ ሹም አለ፡፡

ከእከሌ ጋር ከሚጣሉና ከሚቀየሙ፣ ለምን ይህን አደረግክ ተብለው ከሚጠየቁ ይልቅ ሳይወስኑ፣ ሳይፈርሙና አቋም ሳይዙ የሚሽከረከሩ ባለሥልጣናት አሉ፡፡ የሕዝብ አደራ ተቀብለው፣ የሕገ መንግሥት አደራ ተሸክመው በስንትና ስንት ዜጎች መስዋዕትነት ተሸጋግረው ለሹመት የበቁ ባለሥልጣናት ሕዝብንም፣ መስዋዕትነትንም፣ ትግልንም በመርሳትና በመርገጥ ለጥቅማ ጥቅም ሲሉ አሽከርና ተላላኪ ሆነው ሲሽመደመዱም እያየን ነው፡፡ አገርንና ሕዝብን ለሽያጭና ለጥቅማ ጥቅም የሚያቀርቡ አሉ፡፡

ከመንግሥት ባለሥልጣናት መካከል በደካማነታቸው የሚገለጹ አሉ ስንል ጥሩዎች፣ ሀቀኞችና የሕዝብ አገልጋዮች የሉም ማለታችን አይደለም፡፡ ለአገር ልማት፣ ለፍትሕና ለዴሞክራሲ በተግባር እንቆማለን ብለው እጃቸውን ቢያወጡ የማይገርሙን አሉ፡፡ መጥፎዎች እንዳሉ ሁሉ ሀቀኞችም አሉ፡፡

ሥጋታችን ሞላጫው እየበዛ መምጣቱ ነው፡፡ ሥጋታችን ሞላጫው ድምፁ በከፍተኛ መጠን ሲሰማና ሲስተጋባ የሀቀኛው ድምፅ በሹክሹክታና በለሆሳስ መሆኑ ነው፡፡ ጠላት በአገር ላይ አደጋ የሚያደርሰው በሞላጮቹ፣ በስግበግቦቹና በሙሰኞቹ አማካይነት ነው፡፡ ለጥቅማ ጥቅም ብለው አገርን አሳልፈው የሚሸጡ እነሱ ናቸውና፡፡

መንግሥት ራሱን ያፅዳ እንላለን፡፡ መንግሥት ራሱን በማፅዳት ያጠናክር እንላለን፡፡ መንግሥት የራሱን ጋንግሪን ቆራርጦ ይጣል እንላለን፡፡ መንግሥት ከሚቦረቡር ካንሰር በሽታ ራሱን ይከላከል ይጠብቅ እንላለን፡፡

መንግሥት ሀቀኛ፣ ኩሩና ታማኝ ባለሥልጣናት ሊኖሩት ይገባል፡፡ ከመጀመሪያውም ንፁኃንና ሀቀኞችን ይሹም፡፡ ከሾመ በኋላም መዝቀጥና መንሸራተት እንዳይኖር ይከታተል፡፡ ከታየም የሚታከመውን ያክም፡፡ ታክሞ የማይድነውን ቆርጦ ይጣል እንላለን፡፡

በሀቀኛ ባለሥልጣናት የምንኮራውን ያህል በደካማ፣ በሙሰኛ፣ በተላላኪ ባለሥልጣናት ተግባር እያፈርን፣ እየሰጋና እየተሸማቀቅን እንገኛለን፡፡ አገርንና ሕዝብን ለአደጋ የሚዳርጉ ናቸውና፡፡

ስለዚህ መንግሥት ሆይ! ባለሥልጣናት ሆይ! አገርንና ሕዝብን ከአደጋ ለመጠበቅ በድፍረት ውስጣችሁን ገምግሙ፣ አፅዱ፣ ተጠናከሩ፡፡ ደካሞችና አስመሳዮች ይወገዱ፡፡ ሀቀኞችና የሕዝብ አገልጋዮች በኩራት አዎን ለፍትሕ፣ ለዴሞክራሲ፣ ለልማት፣ ለአገር፣ ለሕዝብ፣ በሀቅ፣ ከልብ፣ በእምነት፣ በትጋትና በተግባር እየሠራን ነን ብላችሁ እጃችሁን አውጡ፡፡  
ምንጭ ሪፖርተር ጋዜጣ

Friday, July 26, 2013

በቅርቡ በኦሮሞ ወንድሞቻችን ላይ የተፈጸመዉ ሰቆቃ ሊቆጨን፤ ሊያንገበግበንና ሊያስተባብረን ይገባል

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አለምአቀፋዊ የሰብዓዊ መብቶች ድንጋጌ አንቀጽ ዘጠኝ፤ አንቀጽ አስርና አንቀጽ አስራ አንድ የማንኛዉም አገር ዜጋ ያለ አግባብ መታሰር እንደሌለበት፤ በወንጀል ተጠርጥሮ የሚታሰር የማንም አገር ዜጋ በአስቸኳይ ፍርድ ቤት መቅረብ እንዳለበትና የፍርድ ቤቱ ሂደት አስከተፈጸመ ድርስ ደግሞ የተጠርጣሪዉ ዜጋ ንጽህና የተረጋገጠ መሆን እንዳለበት ይደነግጋል። በዚሁ የተመድ አለምአቀፋዊ ሰብዓዊ መብቶች ጥበቃ ድንጋጌ ሰነድ ላይ ተመስርቶ የተጻፈዉ የ1994ቱ የኢትዮጵያ ህገመንግሰት አንቀጽ 17 ንዑስ አንቀጽ ሁለት ደግሞ ማንም ዜጋ ያለ አግባብ መታሰር እንደሌለበት፤ ማንም ዜጋ ከፍርድ ቤት ትዕዛዝ ዉጭ መታሰር እንደሌለበትና በፍርድ ቤት ትዕዛዝ የታሰረ ዜጋም ቢሆን በአስቸኳይ ፍርድ ቤት መቅረብ እንዳለበት በግልጽ ይደነግጋል። ኢትዮጵያ ደግሞ የተመድ የሰብዓዊ መብቶች ድንጋጌ ያረቀቀችና ያጸደቀች አገር ብቻ ሳትሆን ከሃምሳ አንዱ የተመድ መስራች አገሮች ዉስጥ አንዷ ናት።
የ17 አመት የጫካ ዉስጥ ትግል ያካሄደዉና በ1983 ዓም አዲስ አበባ ገብቶ ላለፉት ሃያ ሁለት አመታት የኢትዮጵያን በትረ ስልጣን ጨብጦ የያዘዉ ህወሃት ኢትዮጵያ በፊርማዋ ያፀደቀችዉን የተመድን አለምአቀፋዊ የሰብዓዊ መብቶች ድንጋጌም ሆነ እሱ እራሱ አርቅቆ የጻፈዉን የኢትዮጵያ ህገመንግስት ማክበር ቀርቶ የሰነዶቹ ምንነት በዉል የጋባዉ ድርጅት አይደለም። ህወሀት የተወለደዉና ጥርሱን ነቅሎ ያደገዉ ጫካ ዉስጥ ሲሆን ዛሬም ከ22 አመታት የከተማ ዉስጥ ቆይታዉ በኋላ ኢትዮጵያን ያክል ትልቅ አገር የሚያስተዳድረዉ በዚያዉ ተወልዶ ባደገበትና በተካነዉ የጫካ ዉስጥ ህግ ነዉ። ህወሀትን ይዞት ካደገዉ ባህሉና ከዋና መገለጫ በህሪይዉ ተላቀቅ ማለት ዉኃ መዉቀጥ ሊሆን ይችላል፤ ሆኖም የጥቁር ህዝብ የነጻነት ምልክት የሆነዉን የኢትዮጵያን ህዝብ በጫካ ዉስጥ ህግ መዳኘትና ማስተዳደር ግን የኢትዮጵያ ህዝብ በፍጹም ሊቀበለዉ፤ አለም አቀፉ ህብረተሰብ ደግሞ አፉን ዘግቶ ሊመለከተዉ የማይገባ በህዝብና በአገር ላይ የሚፈጸም ከባድ ወንጀል ነዉ።
ዘረኛዉ የወያኔ አገዛዝ የተቃወመዉን ማሰር፤ ሀሳቡን በንግግር ወይም በጽሁፍ የገለጸዉን ማሰቃየትና የዘረኝነት ፖሊሲዉንና ኢትዮጵያን የማፍረስ አላማዉን ያወገዘን ዜጋ ሁሉ አስሮ ሰቆቃ መፈጸም ወይም ከአገር እንዲሰደድ ማድረግ ከመደበኛ አገር የመምራት ፖሊሲዎቹ ዉስጥ ዋና ዋናዎቹ ናቸዉ። በወያኔዋ ኢትዮጵያ ዉስጥ ወንጀል ተብለዉ ዜጎችን ከሞት እስከ ዕድሜ ልክ እስራት ድረስ የሚያስቀጡት የፈጠራ ክሶች አፍሪካን ጨምሮ በብዙዎቹ የአለማችን አገሮች ዉስጥ የማይገሰሱ የዜጎች መብቶች ናቸዉ። የሚገርመዉ ወረቀት ላይ የሰፈረዉ የወያኔ ህገመንግስትም ይህንኑ ይደነግጋል፤ ሆኖም ኢትዮጵያ ዉስጥ ሁለት አይነት ዜጎች ያሉ ይመስል በአንድ በኩል ህገመንግስቱ የሚቆምላቸዉ ዜጎች አሉ በሌላ በኩል ደግሞ ህገመንግስቱ የሚቆምባቸዉ ዜጎች አሉ። ዜጎችን በግልሰብ ደረጃ በባህሪያቸዉና በችሎታቸዉ ሳይሆን በቡድን ለይቶ በዘር ማንነታቸዉ የሚመለከተዉ ዘረኛዉ የወያኔ አገዛዝ ስልጣኔን ይቀናቀኑኛል ብሎ ካሰባቸዉ ከሁለቱ ግዙፍ የአገራችን ብሄረሰቦች ማለትም ከአማራዉና ከኦሮሞዉ ብሔረሰቦች ጋር ለብዙ ግዜ ጥርስ ተናክሶ ቆይቷል። ባለፉት ሁለት አመታት አማራዉን በአማራነቱ ብቻ እያሳደደ መድረሻ ያሳጣዉ ዘረኛዉ የወያኔ አገዛዝ በቅርቡ በግፍ ታስረዉ በቁጥጥሩ ስር በሚገኙ 69 የኦሮሞ ተወላጆች ላይ ይህ ነዉ ተብሎ በሰዉ አንደበት ሲነገር አጅግ በጣም የሚዘገንን ወንጀል ፈጽሞባቸዋል።
መለስ ዜናዊ ከመሞቱ ከአንድ አመት በፊት ከፍርድ ቤት ፈቃድ ዉጭ በግፍ ሰብስቦ ያሰራቸዉና ፍርድ ቤት ሳይቀርቡና ለምን እንደታሰሩ እንኳን ሳያዉቁ ለሁለት አመታት እስር ቤት ዉስጥ የከረሙት 69 የኦሮሞ ተወላጆች ባለፈዉ ሳምንት እስር ቤት ዉስጥ እንዳሉ እጅግ በጣም የሚዘገንን ወንጀል ተፈጽሞባቸዋል። ባለፈዉ ሀምሌ 6 ቀን ፍርድ ቤት ለመቅረብ በዝግጅት ላይ እንዳሉ ቀጠሯቸዉ በአራት ወር የተራዘመባቸዉ ስልሳ ዘጠኙ የኦሮሞ ተወላጆች የቀጠሮዉን መራዘም በመቃወም አቤቱታቸዉን ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ጽ/ቤት ለማቅረብ ሲሞክሩ የማረሚያ ቤቱ አስተዳዳሪዎች እንዴት እንዲህ ይታሰባል በሚል በቂም በቀል በመነሳት እስረኞቹን በቡድን በቡድን በመከፋፈልና እጅና እግራቸዉን በማሰር ከፍተኛ ድብደባ መፈጸማቸዉን ከሆስፒታል ምንጮች የተገኘዉ መረጃ ያመለክታል። በዕለቱ ድብደባ ከፍተኛ የአካል ጉዳት ከደረሰባቸዉ እስረኞች ዉስጥ ስምንቱ በድብደባ ብዛት እራሳቸዉን በመሳታቸዉ ወደ ሆስፒታል ተወስደዋል። ስልሳ ዘጠኙ አስረኞች በሶስት ቡድን ተከፍለዉ ድብደባዉ የተፈጸመባቸዉን ክፍሎች በአይናቸዉ ከተመለከቱ ሰዎች በተገኘዉ መረጃ መሰረት እስረኞቹ የተደበደቡባቸዉ ክፍሎች በደም በመጨቅየታቸዉ አርብ ቀኑን ሙሉ በውሀ ሲታጠቡ አንደነበር ለማወቅ ተችሏል።
ይህ ወያኔ ቀድሞዉኑም ቢሆን ያለ አግባብ ባሰራቸዉ ንጹህ የኦሮሞ ተወላጆች ላይ የፈጸመዉ ወንጀል በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ በየቀኑ የሚፈጽመዉ በደልና ወንጀል አካል በመሆኑ ግንቦት ሰባት የፍትህ የነጻነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ የህንን ዘግናኝ ወንጀል በራሱ ላይ እንደተፈጸመ አገራዊ ወንጀል በመቁጠር ከወያኔና ከዘረኛ ስርዐቱ ለመገላገል የሚያደርገዉን ትግል በያለበት እንዲያፋፍም ወገናዊ ጥሪዉን ያስተላልፋል። ኦሮሞዉ ሲጠቃ አማራዉ ካልደረሰለት አማራዉ ሲረገጥ ሶማሌዉ ፤ አፋሩ፤ ሲዳማዉና ወላይታዉ ወዘተ ካልደረሱለት ከፋፋዩ የወያኔ ስርዐት እያንዳንዳችንን ተራ በተራ ማሰቃየቱንና መርገጡን መቀጠሉ የማይቀር ነዉ። ስለዚህ ከወያኔ ጋር በምናደርገዉ የሞት የሽረት ትግል የኛ ኃይል አንድነት የወያኔ ኃይል ደግሞ መነጣጠላችን መሆኑን አዉቀን ይህንን ዘረኛ ስርዐት በቃ ብለን ከጀርባችን ላይ አሽቀንጥረን ለመጣል በህብረት እንነሳ።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!



    Wednesday, July 24, 2013

    ወ/ሮ አዜብ መስፍን ኢሕአዴግ የአቶ መለስን ሕልፈት ለመቀስቀሻ ተጠቅሞበታል መባሉን አስተባበሉ

      ነሐሴ 14 ቀን የአቶ መለስ ዜናዊ መታሰቢያ እንዲሆን ተወሰነ

    የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ከዚህ ዓለም በሞት ሲለዩ፣ ኢሕአዴግ ሕዝብን ለማነቃቃትና የፖለቲካ እንቅስቃሴውን ለማስፋት ተጠቅሞበታል መባሉን፣ ባለቤታቸው ወ/ሮ አዜብ መስፍን አስተባበሉ፡፡
    24 JULY 2013 ተጻፈ በ  
    ወ/ሮ አዜብ ሐምሌ 13 ቀን 2005 ዓ.ም. ማስተባበያውን የተናገሩት፣ የባለቤታቸውን አቶ መለስ ዜናዊን የሙት ዓመት አከባበር አስመልክቶ ከፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባዔ አቶ ካሳ ተክለ ብርሃን ጋር ጋዜጣዊ መግለጫ ሲሰጡ ከጋዜጠኞች ለቀረበላቸው ጥያቄ ምላሽ ሲሰጡ ነው፡፡

    ‹‹ኢሕአዴግ የአቶ መለስን ሞትና መለስ ዜናዊ ፋውንዴሽንን ለሕዝብ ማነቃቂያነት እየተጠቀመበት መሆኑ እየተገለጸ ነው፡፡ ምላሽዎ ምንድነው?›› የሚል ጥያቄ የቀረበላቸው ወ/ሮ አዜብ፣ መጀመሪያ ‹‹መለስ ማነው?›› የሚለውን ጥያቄ መመለስ አስፈላጊ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

    ወ/ሮ አዜብ በምላሻቸው፣ ‹‹መለስ ኢሕአዴግ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝብ ለመለስ ከፍተኛ ፍቅር አለው፡፡ ከኢሕአዴግ በፊት የመለስን ሐሳቦች፣ ጅምሮችና ውጥን ሥራዎች ለማስቀጠል ሕዝቡ ቃል ገብቷል፡፡ ሕዝቡን ፓርቲው ኢሕአዴግ ቀስቅሶት ሳይሆን የራሱ ስሜትና ፍቅር ፈንቅሎት ወጥቷል፤›› በማለት አስረድተዋል፡፡

    የአቶ መለስ ዜናዊ ሥራዎች በኢሕአዴግ ቅስቀሳ ላይ ተመሥርተው ከሕልፈታቸው በኋላ የሰረፁ አለመሆናቸውን የገለጹት ወ/ሮ አዜብ፣ አቶ መለስ በነበሩበት ወቅት ምንም ዓይነት ቅስቀሳም ሆነ ሌላ ነገር ሳይኖር፣ በሕዝቡ ውስጥ ሰርፆ የቆየና ገንፍሎ የወጣ መሆኑን አውስተዋል፡፡

    ሕዝቡ የኢሕአዴግ ቅስቀሳ እንደማያስፈልገው የተናገሩት ወ/ሮ አዜብ፣ በአቶ መለስ የተጀመሩ ሥራዎችን ከዳር ለማድረስ ግን ኢሕአዴግ የመምራት ግዴታ እንዳለበትና እየመራም መሆኑን ገልጸዋል፡፡ የሚመራቸው ሥራዎች በሙሉ የአቶ መለስ ጅምሮች በመሆናቸውና በተሰባሰበ የሰው ኃይል መሠራት ስላለባቸው፣ ኢሕአዴግ የማስፈጸም ሥራውን ሊያከናውን የግድ እንደሚለውም አክለዋል፡፡
    24 JULY 2013 ተጻፈ በ  
    እንደ ወ/ሮ አዜብ ገለጻ፣ ፓርቲው የአቶ መለስ ክብርና ፍቅር ስላለው እንደማንኛውም የኅብረተሰብ ክፍል ስማቸውን መጥራቱና ማንሳቱ ነውር የለውም፡፡ ለመነገጃነት ግን አለመጠቀሙን ሕዝቡ ሊገነዘብ እንደሚገባ ጠቁመዋል፡፡

    በመለስ ዜናዊ ፋውንዴሽን የቦርድ አመራር ሆነው ከተመረጡት ከወ/ሮ አዜብ በስተቀር፣ ሌሎቹ የመንግሥት ባለሥልጣናት መሆናቸው ‹‹አቶ መለስና ሥራዎቻቸው የሕዝብ ናቸው›› ከሚለው ጋር እንደሚጋጭና ሌላው የኅብረተሰብ ክፍል ለምን እንዳልተካተቱ እንዲያብራሩ የተጠየቁት ወ/ሮ አዜብ፣ ጥያቄው ትክክል ነው ብለዋል፡፡

    ‹‹ፋውንዴሽኑ በተቋቋመበት ወቅት ይኼንን ኃላፊነት ተሸክሞ መንቀሳቀስ የሚችለው የቅርብ ኃይል አሁን ቦርድ ሆኖ የተሰየመው ነበር፤›› ካሉ በኋላ፣ ሕዝቡ ግን ፍላጎት እንዳለው እንደሚያውቁ ገልጸዋል፡፡ ሁሉም የኅብረተሰብ ክፍል ባለቤት የሚሆንበት ማዕከል እንደሚገነባና አሁን ያለው ሁኔታም እንደሚስተካከል አስረድተዋል፡፡

    ‹‹ዘመቻ መለስ ለአረንጓዴ ልማት›› በሚል መሪ ቃል ተራራዎችን በችግኝ ለማልበስ፣ የፋውንዴሽኑ ቦርድ በችግኝ ማፍላት ዙርያ ሲረባረብ መክረሙን የገለጹት የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባዔ አቶ ካሳ ተክለ ብርሃን ሲሆኑ፣ የችግኝ ተከላው ፕሮግራም በሁሉም የአገሪቱ ክፍሎች እንደሚካሄድ አስታውቀዋል፡፡

    የአቶ መለስ ዜናዊን ሙት ዓመት አስመልክቶ የተለያዩ ፕሮግራሞች እንደሚኖሩ የገለጹት አቶ ካሳ፣ ‹‹አረንጓዴና ዘላቂ ልማት›› የሚለው የአቶ መለስ ፅኑ እምነት በመሆኑ፣ በስማቸው የሚሰየም ቦታን በመከለልና በፈቃደኝነት ላይ የተመሠረተ የችግኝ ተከላ በወረዳ፣ በክፍለ ከተማና በማዕከል እንደሚካሄድ አስረድተዋል፡፡

    የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አንዳንድ የሚያስተካክለውና የሚሠራው በመኖሩ፣ ሙዚየሙና ፓርኩ የሚገነባበት ትክክለኛ ቦታ ለጊዜው ባይታወቅም፣ ዲዛይኑ በመሠራት ላይ መሆኑንና በቅርቡ ለሕዝቡ ይፋ እንደሚደረግ አፈ ጉባዔው አስታውቀዋል፡፡

    በሙዚየሙና በፓርኩ መሥሪያ ቦታ ላይ ነሐሴ 14 ቀን 2005 ዓ.ም. የመሠረት ድንጋይ እንደሚቀመጥ የገለጹት አቶ ካሳ፣ ነሐሴ 14 ቀን የአቶ መለስ ሕልፈት የተነገረበትና የኢትዮጵያ ሕዝብ ከፍተኛ ድንጋጤና ሐዘን የሰማበት ቀን በመሆኑ፣ ‹‹የአቶ መለስ ዜናዊ መታሰቢያ ቀን›› እንዲሆን ቦርዱ መወሰኑንም ተናግረዋል፡፡ ኅብረተሰቡ በፍላጎቱ ለሙዚየሙና ለፓርኩ ግንባታ መዋጮ ማድረግ እንደሚፈልግ በተለያየ መንገድ እየገለጸ መሆኑን፣ በፍላጎቱ መሠረትም ማዋጣት እንዲችል በኢትዮ ቴሌኮም አማካይነት በሚሰጡ ቁጥሮች ከሁለት እስከ አንድ መቶ ብር መላክ እንዲያስችለው መመቻቸቱንና በቅርቡ በመገናኛ ብዙኀን እንደሚገለጽ አስታውቀዋል፡፡     
    ምንጭ ሪፖርተር.

    የፓርላማው ውይይት መታፈኑን በይፋ ያጋለጠው የኢቲቪ ጋዜጠኛ ከሥራ ተባረረ

    (በአዲስ አበባ ታትሞ የወጣው ሰንደቅ ጋዜጣ እንደዘገበው)
    የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት “የዴሞክራሲ ተቋማት ሚናና የአስፈፃሚ ተቋማት ኃላፊነት” በሚል ጥቅምት 23 ቀን 2005 ዓ.ም ያደረገውን ውይይት በኢትዮጵያ ራዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት በኩል ተቆራርጦና ተዛብቶ እንዲተላለፍ ተደርጓል በሚል አንድ ዜና መዘገቡ ይታወሳል።
    ይህን ዜና በሰንደቅ ጋዜጣ የህዳር 5 ቀን 2005 ዓ.ም ዕትም “ኢቲቪ የከፍተኛ ባለሥልጣናትን ውይይት በማፈን ተወቀሰ” በሚል ርዕስ ከቀረበ በኋላ፤ በዚህ ዘገባ ላይ ተመድቦ የሠራው የቀድሞ የኢቲቪ ባልደረባ ጋዜጠኛ አዲሱ መሸሻ ረቡዕ ህዳር 12 ቀን 2005 ዓ.ም በጉዳዩ ላይ ለዝግጅት ክፍላችን ምላሹን ሰጥቷል።
    ጋዜጠኛ አዲሱ መሸሻ
    (ፎቶ ከሰንደቅ ጋዜጣ)
    እነዚህ ዘገባዎች ከተስተናገዱ በኋላ፣ ጋዜጠኛ አዲሱ መሸሻ ለሰንደቅ ጋዜጣ መረጃ እንደሰጠና ሚስጢር እንዳወጣ ተቆጥሮ የዲስፒሊን ክስ ቀርቦበታል። ኢ.ሬ.ቲ.ድ በዲስፒሊን ክሱ ላይ አራት ከፍተኛ የሥራ አመራሮች በምስክርነት ዘርዝሮ አቅርቧል። የድርጅቱ የዲስፒሊን ኮሚቴ በከሳሽ በኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት እና በጋዜጠኛ አዲሱ መሸሻ መካከል የክስ ዝርዝር እና የመልስ መልስ ደብዳቤዎች ሲያዳምጥ ከሰነበተ በኋላ ግንቦት 9 ቀን 2005 ዓ.ም በቁጥር ቴ02.1/131-304/02/8/ በተፃፈ ደብዳቤ ጋዜጠኛ አዲሱ መሸሻ ከግንቦት 10 ቀን 2005 ዓ.ም ጀምሮ ከሥራ የሚያሰናብተውን ቅጣት አሳልፏል።
    በሕዝብ ተወካዮች ምክርቤት ባለቤትነት በጠ/ሚኒስትሩ ቢሮ ጥቅምት 23 ቀን 2005 ዓ.ም የተካሄደው ስብሰባ በመልካም አስተዳደር፣ በተጠያቂነት፣ በሙስና ችግሮችና በመሳሰሉት ላይ ልዩ ትኩረት በመስጠት የተካሄደ ሲሆን በዚህ ውይይት ላይ የኢፌዲሪ ምክትል ጠ/ሚኒስትርና የትምህርት ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ጨምሮ የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት አፈጉባኤ አቶ አባዱላ ገመዳ፣ በሚኒስትር ማዕረግ የስኳር ኮርፖሬሽን ዋና ዳይሬክተር አቶ አባይ ፀሐዬ፣ የመገናኛና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል፣ የእምባ ጠባቂ ተቋም ዋና እምባ ጠባቂ ወ/ሮ ፎዚያ አሚን፣ የፌዴራል የሥነ ምግባርና የፀረ ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ዓሊ ሱሌይማን፣ የአ/አ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አቶ አበባው ስጦታው እና ሌሎችም የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተው ነበር።
    የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት የጠራውና የአስፈፃሚ አካላትና የዴሞክራሲ ተቋማት ሚናን በተመለከተ የተደረገው ውይይት፣ በዕለቱ በሥፍራው ባልነበረ ጋዜጠኛ ተገቢ ባልሆነ መልኩ ተቆራርጦና ተዛብቶ ለሕዝብ መቅረቡ ትክክል እንዳልነበረ በይፋ በመግለፁ ምክንያት ከሥራ የተሰናበተው የኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቭዥን ድርጅት ባልደረባ የነበረው ጋዜጠኛ አዲሱ መሸሻን ስለሁኔታው ፋኑኤል ክንፉ አነጋግሮታል።
    ሰንደቅ፡- የዚህ ዜና መነሻ አንተን አድርገው ለመውሰድ ያስቻላቸው ምክንያቶች ምንድን ናቸው?
    ጋዜጠኛ አዲሱ፡- ይህን ምላሽ መስጠት የሚችሉት እነሱ ናቸው። በሰጡኝ የክስ ዝርዝር ላይ ግን ሌላ ምክንያት ነው ያስቀመጡት። ወይም ደግሞ ላነሳኸው ጥያቄ ማረጋገጫ ማቅረብ የሚችለው የዚህ ጋዜጣ ዝግጅት ክፍል ብቻ ነው።
    ሰንደቅ፡- እንዴት?
    ጋዜጠኛ አዲሱ፡- ምክንያቱም “ኢቲቪ የከፍተኛ ባለሥልጣናትን ውይይት በማፈን ተወቀሰ” ለሚለው ዜና መነሻ ለሰንደቅ ጋዜጣ ዝግጅት ክፍል በእኔ በኩል ያልኩትም አንዳች ነገር የለም። እንደማንም አንባቢ ይህ ዜና በሰንደቅ ጋዜጣ ከወጣ በኋላ ነው የተመለከትኩት። ስለዚህም መረጃ ከእኔ አግኝታችሁ ከሆነ አግኝተናል፤ ካላገኛችሁ አላገኘንም ለሚለው ምላሽ መስጠት የሰንደቅ ጋዜጣ ዝግጅት ክፍል ይመስለኛል።
    ሰንደቅ፡- በርግጥ የሰንደቅ ጋዜጣ ዝግጅት ክፍል ለዚህ ዜና መነሻ መረጃውን ያገኘው ከሌላ ሶስተኛ ወገን መሆኑን ማረጋገጥ እንችላለን። ሆኖም ግን ይህ ዜና በወጣ በሳምንቱ ህዳር 12 ቀን 2005 ዓ.ም. እርሶ ለሰንደቅ ጋዜጣ ማስተባበያ መስጠትዎ የሚታወስ ነው። በወቅቱ ከዜናው ጋር በተያያዘ ለምን ማስተባበል ፈለጉ?
    ጋዜጠኛ አዲሱ፡- “የዴሞክራሲ ተቋማት ሚናና የአስፈፃሚው ተቋማት ኃላፊነት” በሚል የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ያዘጋጀውን ፕሮግራም የቀረጽኩት እኔ በመሆኔ ነበር። በሰንደቅ ጋዜጣም የተሰራው ዜና “የባለስልጣናት ድምጽ ታፈነ” የሚል በመሆኑም ጭምር ነው። ከዚህ አንፃር እንደአንድ ጋዜጠኛ ውይይቱን አፈነ ተብሎ መወንጀል በጣም አደገኛ ነው። እንዲሁም ማንስ አፈነው? እንዴት ታፈነ? ለሚሉት ጥያቄዎችም ምላሽ የሚፈልጉ መሆናቸው ግልፅ የሆነ ነገር ነው። በተለይ በውይይቱ ላይ ተሳታፊ የነበሩትን ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናትን ኃላፊነት ታሳቢ ስታደርግ በእኔ ውስጥ ሊፈጠር የሚችለውን ድንጋጤ መገመት ከባድ አይደለም። የእነዚህን ከፍተኛ ባለስልጣናት አንደበትን ለማፈን በእኔ በተራ ረዳት አዘጋጅ ቀርቶ በሌላው የተቋሙ ከፍተኛ አመራር የሚሞከር ተግባር ተደርጎ የሚወስድ አካል ያለ አይመስለኝም።
    ይህ ችግር ከተፈጠረ በኋላም ከስራ ባልደረቦቼ ጋር ተወያይቻለሁ። እንዲሁም አንድ የተቋሙ ከፍተኛ አመራር ለማግኘት ጥረት ባደርግም አልተሳካልኝም። የሆኖ ሆኖ ከባልደረቦቼ ጋር ከመከርኩ በኋላ ፕሮግራሙ ታፍኗል ብሎ ለዘገበው ጋዜጣ ማስተባበያ በመስጠት እራሴን ከጉዳዩ ነፃ ማድረግ እንዳለብኝ ተማምነናል። የመንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናቱም እኔ አለማድረጌን ሊገነዘቡ የሚችሉት ፕሮግራሙ ታፍኗል የሚለውን ዜና ባሰራጫው ሚዲያ መሆኑ አሻሚ አይደለም። ስለዚህም በዚህ ጉዳይ ላይ ንፁህ መሆኔን ለማረጋገጥ ለሰንደቅ ጋዜጣ ዝግጅት ክፍል በጉዳዩ ላይ ያለኝን መረጃ ለመስጠት ተገድጃለሁ።
    ሰንደቅ፡-እርሶ እንደዚህ ቢሉም፣ በኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት ታህሳስ 01 ቀን 2005 ዓ.ም. በተፃፈ ደብዳቤ የዲስፕሊን ኮሚቴው “አቶ አዲሱ መሸሻ በየነ በፕሮግራሙ ኢ.ሬ.ቴ.ድ የባለስልጣኖች ድምጽ አፍኗል። ፕሮግራሙ ቆራርጧል የሚል የተሳሳተና ከኃላፊነት የራቀ እና በሀሰት የተሞላ መግለጫ ለሰንደቅ ጋዜጣ” ሰጥቷል ሲል ይከሳል። በዚህ ላይ የእርሷ አስተያየት ምንድን ነው?
    ጋዜጠኛ አዲሱ፡- እዚህ ላይ መታወቅ ያለበት የኢ.ሬ.ቴ.ድ “የከፍተኛ ባለሥልጣናትን ውይይት በማፈን ተወቀሰ” ያለው ሰንደቅ ጋዜጣ እንጂ እኔ አዲሱ አይደለሁም። በወቅቱም በሰጠሁት ማስተባበያ ተቋሙን በተመለከተ ያልኩት አንዳች ነገር የለም። የማፈን ነገር ተፈጽሟል ከተባለም ግለሰቡ እንጂ ተቋሙ ሊሆን አይገባም በማለት ነበር ተቋሙን የተከላከልኩት። በሌሎችም ተቋማት ግለሰቦች ከተቋሙ ዓላማ በመውጣት የሚፈጽሙት ስህተት በእኛም ተቋም በተመሳሳይ ሁኔታ ተፈጽሟል። ይህ ማለት ግን ግለሰቦች ከተቋም በላይ ናቸው ማለት አይደለም። ስለዚህም ግለሰቦች በሰሩት ጥፋት በግል መጠየቅ አለባቸው እንጂ በተቋም ደረጃ ስህተቱ ሊታይ አይገባም። ስለዚህም አንድ ሰው በራሱ መነሻ በፈጸመው ተግባር የተቋም አድርጎ መውሰድ ከሕግም ከሞራልም አንፃር የሚያስኬድ አይመስለኝም።
    ሰንደቅ፡- የተከሰስክበት የደብዳቤ ይዘት ሚስጥር በማውጣት የሚል ነው። የሰጠኸው ማስተባበያ ከሚስጥር መጠበቅ ጋር እንዴት ትገልፀዋለህ?
    ጋዜጠኛ አዲሱ፡- በመጀመሪያ ደረጃ ሚስጥር ማባከን ከመጥፎ ፍላጎት (intention) የሚመነጭ ነው። ሚስጥር የሚባክነው ተቋምን ወይም ግለሰብን ለማጥቃት ከመፈለግ የሚመጣ ክፉ መንፈስ ነው። ከዚህ አንፃር ስትወስደው፣ እኔ በሰንደቅ ጋዜጣ ላይ የሰራሁትን ፕሮግራም የሚመለከት ዜና በመሰራቱ ብቻ ማስተባበያ ሰጠው እንጂ ምን አጠፈሁ። ከእኔ ጋር ተያያዥነት ያለው ዜና ባይወጣ እኔም ባልተናገርኩ፤ እነሱም ክስ ያሉት ክስ ባልመሰረቱብኝ ነበር። ስለዚህም የጋዜጠኝነት ሙያዬን (integrity) በሚያጠፉ “አፋኝ” ተብሎ በተሰየመ ሁኔታ ስሜ ጠፍቶ፣ ስሜን ለመመለስ መከላከሌ ተገቢ ነው ብዬ አምናለሁ። ይህ ከሚስጥር ማባከን ከመጠበቅ ጋር ምን ያገናኘዋል?
    ሁለተኛው፣ “የዴሞክራሲ ተቋማት ሚናና የአስፈፃሚው ተቋማት ኃላፊነት” በሚል በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተካሄደው ውይይት ዋናው ዓላማው፣ ውይይቱ ለሕዝብ እንዲቀርብ ነበር። ተደራሽነቱም ለሕዝቡ ነው። ለሕዝቡም ግልፅ መረጃ ለማቅረብ የተዘጋጀ ውይይት ነበር። ከሁሉ በላይ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የነበረው የስብሰባ ይዘት፣ የኪራይ ሰብሳቢነት አደጋ በዚህች ሀገር ውስጥ የደረሰበትን ከፍተኛ ደረጃ ለሕዝብ ማሳየት ነበር። ሕዝቡም አደጋውን በመረዳት ከመንግስት ጎን በመሰለፍ የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ ግንዛቤ ለማስጨበት ያለመ ስብሰባ ነበር። ይህ ታዲያ ምን ሚስጥር አለው? ሚስጥር ከሆነ መጀመሪያውኑ ሚዲያውን አይጋብዙም ነበር። በወቅቱም ፕሮግራሙ ሲቀረጽም ሚስጥር ነው ያለ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣን አልነበረም።
    ሌላው በዚህ ተቋም ውስጥ በቆየሁበት የስራ ዘርፎች ሚስጥር ተብለው የሚቀረፁ ስራዎችን ጠንቅቄ አውቃለሁ። በሚስጥር ደረጃ የተቀረፁ ስራዎችንም ሰርቼ አውቃለሁ። በዚህ ደረጃ የሰራኋቸውን ስራዎች እንኳን ለሶስተኛ ወገን፣ በተቋሙ ውስጥ ማወቅ ከሚገባቸው ሰዎች ውጪ ዉይይት አድርጌም አላውቅም። አለቆቼም ይህን ጠንቅቀው ያውቁታል።
    ሰንደቅ፡- የዲሲፕሊን ኮሚቴው እንደሚለው ከሆነ “በስሜት ያደረኩት ነው” ሲሉ አቶ አዲሱ በኢዲቶሪያል ስብሰባ ላይ ገልጸዋል ይላል። በዚህ ላይ የእርስዎ አስተያየት ምንድን ነው?
    ጋዜጠኛ አዲሱ፡- በነገራችን ላይ የነበረው ኢዲቶሪያል ስብሰባ በአዋጅ ከተሰጠው ስልጣን ብዙ ርቆ የሄደ ነው። ግልፅ የፖሊስ ምርመራ ነበር የተደረገብኝ። አስራ አራት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ባሉበት የተደረገ ስብሰባ ሲሆን አውጣ፣ አታውጣ የሚሉ ጥያቄዎች ነበሩ። እኔ ለማስፈራራት፣ ለማሸማቀቅ የተደረገ ኢዲቶሪያል ስብሰባ ነበር። የቀረበብኝ ውንጀላ እስከሀገር ክህደት የሚደርስ መሆኑ ነበር የተነገረኝ። የፖለቲካ ይዘት ፈጥረውለት እኔ አንገት ለማስደፋት በአደባባይ ውጣና ማስተባበያ ስጥ ብለውኛል። የሚገርመው እኔ ነኝ ፕሮግራሙን የቆረጥኩት ያለው አመራር በዚህ ስብሰባ ውስጥ አንዱ ወቃሽ ሆኖ የተገኘበት ነበር።
    ሰንደቅ፡-በዚህ ስብሳባ ደረሰብኝ የሚሉት ጉዳት አለ?
    ጋዜጠኛ አዲሱ፡- አለ እንጂ። ከዚህ በፊት የኢዲቶሪያል ስብሳባ የምናደርገው አየር ላይ የዋሉ ፕሮግራሞችን ጠንካራና ደካማ ጎናቸውን ለመገምገም ነው። ከዚህ ዜና ጋር በተያያዘ የተደረገው ኢዲቶሪያል ግን መንፈሱን የተለየ ነው። የአንድ ተቋም ኃላፊዎች ተሰብስበው የፖሊስን ስራ በመተካት ያን ሁሉ ወከባ ማስፈራራት ሲፈጥሩ መመልከት በጣም አሳዛኝ ተግባር ነው። በእኔ ውስጥ የፈጠረው ስሜት ለረጅም ጊዜ ውስጤን ጎድቶታል። በተለይ የኢ.ሬ.ቴ.ድ ተጠሪነቱ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መሆኑ ይታወቃል። የምክር ቤቱን ውይይት መቁረጡን በግልፅ መናገሩን ሳይፈራ፣ ለምን እኔን ውይይቱ ተቆርጧል ብልሃል ብሎ ከስራ ሊያሰናብተኝ እንደፈለገ አልገባኝም።
    ሰንደቅ፡-በታህሳስ 01 ቀን 2005 ከዲሲፕሊን ኮሚቴው ወጪ በሆነው ደብዳቤ ላይ “ፕሮግራሙን ያዘጋጁት ባልደረባችን አቶ አዲሱ መሸሻ” የሚል ሲሆን፣ በጥር 20 ቀን 2005 ከዲሲፕሊን ኮሚቴው የወጣው ደብዳቤ በበኩሉ “ፕሮግራሙን ከ90 በመቶ በላይ የሰራው አቶ ሳሙኤል ከበደ” ናቸው ይላል። ከዲሲፕሊን ኮሚቴው በዚህ መልኩ ደብዳቤዎቹ ሊዘጋጁ ቻሉ? ፕሮግራሙን የሰራው ማነው ሊባል ይችላል?
    ጋዜጠኛ አዲሱ፡- ዲሲፕሊን ኮሚቴው ያወጣው ደብዳቤ እርስ በእርሱ የሚጋጭ ነው። ለክሱ እንዲረዳቸው አንድ ደብዳቤ በእኔ አዘጋጁ። ለመከላከል እንዲረዳቸው ደግሞ ፕሮግራሙን ከ90 በመቶ በላይ የሰራው አቶ ሳሙኤል ከበደ ናቸው የሚል ደብዳቤ አዘጋጅ። ይህ በራሱ የሚነግርህ ነገር አለ። በማኛውም ዋጋ እኔ መክሰስ እና ከስራ ማፈናቀል ለዲሲፕሊን ኮሚቴው የተሰጠው ተልዕኮ ነው። አቶ ሳሙኤል በወቅቱ ትምህርት ላይ ነበሩ። እንዴትም እንደመጡ አላውቅም።
    እውነቱ ግን ጥቅምት 24 ቀን 2005 ዓ.ም. ቅዳሜ ፕሮግራሙን ሰርቼ ሙሉ ዝግጅቱ እሁድ ጥቅምት 25 ቀን 2005 ዓ.ም. ከምሽቱ ሁለት ሰዓት ዜና በኋላ የሚቀርብ መሆኑ ነው። በዚህ ዕለት የሚተላለፍ መሆኑን የሚገልፅ ከውይይቱ የተወሰዱ አጫጭር ንግግሮች የሚያሳይ ማስታወቂውን /ስፖት/ የሰራሁትም እኔው እራሴ ነኝ።
    ሰንደቅ፡- አሁን በዚህ መልስ በእርሶ ላይ የተወሰደው እርምጃ በሌላው ሰራተኛ ላይ የሚያሳድረው ተፅዕኖ ምንድን ነው?
    ጋዜጠኛ አዲሱ፡- ይህ ጥያቄ ከነሳህልኝ በውይይቱ ላይ አንድ የተሰነዘረ ነጥብ ልንገርህ። በዚህ ውይይት ከተሳተፉት ተሳታፊዎች መካከል የሥነምግባርና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር የሆኑት አቶ ዓሊ ሱሌማን አንዱ ናቸው። እሳቸው ከገጠማቸው አስቸጋሪ የፀረ-ሙስና ትግል ሲገልፁ፤ “የመልካም አስተዳደርን ለማስፈን የሚታገሉ እና የሙስና ተግባራትን የጠቆሙና ያጋለጡ ሰዎች በአለቆቻቸው የተለያዩ አስተዳደራዊ እርምጃዎች እየተወሰዱባቸው ቤሰቦቻቸው ተበትነዋል። በዚህም የተነሳ እነዚህ ግለሰቦች ምነው ይህን ባልተናገርኩ እያሉ አንገታቸውን ደፍተው ተሸማቀው እየሄዱ ነው። እነዚህ ሃይሎች ገነው ወጥተው ለፀረ-ሙስና ትግል የተሰለፉ ኃይሎች ግን አንገታቸውን ደፍተው ይገኛሉ” ነበር ያሉት።
    ሰንደቅ፡- አሁን እርሶ ላይ የደረሰውን ነገር ከዚህ ከአቶ አሊ ሱሌይማን አባባል ጋር እንዴት ያስታርቁታል?
    ጋዜጠኛ አዲሱ፡- የኮሚሽነሩን አስተያየት በእኔ ላይ መፈጸሙን ስመለከት በጣም አስገርሞኛል። ምክንያቱም በውይይቱ ላይ ተገኝቼ የቀረጽኩት ውይይቱን ለሕዝብ ለማቅረብ እንጂ፣ በዚህ የውይይት ፕሮግራም መቆራርጥ መነሻ እና በመልካም አስተዳደር ዕጦት ሰለባ ለመሆን አልነበረም። የሆነው ግን በእውነት አስገራሚ ነው። ከስራ ተፈናቅያለሁ። ልጆቼን ለጊዜው ለወላጆቼ ሰጥቻለሁ። ባለቤቴን ከፍዬ ነው፤ የማስተምረው። የፓርላማውን ውይይት በፈለጉት መንገድ የቆረጡት ግን ደረታቸውን ነፍተው ለእኔ የስንብት ደብዳቤ ፅፈው ሰጥተውኛል። ኮሚሽነሩም ያሉት ከላይ የዘረዘርኳቸውን ሂደቶች ነበር። ለእሳቸው አስተያየት ከእኔ በላይ ማረጋገጫ ማን ሊያቀርብ ይችላል?
    እዚህ ላይ ማወቅ ያለብህ በጋዜጣችሁ ዝግጅት ክፍል ይህን እድል አግኝቼ ለመናገር ቻልኩ እንጂ ስንቶቹ የሆዳቸውን ይዘው የቢሮክራቶች ሰለባ ሆነው ቁጭ ማለታቸውን መዘንጋት የለብንም።
    ሰንደቅ፡- ተጠሪነታችሁ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ነው። አሁን ደርሶብኛል የምትለውን የመልካም አስተዳደር ችግር በአካል ሄደህ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የባህል፣ የቱሪዝምና መገናኛ ብዙሃን ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ያመለከትከው ነገር የለም?
    ጋዜጠኛ አዲሱ፡- በመጀመሪያ የወሰድኩት እርምጃ እራሴን ማረጋጋት ነበር። በዚህ ጉዳይ አንተ ሶስተኛ ወገን ስለሆንክ እንጂ የተፈጠረው ሁኔታ እጅግ ድፍረት የተሞላበት ነው። መዋሸት የማልፈልገው ከስራ ተሰናብተሃል የሚለውን ውሳኔ ስሰማ ደንግጫለሁ።
    ሰንደቅ፡- ለምን?
    ጋዜጠኛ አዲሱ፡- ምክንያቱም የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለጠራው ስብሳባ ታማኝ ባለመሆኑ ይቅርታ መጠየቅ የነበረበት ኢ.ቴ.ሬ.ድ ነው። ይህን የምለው የእኛ ተቋም አስፈፃሚ መስሪያቤት በመሆኑ ተጠሪ ለሆነበት ተቋም በሰራው ስህተት ይቅርታ መጠየቅ ይገባዋል የሚል እምነት ስለነበረኝ ነው። የሆነው ግን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ውይይት በአግባቡ አልተስተናገደም የሚል መከራከሪያ ባነሳሁት ግለሰብ ላይ፣ የስራ ስንብት ደብዳቤ ሲሰጥ ምን ሊሰማህ ይችላል። እንደዚህ ዓይነት ድፍረት የተሞላበት እርምጃ እንዴት ይወስዳሉ ብለህ ትገምታለህ። ስለዚህም ግራና ቀኙን ለመመልከትና የተፈጠረብኝን ጫና ለመርሳት ወደ ሆነ ቦታ ዞር ማለትን ነበር የመረጥኩት።
    ሰንደቅ፡- ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በዚህ ጉዳይ ምን ትጠብቃለህ?
    ጋዜጠኛ አዲሱ፡- የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በዚህ ጉዳይ ላይ ከእኔ ስራ መፈናቀል በላይ አጀንዳ ያለው ይመስለኛል። ምክንያቱም ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተጠሪ የሆነ ተቋም፣ በምን ምክንያት ውይይቱን ሊቆርጠው ይችላል? ውይይቱ መቆረጡንም ምክር ቤቱ ያውቃል። እዚህ ላይ የሚነሳው ጥያቄ ምክር ቤቱ ውይይቱ እየተቆራረጠ መቅረቡን እንደሚያውቅ እየታወቀ፣ ለምን የሃሰት መረጃ እንዳቀረብኩ ተቆጥሮ ከስራ ገበታዬ እስናበታለሁ? የፓርላማው ውይይት በትክክል አለመዘገቡን በመቃወም ምላሽ መስጠቴ ዋጋው ከስራ መሰናበት ከሆነ፣ ከእኔ የስራ ዋስትና በላይ ፓርላማው ሊመለከተው የሚገባ ጉዳይ ነው። ይህን መሰል ብልሹ የመልካም አስተዳደር ከተለመደ ተቋሙም ወዴት እየሄደ እንደሆነ ቆም ብሎ ማሰብ ተገቢ ይመስለኛል።¾
    (ምንጭ፡- ሰንደቅ ጋዜጣ 8ኛ ዓመት ቁጥር 411 ሀምሌ 17/2005)

    Short URL: http://www.zehabesha.com/amharic/?p=5617

    Tuesday, July 23, 2013

    የዘር ፖለቲካ የትም አያደርሰንም!!

    ለዚህ ፁሁፍ መንደርደሪያ የሆነኝ በፌስቡክ ግድግዳላይ ተፅፎ ያየሁት አስታያት ወይም commentመነሻነት ነው
    ኢትዮ ጵያ ገደል ትግባ የሚል ፁሁፍ አይቼነው በእውነት ለመናገር ቆሽትዬ ነው የደበነው በርግጥ ይህን ግለስብ
    ለዚ አባባሉ ያስነሳው ዓብይ ምክንያት ሰሞኑን በሶሻል ሚዲያው ላይ ትልቅ አነጋጋሪ የሆነውን የንግግር መንሽራተት
    ወይም የአፍወለምታነው የግለሰቡ የንግግር ስተት ምናልባት አንድ ቀን ወደ ራሱ ቀልብ ሲመጣ በይቅርታ ሊስተካከል
    ይችል ይሆናል ሆኖም ገን ትልቋን ኢትዮጵያ ገደል ትግባያለውን ነው የሶስት ሺ ዘመን ታሪክ ያላትን፣ የመጀመሪያ
    የሰውልጅ ዘር መገኛ የሆነችውን፣በጀግንነትና  ለመላው የጥቁር ህዝብ የነፃነት ተምሳሌትና ኩራት የሆነችውን
     በቅዱስ መፃሀፍ ውስጥ 40 ጊዜ የተገለፀች ኢትዮጵያ እጆቿን ወደ እግዛብሔር ትዘርጋለች ተብሎ የተጻፈላት
    እውን ነብር ዥንጉርጉርነቱን ኢትዮጵያዊ ኢትዮጵያዊነቱን አይለውጥም የተባለለት።
           እንግዲ ኢትዮጵያ ስንል የትኛዋን ኢትዮጵያ ነው፧
    እስቲ ያሳያቹሁ የትግራይ ህዝብ እጆቹን ወደ እግዛብሔር፣የኦሮሞ ህዝብ እጆቹን ወደ እግዛብሔር ፣የአማራ ህዝብ
    እጆቹን ወደ እግዛብሔር ወይም ሌሎችም ብሄር ብሄርሰቦች እጆቻቸውን ወደ እግዛብሔር ይዘርጋሉ እንኳን ተብሎ
    አልተጻፈም ወይም አልትገለጸም ሰለዚህ እምዬ ኢትዮጵያ ማለት የነዚህ ሁሉ ብሄር ብሄረሰቦች የድምር ውጤት መሆኖን
    መገንዘብና ማወቅ አለብን ።
          በታሪክ እንደምንረዳው በነብዩ ማህመድ ፍት ህና ሰላም ታገኛላቹሁ ተብለው ወደ ኢትዮጵያ ሂዱነው ተብለው
    የተሰደዱባት ከዚህም የተነሳ ኢትዮጵያኖችን አትንኮቸው ነው የተባለው እንደውም በታሪክ የመጀመሪያ የስደተኛ
    ተቀባይ አገር ሊያስብለን ይችል ይሆናል።
       ስለዚህ ሁላችንም የወያኔ አገዛዝ የጠላናቸውና የምንታገላቸው በጠባብነታቸው ዘረኝነታቸው ነው እንጂ
    አንዳንዶች እንደሚሉት ከሰሜን ሰለመጡ ወይም የትግሪኛ ቋንቋ በመናገራቸው አይደለም በአንደኛ ደርጃ
    አገሪቶን እያስተዳደሩ ያሉት ገዥዎቻችን የኢትዮጵያዊነት ደም ወይም ሞራል ፣ፍቅር ስሌላቸው ነው
    የሁላችንም ትኩረት መሆን ያለበት የሁላችን ጠላት ወደሆነው ወደ ወያኔ ከፋፋይና ጎጠኛ መንገስት ነው
    የችግሮቻችን መፍትሄ የሚገኙት በመነጋገር፣ በመግባባት፣በመቻቻል፣በመደማመጥ እንጂ በመሰዳደብ በዘርኝነት
    የትም አንደርስም ።
        ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!!!!!!
         ዳዊት ወንድሙ!!!!!!!!

    Sunday, July 21, 2013

    ወያኔ የቀረበውን የሚያደማ እሾህ ነው

    ሼህ ይማም ኑሩን ማን ገደላቸው?
    በምርጫ 97 ማግሥት “ድምፃችን ይከበር” በማለታቸው ከሁለት መቶ በላይ ንፁሀን ዜጎች በግፍ መጨፍጨፋቸው በተነሳ ቁጥር የወያኔ ሹማምንት ከሰልፈኞቹ መሀል መሣሪያ የታጠቁ እንደነበሩና ሦስት ፓሊሶችም መገደላቸውን ይናገራሉ። የእነዚያ ፓሊሶች ሞት አሳዛኝ አውነት ሲሆን አሟሟታቸው ግን ጉዳዩን እንዲያጣራ ለተቋቋመው አጣሪ ኮሚሽን እንኳን ምስጢር ነው። ለጊዜው እውነት ተዳፍናለች፤ ፍትህ ተረግጣለች። ጊዜው ሲደርስ ግን የፓሊሶቹ አውነተኛ ገዳይ መውጣቱ አይቀርም። ይኽ ዛሬ ምስጢር የሚመስለን የሦስቱ ፓሊሶች አሟሟት “ንፁሀን ዜጎችን ለመፍጀት ሰበብ ለማግኘት ሲባል በሥራ ገበታቸው ላይ በነበሩ የፓሊስ አባላት የተፈፀመ አጅግ መሠሪና አስነዋሪ ወንጀል” ተብሎ የሚጠቀስበት ወቅት ይመጣል። ይህ የወያኔ ድርጊት ይበልጥ አሳሳቢ የሚያደርገው የአንድ ወቅት የተናጠል ክስተት አለመሆኑ ነው።
    ከአሜሪካ ኤምባሲዎች ሾልከው የወጡ በርካታ ሰነዶች የተዘረገፉበት ዊኪሊክሰ በተሰኘው ድረገፅ የተገኙ መረጃዎች እንደሚያረጋግጡት ወያኔ ሰዎችን ገደሎ በተቃዋሚዎች እንደሚያላክክ አሜሪካ ታውቃለች። ከእነዚህ ሰነዶች አንዱ – ለምሳሌ – ወያኔዎች ሚኒባስ ታክሲ ውስጥ ቦንብ አፈንድተው በተቃዋሚዎች ማሳበባቸው ተብራርቷል።
    ከምርጫ 97ም ሆነ ከዊኪሊክስ በፊትም ሆን በኋላ ወያኔ በእንዲህ ዓይነት አኩይ ተግባራት መካኑ ተከታዮቹና ደጋፊዎቹ የነበሩ ሰዎች የሚመሰክሩት ሀቅ ነው። የሀውዜን ሕዝብ አንዲጨፈጨፍ የተደረገው የትግራይ ሕዝብ በደርግ ላይ እንዲያመር በወያኔ በተረቀቀ ስልት መሆኑ ጉዳዩን በቅርበት የሚያውቁ የቀደሞ አባላቱ ደጋግመው የሰጡት ቃል ያረጋግጣል። በኦሮሞ ማኅበረስብ ተሰሚነት የነበራቸው አቶ ደራራ ከፈኔን በኮሜቴ ውሳኔ አስገድለው በኦነግ ማላከካቸው በወቅቱ ውስጥ አዋቂ የነበረ ጋዜጠኛ በፃፈው መጽሐፍ አሳውቆናል። የወያኔ መሠሪነት ልክም ድንበርም የለውም።
    ከላይ የተዘረዘረው መረጃ ያለው ሰው ሼህ ይማም ኑሩን ማን አንደገደላቸው መገመት አይቸግረውም። ግምቱም ተራ ግምት ነው የሚባል አይደለም። ዋነኛው ተጠርጣሪ መርማሪ በሆነበት ሥርዓት ውስጥ ከዚህ የተሻለ ማስረጃ ማግኘት ይከብዳል። ዋነኛው ተጠርጣሪ መርማሪም ዳኛም በሆነበት ሥርዓት የሼህ ይማም ኑሩ እውነተኛው ገዳይ ለፍርድ እንደማይቀርብ እርግጠኛ መሆን ይቻላል።
    ከዚህ አሳዛኝ የግድያ ድራማ የምንቀስመው ትምህርት ምንድነው?
    ዜጎች ከዚህ የሚከተሉትን ነጥቦች በአንክሮ እንዲያጤኑ ግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ይመክራል።
    1. ወያኔን መጠጋት ከህሊና ጋር ቢያጣላም እንኳን ጥቅም የሚያስገኝ “ቢዝነሰ” አድርጋችሁ ለምታዩ ሁሉ እውነታው የምታስቡትን ተቃራኒ ሊሆን የሚችል መሆኑን እወቁ። ወያኔ ጥቅም የሚያስገኝ መሰሎ ከታየው የራሱንም ሰዎች ለእርድ ያቀርባል። ወያኔ ከራሱ በስተቀር ወዳጅ የለውም። ወያኔ የቀረበውን የሚያቆስል የአጋም እሾህ ነው። ጥቅም የሚያስገኘለት ከሆነ ወያኔ የሚላላኩለትንም የሚበላ አኩይ ኃይል መሆኑን ከሸህ ይማም ኑሩ እጣ ፈንታ እንማር።
    2. ለጊዝያዊ ጥቅም ወያኔን መጠጋት በክፉ ቀን ከጎን የሚቆም አጋርን ማጣት እና የግል ታሪክን ማቆሸሽ መሆኑን እንገንዘብ። በታሪክ ውስጥ ሼህ ይማም የሚታወሱት በእምነት ወንድሞቻቸውና እህቶቻቸው እንደተነሱ ሰው መሆኑ የማይቀር ነው።
    3. ከፋሺስቱ ወያኔ ጋር በመሆን ፍትህ እንዲጓደል፤ ሰቆቃ እንዲበዛ አስተዋጽዖ እያደረጋችሁ ያላችሁ ዳኞች፣ ፓሊሶች፣ የመንግሥትም ሆነ መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማት ሠራተኞች ከዚህ ተግባራችሁ ተቆጠቡ። ወያኔ ለእናንተም አይበጅም።
    ይህንን ምክር አልሰማ ብላችሁ ከወያኔ ጋር በማበር ሕዝብን ለሞት፣ ለእስራት፣ ለሰቆቃ፣ለመፈናቀል፣ ለስደት እና ለእንግልት የምትዳርጉ አድርባዮች ከህሊና ወቀሳ ብቻ ሳይሆን ከቅጣት የማታመልጡ መሆኑን ግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ በጥብቅ ያስታውቃል።
    ድል ለኢተዮጵያ ሕዝብ!

    Friday, July 19, 2013

    EU delegation: Ethiopia should release jailed journalists and activists


    By Associated Press
    ADDIS ABABA, Ethiopia — A European Union parliament delegation on Wednesday called on Ethiopia’s government to release jailed journalists and activists, but in a sign the call may not be heeded the delegation was denied from visiting a prison it had been approved to see.
    The head of the delegation, Barbara Lochbihler, said Ethiopia is jailing journalists and activists for “exercising their legitimate right to freedoms of expression, association and religion.” The group is concerned by reports of misuse of the country’s anti-terrorism legislation to stifle dissent, she said.
    “Despite the country’s excellent constitution, we note flaws in the impartiality of the judicial system,” Lochbihler told journalists at a press conference Wednesday.
    A spokesman for the Ethiopian Prime Minister said the country doesn’t have any political prisoners and that prisoners would not be released “just because some European Union members said so.”
    According to the Committee to Protect Journalists, the Ethiopian government criminalizes the coverage of any group the government deems to be a terrorist group, a list that includes opposition political parties.
    “Among those jailed is Eskinder Nega, an award-winning blogger whose critical commentary on the government’s extensive use of anti-terror laws led to his own conviction on terrorism charges,” the group said in its latest survey, which placed Ethiopia among the world’s top ten worst jailers of journalists.
    The EU parliament delegation said certain broadcasters are jammed in Ethiopia and that access to the Internet and social media are “regularly restricted.” The practice is at odds with the Ethiopian constitution, the delegation said in a statement.
    The four-person delegation, drawn from the parliament’s subcommittee on human rights, said the Ethiopian government must guarantee freedom of speech and the right to peaceful assembly at all times in accordance with its constitution and obligations under international law. The delegation met top government officials, activists and leaders of the opposition.
    Earlier on Wednesday the delegation was scheduled to visit to the country’s Kaliti prison where most activists are believed to be serving their sentence. But the prison director turned the group back on arrival, saying “he didn’t have time to work with you,” according to a member of the delegation, Jorg Leichtfried.
    Leichtfried told a news conference their visit was “overshadowed” by the incident. He described it as an episode he doesn’t wish to experience again. All four delegation members spoke about the incident, which appeared to have frustrated them.
    The delegation said Ethiopia itself has requested international assistance to improve its detention centers and their visit was to have a firsthand experience of the detention conditions.
    Getachew Reda, a spokesman for Ethiopian Prime Minister Hailemariam Desalegn, said he was not aware of any decisions either to grant permission to see the prison or to deny it. Getachew said only family members can visit the prisoners.
    “We don’t have any single political prisoner in the country. We do have, like any other country, people who were convicted of crimes including terrorism who are currently serving their sentence. They would only be freed when either they complete their sentence or probation on good behavior,” Getachew told the Associated Press on Wednesday. “We are not going to do release anyone just because some European Union members said so.”
    He criticized the delegation’s statement, calling it “unhelpful” to relations between Ethiopia and the EU.
    The EU is one of Ethiopia’s largest donors with millions of dollar spent on development projects across the country.
    Hailemariam was scheduled to meet the visiting delegation on Wednesday night.
    The European lawmakers also met with African Union officials. Lochbihler criticized Nigeria and the AU for allowing Sudanese President Omar al-Bashir to travel to Abuja earlier this week. The International Criminal Court has an arrest warrant out for Bashir.
    Copyright 2013 The Associated Press. All rights reserved. This material may not be published, broadcast, rewritten or redistributed.

    አዜብ መስፍን ከአቶ ገ/ዋህድ፣ አቶ ነጋና ምህረተአብ ጋር በመመሳጠር በ3 መርከብ ስሚንቶ አስጭነው በማስገባት የሙስና ወንጀል መፈፀማቸውን ምንጮች አጋለጡ (ከኢየሩሳሌም አርአያ)

    (ከኢየሩሳሌም አርአያ)
    ወ/ሮ አዜብ መስፍን ከአቶ ገ/ዋህድ፣ አቶ ነጋና ምህረተአብ ጋር በመመሳጠር በሶስት መርከብ ስሚንቶ አስጭነው አገር ውስጥ በማስገባት ከፍተኛ የሙስና ወንጀል መፈፀማቸውን ምንጮች አጋለጡ። በተከለከለ ፍራንኮ ቫሉታ ፈቃድ አገር ቤት የገባው ስሚንቶ በመቶ ሚሊዮን የሚቆጠር ትርፍ አዜብና ግብረአበሮቻቸው እንደዛቁበት ያረጋገጡት ምንጮቹ፣ አያይዘውም ጉዳዩ በደህንነት ሹም አቶ ጌታቸው አሰፋ እጅ እንደገባ አስታውቀዋል። በሕገወጥ መንገድ የውጭ ምንዛሪ በከፍተኛ ደረጃ በመመደብና አስፈላጊውን ትእዛዝ በመስጠት እንዲሁም የጥቅም ተካፋይ በመሆን ግንባር ቀደም ሚና የተጫወቱት አዜብ መስፍን ከዚህ ድርጊታቸው በተጨማሪ ከዚህ ቀደም ከስሚንቶው ጋር በተያያዘ ተመስርቶ የነበረውን ክስ እንዲቋረጥ ማድረጋቸውን የጠቆሙት ምንጮች፣ ይህና ሌሎች ተያያዥ የወንጀል ድርጊቶችን የሚያስረዱ ማስረጃዎች በአቶ ጌታቸው እጅ እንደገቡ አረጋግጠዋል። አቶ ነጋ ገ/እግዚያብሄር በኮንትሮባንድ ቀረጥ ሳይከፈልባቸው ወደ አገር ውስጥ ያስገቧቸው የህክምና መሳሪያዎች ተይዘው ክስ ከተመሰረተባቸው በኋላ ክሱ እንዲቋረጥ ያደረጉት አዜብ መሆናቸውን የገለፁት ምንጮቹ፣ በተለያዩ ጊዜያት የገቡና የነጋ ገ/እግዚያብሄር ንብረት የሆኑ ከባድ ተሽከርካሪዎች ያለቀረጥ እንዲገቡ በማድረግ አዜብ መተባበራቸውን አያይዘው ገልፀዋል። ጉዳዩም «ክስ በማቋረጥ..» በሚል በሰነድ ተደግፎና ከሌሎች መሰል ድርጊቶች ጋር ተያይዞ በታሳሪዎች ላይ ክስ የቀረበ ቢሆንም፣ ዋናው ተዋናይ ግን አዜብ ሳይጠየቁ መቅረታቸው አነጋጋሪ መሆኑን ምንጮቹ አልሸሸጉም። ከስሚንቶው ጋር በተያያዘ አስተያየት የጠየኳቸው ታዋቂ የሆኑ ከፍተኛ የኢኮኖሚ ባለሙያ ፥ « መንግስት ስለ ፍራንኮ ቫሉታ ሕግ አውጥቷል፤ ይህን በመተላለፍ ሶስት መርከብ ስሚንቶን የሚያክል ነገር በታሳሪዎቹ ብቻ ሊፈፀም አይችልም፤ ከዚህ ሕገወጥ ድርጊት በስተጀርባ ትልቅና ቁልፍ ስልጣን ያለው ሰው እጁ እንዳለበት ግልፅ ነው።» ብለዋል።
    በተያያዘም ስለ ነጋ ገ/እግዚያብሄርና ገ/ዋህድ ወ/ጊዮርጊስ የጀርባ ታሪክ በተመለከተ ምንጮቹ ተከታዩን መረጃ አስቀምጠዋል፤ “ ሕወሐት/ኢህአዴግ ወደ ስልጣን ሲመጣ የአቶ ነጋ ስራ የመኪና ድለላና ኮረዶችን ከባለስልጣናት ጋር የማገናኘት የድለላ ተግባር ላይ ተሰማርቶ እንደነበረ ይገልፃሉ። በተለይ ሴቶችን እየመረጠ ለበርካታ የገዢው ሹማምንት ለወሲብ ከማቅረብ ጎን ለጎን የሕወሐት ቁልፍ ባለስልጣናትን በእጁ የማስገባት አጋጣሚ ፈጥሮለታል ፥ ይላሉ ምንጮቹ። ከባዶ ተነስቶ ሚሊየነር የሆነበት ምስጢሩ አዜብ መስፍን መሆናቸውን ያሰምሩበታል። ለዚህም «ነፃ ትሬዲንግ፣ ባሰፋና…» ሌሎች ከፍተኛ የቢዝነስ ተቋማቱና በሕገወጥ የዘረፋ ተግባር በድፍረት ተሰማርቶ መቆየቱን ከሞላ ጎደል ይጠቅሳሉ። በባለስልጣናቱ ተረማምዶ ከአዜብ ጋር በፈጠረው <ልዩ ቁርኝት> የተገኘ ሃብት እንደሆነ ይገልፃሉ። ከአዜብ ጋር በማሌዢያና ለንደን የፈፀሟቸው አስነዋሪ ተግባራት የሚያሳዩ የምስል ማስረጃዎች በደህንነት ሃላፊው እጅ እንደገቡ የጠቆሙት ምንጮቹ፣ የሁለቱን ግንኙነት በተመለከተ አብዛኛው የሕወሐት አመራር ጠንቅቆ እንደሚያውቀው አስታውቀዋል። አቶ ነጋ በቁጥጥር ስር ሲውሉ ማመን ተስኗቸው ከማንገራገራቸው ባሻገር፥ «..ለአዜብ ስልክ እንድደውል ፍቀዱልኝ?» በማለት መማፀናቸውንና ደህንነቶቹ እንዳልተቀበሏቸው ምንጮቹ አመልክተዋል። በሌላም በኩል ከአዜብ ጋር ተመሳሳይ <ግንኙነት> ያላቸው ሌሎች ሁለት ባለሃብቶች፥ አንዱ 40 ሚሊዮን የፈጀ ባለስድስት ፎቅ የቢዝነስ ተቋም (ቦሌ ከሜጋ አጠገብ) አዜብ በለገሱት ገንዘብ እንዲገነባ ሲደረግ፣ ከዚህ ግለሰብ ጋር በተደጋጋሚ በዱባይ በውቂያኖስ ላይ በተገነባውና የቱጃሩ አልወሊድ ቢንጣለል ንብረት በሆነው “ኪንግደም” ባለ4 ኮከብ እጅግ ዘመናዊ ሆቴል እንደተገናኙ፣ እንዲሁም ሌላኛው የአንድ ቢሊየን ብር ባለሃብት ሆኖ ከፍተኛ ደረጃ እንዲደርስ አዜብ ማድረጋቸውን ምንጮቹ አጋልጠዋል።
    የአቶ ገ/ዋህድ ማንነት በተመለከተ ምንጮቹ ይህን ይላሉ፤ « ገ/ዋህድ የኢሰፓ አባል ሆኖ በአስመራ እስከ 1982ዓ.ም ያገለግል ነበር። በዚሁ አመት መጨረሻ በራማ በኩል አድርጎ ሕወሐትን ተቀላቀለ። በወቅቱ በመቀሌ እንዲቋቋም በተደረገውና የቀድሞ የደርግ ከፍተኛ መኮንኖች (ምርኮኛ) የተካተቱበት <ኢዴመአን> የተባለ ድርጅት መስራች አባል ነበር – ገ/ዋህድ። በ1983 ዓ.ም የሁለት ሳምንት ወታደራዊ ስልጠና ወይም በድርጅቱ አጠራር “ተአለም” ከወሰደ በኋላ በአጋጣሚ ፓርቲው መላ አገሪቱን እንደተቆጣጠረ ምንጮቹ ያመለክታሉ። በሲቪል ሰርቪስ አልፎ ደቡብን ከጀርባ እንዲመሩ ከተመደቡት አቶ ቢተው በላይ ጋር በአዋሳ ተመደበ። በ1993ዓ.ም በተፈጠረው የፓርቲው መሰንጠቅ አመቺ አጋጣሚ የተፈጠረለት ገ/ዋህድ የክልሉን ፕ/ት አቶ አባተ ኪሾን፣ ቢተው በላይና ሌሎችም እንዲታሰሩ በማድረግ ከፍተኛ ሚና ተጫወተ። ለዚህ ታማኝነቱ የላቀ ቦታ በመለስ ማግኘት እንደቻለና ከዛ በኋላ በየቀኑ ከአዜብና መለስ ጋር በስልክ ይገናኝ እንደነበረ በፈለገው ጊዜ ቤተመንግስት ይገባና ይወጣ እንደነበረ ምንጮቹ አረጋግጠዋል። በአዜብ መልካም ፈቃድ በጉምሩክ ወሳኝ ስልጣን እንዲጨብጥ መደረጉንም አክለው ገልፀዋል። ከአዜብና ሸሪኮቻቸው ጋር በመነጋገርና በመመሳጠር ስሚንቶና ሌሎች ቁሳቁሶች በህገወጥ መንገድ ቀረጥ ሳይከፈልባቸው አገር ቤት እንዲገቡ በማድረግ ከፍተኛ ሚና የተጫወተው ገ/ዋህድ፣ በሚሊዮን የሚገመት ሃብት ከዘረፋው እንዳተረፈም ተመልክቷል። ባለቤቱ ኮ/ል ሃይማኖትም እንዲሁ አዜብ በሚመሩት የሴቶችና ፀረ-ኤድስ ተቋም በምክትል ሃላፊነት እንዲመደቡና በየአመቱ ከአሜሪካ ብቻ እስከ 240 ሚሊዮን ዶላር በእርዳታ መልክ የሚገኘውን ገንዘብ በግልፅ በመዝረፍ ተባባሪ ሆነው መቆየታቸውን ምንጮቹ አስታውቀዋል።
    Short URL: http://www.zehabesha.com/amharic/?p=5428

    Wednesday, July 17, 2013

    ኢትዮጵያዊነት ሁሌም ጀግንነት ነው

    ኢትዮጵያዊ ሆኖ መፈጠር በራሱ ኩራት ነው ይህን ለማለት ያስቻልኝ ቅደምትና ስመገናና የሆነቸውን ሀገራችንን ለማጥፋት
    በተለያዩ ዘመናቶች ጠላቶች ተነስተዋል ሆኖም ግን ሁሌም ነፃነት ፈላጊው ህዝብ ሁሉንም እንዳአመጣጠቻው ምክተው
    ደማቸውን አፍስሰው አጥንታቸውን ከስክስው ድልአድርገዋል የአባቶቻችን ደማቅ ታሪክ እና የስንደቃ ዓላማ ያነገባው
    ትውልድ አሁንም ታሪኩን እየደገመ እያሳየ ነው።
     ከምርጫ 97 በኃላ የታፈነው ህዝባችን ከ8 ዓመት በኃላ
    የስላማዊ ትግሉን በስማያዊ ፓርቲ መሪነት በአዲስ አበባ ተጀምሮ በአንድነት ፓርቲ አስተባባሪ ነት በጎንደር እና በደሴ
    የቀጠላው ሰላማዊ ሰልፍ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት በቀጣይም ህዝቡን የማነሳሳት ተግባራት ወደ
    ባህርዳር፣ድሬደዋ፣ጅማ፣ነቀምት፣አዋሳ፣ስሜን ሽዋ ደብረብርሃን እና ሌሎችም ከተሞች ማስፋፋት ይገባል አንባገነኖችን
    ከስልጣን የማውርድ የትግሉ ሂደት አንዱ አማራጭ ነው ከግብፅ መማር ያልበን አብይ ጉዳይ ነው በአንድ አመት ወስጥ
    ሁለት መንግስት ከስልጣን ለማውረድ ያስቻላቸው የህዝብ በአንድነት የመቆምና ነፃነቱን በሰላማዊ ተቃውሞ በመገለፅ ነው።
           በተለይም የዘርና የጎጥ እርኩስ መንፈስ መርዙን የሚረጭብን የወያኔ አንባገነናዊ አገዛዝ ከስር መሰርት ገልብጠን ህዝባዊ መንገስት የመመስርቻው ግዚው አሁን ነው በሀገሩስጥ ያሉት ወገኖቻችን ፊት ለፊት ወያኔ በሚጋፈጡበት ሁኔታ
    በተለያዩ አገራት የምንኖር ኢትዮጵያዊያን ከጎናቸው በመስለፍ ወገናዊነታችንን በማሳየት ትግሉን ማፋፋም እና ወያኔን
    ግራማጋባት ነው።
      ዳዊት ወንድሙ

    Tuesday, July 16, 2013

    “ኢህአዴግ አንገቱን ታንቋል” ዓለም ባንክ ርምጃ ለመውሰድ ጫፍ ደርሷል

    /ዜና ጎልጉል/ ኢህአዴግ ላይ ቀደም ሲል ሲቀርቡበት ከነበሩት ሪፖርቶች በተለየ ጥቅሞቹ ላይ ያነጣጠሩ አስደንጋጭ መረጃዎች እንደወጡበት ተሰማ። መረጃው የኢህአዴግን አንገት የማነቅ ያህል እንደሚቆጠርና ለተግባራዊነቱ የተንቀሳቀሱትን አካላት “የአስተዋይነት” ትግል ውጤት እንደሆነ ተጠቁሟል።
    ኢህአዴግ በህዝብ ስም በብድርና በርዳታ የሚያገኘውን ከፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብ ለፖለቲካ ስራ እንደሚያውለውና ለአፈና ተቋማቱ ማጠናከሪያ እንደሚጠቀምበት የተከሰሰበት ሪፖርት መጠናቀቁን የገለጹት የጎልጉል ታማኝ ምንጮች ናቸው። ምንጮቹ እንዳሉት ሪፖርቱ የቀረበለት የዓለም ባንክ በቅርቡ መረጃውን ተቀብሎ ርምጃ ይወስዳል ተብሎ ይጠበቃል። ኢህአዴግ ርምጃው ተግባራዊ ከመሆኑ በፊት ለማክሸፍ የተለመደውን ሩጫ መጀመሩ ተሰምቷል።
    በኢህአዴግ ላይ የቀረበው ሪፖርት የመፍትሄ ሃሳብም ያካተተ እንደሆነ የተናገሩት የጎልጉል ምንጮች፣ የዓለም ባንክ የሥራ አስፈጻሚ ቦርድ ሪፖርቱን ሙሉ በሙሉ እንደሚቀበለውና ይፋ እንደሚያደርገው አስረድተዋል። የምርመራ ዘገባውን ስላጠናውና ስላቀረበው የኢንስፔክሽን ተቋምና የስራ ተሞክሮ በቂ ግንዛቤ ያላቸው እነዚህ ክፍሎች እንደሚሉት የዓለም ባንክ ቦርድ ይህ ተቋም ከዚህ ቀደም በተመሳሳይ ያቀረባቸውን ሪፖርቶች ላለመቀበል አንገራግሮ እንደማያውቅ ያስረዳሉ።
    በሚመሩት ህዝብ ላይ ግፍ የሚፈጽሙ መንግስታትና በልማት ስም የሰብዓዊ መብት ጥሰት የሚያካሂዱ አገራት የሚፈጸሙ ወንጀሎችን በስፍራው በመገኘትና መረጃዎችን ከመሠረታቸው ዘልቆ በመመርመር  አጥንቶ ተጠያቂ የሚያደርገው ኢንክሉሲቭ ዴቨሎፕመንት ኢንተርናሽናል Inclusive Development International (IDI) የሚባለው ተቋም ከኢትዮጵያውያኑ ሰለባዎች ውክልና በመውሰድ ስራውን ለማከናወን እንቅስቃሴ መጀመሩን ጎልጉል ምንጮቹን በመጥቀስ መዘገቡ ይታወሳል። ተቋሙም በውክልናው መሰረት ለኢንስፔክሽን ፓናል በዝርዝር የሰለባዎቹን በደል በማተት አሳውቆ ነበር።
    ኢህአዴግ በርዳታና በብድር የሚያገኘውን ከፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብ ለፖለቲካ ስራ፣ ለአፈና፣ ለወታደራዊ አቅም ግንባታ፣ ለተለያዩ የአፈና ተቋም ሰራተኞቹ ደሞዝና ህዝብን በመርገጥ ስርዓቱን ለሚንከባከቡ የተለያዩ ጥቅማጥቅሞችን በመክፈል ገንዘቡን ለመጠቀም ከታለመለት ዓላማ ውጪ እንደሚያውለው በበርካታ መረጃዎች ያረጋገጠው የኢንስፔክሽን ቡድን ለዚሁ ስራው ኬንያ፣ ደቡብ ሱዳንና ኢትዮጵያ በቅርቡ አቅንቶ ነበር።
    ምርመራው ያስደነገጠው ኢህአዴግ በተለያየ መልኩ ሰለባዎች በደላቸውን እንዳይናገሩ፣ በጥቅም የተደለሉ ሰዎችን በየቦታዎቹ በማዘጋጀትና በማስፈራራት አፈና ማካሄዱን የጎልጉል የመረጃ ምንጮች በወቅቱ ቢያስታውቁም ጎልጉል መረጃውን ለስራው መሳካት ሲባል ይፋ ከማድረግ ተቆጥቧል።
    ከቀናት በፊት ሪፖርቱን አጠናቆ ለዓለም ባንክ ቦርድ ያቀረበው የኢንስፔክሽን ቡድን (ፓናል) በማያወላዳ መንገድ ተጽኖ ፈጣሪ ተቋም መሆኑንን ያስረዱት ለስራውና ለተቋሙ ቅርበት ያላቸው ክፍሎች፣ ሪፖርቱን ከቦርዱ አባላት አንዱ እንኳ አልቀበልም ቢሉ ምን ሊከሰት እንደሚችልም አብራርተዋል።
    “አንድ ወይም ከአንድ በላይ የቦርድ አባላት የፓናሉን ሪፖርት ውይይት እንዲደረግበት እስካልጠየቁ ድረስ ፓናሉ ባቀረበው መሠረት እንዳለ ይጸድቃል። ከጸደቀም በኋላ ሪፖርቱ በዓለም ባንክ ስም ይፋ ይሆናል። ሪፖርቱ ታምኖበት ይፋ ከሆነ በሪፖርቱ የቀረቡት የመፍትሄ ጭብጦች ተግባራዊ ከማድረግ ውጪ ሌላ አማራጭ የለም። እስካሁን ባለው አሰራር የፓናሉ ሪፖርት ተቃውሞ አጋጥሞት አያውቅም” ሲሉ መልስ ሰጥተዋል።
    “ይህ ታላቅ ውጤት የተገኘው በእቅድና አስተውሎ በመራመድ ነው። ወደፊትም በቀጣይ የሚከናወኑ ተግባራቶች አሉ። የአገዛዙን ትምክህትና ማን አለብኝነት የሚያረግቡ፣ ብሎም የሚያተኑ ስራዎች ለመስራት ለተጀመረው ስራ ይህ ውጤት ከፍተኛ መነቃቃት ይሆናል” ሲሉ ጉዳዩን በቅርበት በመከታተል እዚህ ያበቁት ክፍሎች አስረድተዋል።
    ምንጭ(www.goolgule.com)

    Ethiopian Police Detain Activists Calling for Terror Law Repeal

    By William Davison - Jul 16, 2013 3:14 PM GMT+0200      Ethiopian police detained 40 opposition supporters distributing leaflets calling for the repeal of an anti-terrorism law they say has been used to stifle dissent, the Unity for Democracy and Justice party said.
    The arrests in four districts of the capital, Addis Ababa, occurred yesterday as UDJ members distributed pamphlets asking people to sign a petition that also demands the release of jailed opposition members, religious leaders and journalists, the party said in an e-mailed statement.
    “It is harassment,” UDJ Chairman Negasso Gidada said in a phone interview today from the capital. “There is no law that says you need permission to distribute leaflets.”
    The mobile phones of government spokesman, Shimeles Kemal, and Bereket Simon, spokesman in the prime minister’s office, were switched off when called for comment. The opposition campaigners were released on bail late yesterday and the group plans to continue gathering signatories for the petition, Negasso said.
    Opposition politicians and reporters have been arrested under an anti-terror law passed by Ethiopia in 2009. The U.S. and United Nations have criticized the legislation for curbing freedom of expression after the arrest of several journalists.
    Online writer Eskinder Nega and Woubshet Taye, former deputy editor of the defunct Awramba Times, were convicted last year under the law for crimes including trying to incite anti-government protests and having links to terrorist organizations.
    Ethiopia’s 547-member parliament has one opposition-party member.
    UDJ held demonstrations on July 14 in two cities to protest the lack of democratic rights under the current government and it is planning to hold more events through September, including in Addis Ababa, Negasso said.
    Its “Millions of Voices for Freedom” campaign follows a public protest in the capital last month by the opposition Blue Party that was the largest demonstration by a political party since 2005 when opposition supporters protested election results.
    To contact the reporter on this story: William Davison in Addis Ababa via Johannesburg atpmrichardson@bloomberg.net.
    To contact the editor responsible for this story: Antony Sguazzin at asguazzin@bloomberg.net.
    source  www.Bloomberg.com

    Monday, July 15, 2013

    የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ተማሪዎች ሕዝበ ክርስቲያኑ ከጎናቸው እንዲቆም ጠየቁ


    የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ተማሪዎች አመጽ እንደቀጠለ ነው። ደቀመዛሙርርቱ (ተማሪዎቹ) ሕዝበ ክርስቲያኑ ከጎናቸው እንዲቆም በመጠየቅ በዛሬው የሥላሴ ክብረ በዓል ላይ የሚከተሉትን መፈክሮች አሰምተዋል።
    የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅን መዝጋት ታሪክን ማጥፋት/ማበላሸት ነው!
    የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ችግራችንን ይመልከት!
    ልጆቹን የማይጠይቅ አባት አለን?
    ሙስናንና ኑፋቄን የሚያደቅ ክንድ አለን!
    የምንማረው በምእመናን ብር ነው፡፡ ሌቦች ሆይ፣ እጃችኹ ይሰብሰብ!
    ጢሞቴዎስ ሆይ፣ አደራህን ጠብቅ፡፡ (፩ኛጢሞ. ፬÷፳)
    ችግራችንን የሚሰማንና መፍትሔ የሚሰጠን አባት ዐጣን!
    የቅ/ሲኖዶሱ አባላት ትኩረት ይስጡን!
    ሙስናን በቃል ሳይኾን በተግባር እንዋጋ!
    ተማሪዎች ሙስናን በመዋጋታቸው ሊበረታታቱ እንጂ ሊባረሩ አይገባም!
    ከአየህጉረ ስብከቱ ቤተ ክርስቲያንን አምነን ወጥተን ለረኀብ ተጋለጥን፡፡
    ኮሌጁ በመዘጋቱ ከተመገብን ሰባተኛ ቀናችን ነው፡፡
    አቤቱ የኾነብንን አስብ፡፡
    ኮሌጁን የሚዘጋው የከፈተው ሲኖዶስ ነው፡፡
    ኮሌጁ የኢትዮጵያ ሕዝብ እንጂ የግለሰቦች አይደለም!
    እውነትን ሙስና አይደለም መቃብር አያሸንፈውም!
    ጌታ ሆይ፣ ከመቅደሳችን ውስጥ የሙስናን እሾኽ ንቀል!
    እየሞትንና እየተራብን ሙስናንና ዘረኝነትን እንቃወማለን!
    ሙስና ከቤተ ክርስቲያናችን ይወገድ!
    ከሓላፊነት መሸሽ በራሱ ሙስና ነው!
    ሐራ ተዋሕዶ ድረ ገጽ እንደዘገበው በነገው ዕለት በመንበረ ፓትርያሪኩ በሚያካሂዱት ከፍተኛ የተቃውሞ ትዕይንት ምእመኑ ከጎናቸው እንዲሰለፍ ጥሪያቸውን አቅርበዋል
    አቡነ ጢሞቴዎስ ደቀ መዛሙርቱን በፖሊቲከኝነት መወንጀል ጀምረዋል
    የተማሪዎች መማክርት የኮሌጁን አስተዳደር በሕግ ለመጠየቅ እየተዘጋጀ ነው
    St Trinity College Disciples demonstrating at the gate of the Patriarchate
    ደቀ መዛሙርቱ በመንበረ ፓትርያሪኩ ቅጽር በተቃውሞ ትዕይንት ላይ
    ምእመናን ቤተ ክርስቲያን ከመሳለምና ገንዘብ ከመስጠት/ከመመጽወት ባሻገር ስለ ቤተ ክርስቲያናቸው ጉዳይ በመጠየቅ ቀጥተኛ ተሳታፊ መኾን እንደሚገባቸው የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ደቀ መዛሙርት አሳሰቡ፡፡
    ደቀ መዛሙርቱ ማሳሰቢያውን ያስተላለፉት፣ በዛሬው የቅድስት ሥላሴ ክብረ በዓል አጋጣሚ በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ለተገኘው ምእመን የኮሌጁ አስተዳደር በትምህርት አመራሩና በአካዳሚያዊ መብቶቻቸው ላይ ስለሚፈጸመው በደል በገለጹበት ወቅት ነው፡፡
    አንጋፋው የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ÷ ሊቃነ ጳጳሳትን፣ የመምሪያ ሓላፊዎችን፣ የአድባራትና ገዳማት አስተዳዳሪዎችን፣ የዩኒቨርስቲ መምህራንን፣ ተመራማሪዎችን፣ በመንግሥትና መንግሥታዊ ባልኾኑ ድርጅቶች በከፍተኛ ሓላፊነት ላይ የሚገኙ ቀደምት ምሩቃንን ያፈራ መኾኑን ደቀ መዛሙርቱ ለምእመናኑ አስታውሰዋል፡፡
    ኮሌጁ አገልግሎቱን የሚያከናውነው ‹‹በእናንተው ገንዘብ ነው›› ያሉት ደቀ መዛሙርቱ፣ ‹‹የምእመኑ ሥራ ገንዘብ መስጠት ብቻ አይኹን፤ ስለ ቤተ ክርስቲያናችኹ ጠይቁ፤ ይህ ኮሌጅ የሕዝብ ነው፤ ነገር ግን የገጠር አብያተ ክርስቲያን እየተዘጉ፣ መናፍቃን እንደ አሸን ፈልተው ቤተ ክርስቲያኒቱን እንደ ቅርጫ ሥጋ ሊከፋፍሏት ባሰፈሰፉበት ወቅት በግለሰቦች እየተዘጋ ነው›› በማለት ከአስተዳደሩ ጋራ ሙስናን፣ ኑፋቄንና ብልሹ አሠራርን በመቃወም የገቡበትን ውዝግብ በሰፊው አብራርተዋል፡፡
    ወደ መንበረ ፓትርያሪኩ ከዐሥር ጊዜያት በላይ በጋራና በተወካዮቻቸው በመመላለስ ጥያቄዎቻቸውን ሲያቀርቡ መቆየታቸውን የገለጹት ደቀ መዛሙርቱ በጥበቃ እየተገፈተሩ ያለውጤት ከመንገላታት በቀር ያገኙት ነገር ባለመኖሩ ምእመኑን፣ ‹‹በየብሔረሰቡ በተለያየ ቋንቋ ቤተ ክርስቲያንን የምናገለግል ልጆቻችኹ ነን፤ ሙሰኞቹ ኀያላን ናቸውና ርዱን! ነገ በጠቅላይ ቤተ ክህነት በሁለት ሰዓት በምናደርገው እንቅስቃሴ አብራችኹን ቁሙ!!›› ሲሉ በከፍተኛ አጽንዖት ተማፅነዋል፡፡
    Short URL: http://www.zehabesha.com/amharic/?p=5271

    Sunday, July 14, 2013

    በደሴ ከተማ ሐምሌ 7 ቀን 2005ዓ.ም. በተደረገው ህዝባዊ ሰላማዊ ሰልፍ ላይ የአንድነት ፓርቲ የደቡብ ወሎ ዞን ሰብሳቢ አቶ ብስራት አቢ ያደረጉት የመዝጊያ ንግግር

    ክቡራን የአንድነት ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች፣ክቡራን የደቡብ ወሎ ዞን የአንድነት ፓርቲ አመራሮች፣አባላትና ደጋፊዎች እንዲሁም ጥሪያችንን አክብራችሁ የተገኛችሁ ክቡራን የኃይማኖት አባቶች ፣ የደሴ ከተማና የአካባቢው ነዋሪዎች በሙሉ ፡-
    በቅድሚያ ለዚህ ታሪካዊ ህዝባዊ የተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፍ በመገኘታችሁ በፓርቲውና በራሴ ስም ልባዊ ምስጋናዬን አቀርባለሁ፡
    ክቡራን የዚህ ህዝባዊ የተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፍ ታዳሚዎች፤ ፓርቲያችን አንድነት ገዥው የኢህአዴግ መንግስት በሀገሪቱ ዜጎች ላይ በተደጋጋሚ የሚፈፅማቸው ህገ መንግስቱን የጣሱ በርካታ ተግባራት በመኖራቸው ፓርቲያችን ከተግባሩ እንዲቆጠብ በተደጋጋሚ በደብዳቤና በጋዜጣዊ መግለጫ መጠየቁ ይታወሳል፡፡
    ይሁን እንጂ ሁላችንም እንደምናውቀው የኢህአዴግ መራሹ መንግስት በዜጎች ላይ የሚፈፅመው ህገወጥ ተግባር ተጠናክሮ በመቀጠሉ በደብደቤና በጋዜጣዊ መግለጫ ብቻ መጠየቁ መፍትሄ ባለማስገኘቱ በሀገራችን ህገ መንግስት አንቀፅ 30 ንዑስ አንቀፅ 1 መሰረት የዛሬውን ህዝባዊ የተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፍ እንድናደርግ ተገደናል፡፡
    በዚህ ተቃውሞም በዋናነት ፓርቲያችን 4 አበይት ነጥቦችን በማንሳት የኢህአዴግ መንግስት ጥያቄያችንን ተቀብሎ በአስቸኳይ ስህተቶቹን እንዲያርም የምንጠይቅ ሲሆን፤ እነኚህም፡
    1.የፀረ-ሽብርተኝነት አዋጁ ህገ መንግስቱን የሚጥሱና የዜጎችን ሐሳብን በነፃነት የመግለፅ መብት፣ የአመለካከትና የኃይማኖት ነፃነትን በነፃነትና በራስ ፈቃድ ለመከተል የሚያስችለውን ተፈጥሯዊ ሰብዓዊ እና ህገ መንግስታዊ መብቶችን የሚጥሱ በርካታ አንቀፆች በመያዙ እንዲሰረዝ እና በምትኩ የሀገሪቱን ዜጎች ሁሉ በእኩልነት ሊጠብቅና ሊጠቅም የሚችል ህግ እንዲወጣ፣በዚህ ህግ ሰበብ የታሰሩ የህሊና እስረኞች በተለይም የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮችና አባላት፣ጋዜጠኞች እና የኃይማኖት ነፃነት መብት ጠያቂዎች በአስቸኳይ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲፈቱ፣
    2. የኑሮ ውድነቱ ከዕለት ወደ ዕለት እየተባባሰ በመሄዱ እና ለራሳቸው፣ለቤተሰቦቻቸውና ለሀገራቸው እንዲሁም ለዓለማችን በጎ አስተዋፅዖ ያላቸው ወጣቶች ላይ በሰፊው እየታየ ያለው ስራ አጥነት የገዥው ፓርቲ ስርዓት የተሳሳተ ፖሊሲ በመሆኑ በአስቸኳይ እንዲታረም፣
    3. ዜጎችን በሚናገሩት ቋንቋንና ዘርን ብቻ መሰረት በማድረግ የሚደረግ ማፈናቀል በአስቸኳይ እንዲቆም፣ የድርጊቱ ፈፃሚዎችም ለፍርድ እንዲቀርቡ እና ከሚኖሩበት አካባቢ በግፍ ለተፈናቀሉ ዜጎችም ተገቢው ካሳ እንዲፈፀም፣
    4.መንግስት በኃይማኖት ጣልቃ አይገባም የሚለው ህገ መንግስት እንዲከበርና መንግስት ከኃይማኖት ጣልቃ ገብነት እጁን እንዲያወጣ እንጠይቃለን፡፡

    ይህ በእንዲህ እንዳለ አምብገነኑ ኢህአዴግ ዜጎችን ማፈኑን ሳያቆም አንድነት ፓርቲ የዓባይ ግድብን አይደግፍም የሚለው ፕሮፖጋንዳ ሐሰት መሆኑን እያረጋገጥኩ አባላቱ ለግድቡ ከሰጡት የገንዘብ ድጋፍ በተጨማሪ ባካበቱት እውቀትና ሙያ ማገልገል ቢፈልጉም እስካሁን ቀን ምላሽ እንዳልተገኘ በዚህ አጋጣሚ መግለፅ እወዳለሁ፡፡
    የአባይ ግድብ የመላው ኢትዮጵያ ህዝብ የሁልጊዜም የህልውና ጥያቄ በመሆኑ ዛሬም ድጋፋችንን እንቀጥላለን፡፡ ነገር ግን ኢህአዴግ ለርካሽ የፖለቲካ ፕሮፖጋንዳ የሚጠቀምበትን አካሄድ እንቃወማለን፡፡ከዚህ በተጨማሪ ሙስና ኢህአዴግ ከከፍተኛ አመራሩ እስከ ዝቅተኛ ካድሬው ድረስ የሚፈፀም መለያ ባህሪው በመሆኑ ይህንንም አጥብቀን እንቃወማለን፡፡ በንግዱ ማኀበረሰብ ላይም የሚጣለውን ኢ-ፍትሐዊና ህገወጥ ከፍተኛ ግብርንም እንቃወማለን፡፡
    ክቡራትና ክቡራን ፡- በአሁን ወቅት ከላይ በተጠቀሱት ምክንያቶች በዜጎች መካከል ገዥው መንግስት ልዩነትና አድሎዓዊነትን በመፈፀም የሀገሪቱን ሰላምና መረጋጋት እንዲሁም አንድነት እያናጋ በመሆኑ ይህም በአስቸኳይ እንዲቆም አጥብቀን እንጠይቃለን፡፡
    በመጨረሻም ፡-እኛ ይህንን ህጋዊና ሰላማዊ የተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፍ በኢትዮጵያዊ ጨዋነት የማንንም መብት ሳንነካ በሰላማዊ መንገድ እንዲጠናቀቅ በመደረጉ እና ጥያቄያችንንም በአደባባይ በማቅረባችን ከሚመለከተው የመንግስት አካል ተገቢውን መልስ እንደምናገኝ፤ ጥያቄያችን ከሚመለከተው አካል ተገቢውን መልስ ካላገኘ ህጋዊና ሰላማዊ ትግላችንን አጠናክረን እንደምንቀጥል እንገልፃለን፡፡
    ለፈጣሪውና ለህሊናው የሚኖሩ እንጂ ለሆዱ የሚገዛ ትውልድ ኢትዮጵያ አትሻም!!
    ለዚህ ሰላማዊ ሰልፍ መሳካት አስተዋፅዖ ላበረከቱ የደሴ ከተማና አካባቢዋ ነዋሪዎች፣ የአንድነት ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች፣ እንዲሁም የደቡብ ወሎ ዞን እና የደሴ ከተማ አስተዳደር እና የፀጥታ ኃይሎች ላደረጋችሁልን ቀና ትብብር በደቡብ ወሎ ዞን የአንድነት ፓርቲ አባላትና አመራሮች እንዲሁም በራሴ ስም ከልብ አመሰግናለሁ፡፡

    Saturday, July 13, 2013

    የነገው ጎንደር እና የደሴው ሰላማዊ ሰልፍ ቅስቀሳ ተጠናክሮ ቀጥሏል

    በደሴ ከተማ በትናንትናው ዕለት ሐምሌ 5 ቀን 2005ዓ.ም. የአንድነት ፓርቲ ሐምሌ 7 ቀን 2005ዓ.ም. ጠዋት ከአራዳ የፓርቲው የደቡብ ወሎ ዞን ጽህፈት ቤት ለሚጀምረው ሰላማዊ ሰልፍ ፓርቲው ከፍተኛ አመራሮች አቶ ግርማ ሰይፉ፣ አቶ በላይ ፈቃዱ፣ አቶ ዳንኤል ተፈራ፣አቶ ፍቃዱ ሰጠኝ ከአዲስ አበባ፤ አቶ ብስራት አቢ፣ አቶ መኳንንት፣ አቶ አንዋር፣ አቶ ከበደ፣ አቶ ሰይድ እና ሌሎች አንድነት ፓርቲ የደሴ ነዋሪዎች በራሪ ወረቀት ሲበትኑ በአማራ ክልል ልዩ ፖሊስና በአድማ በታኝ እንዲያቆሙ በማድረግ ወደ ፖሊስ ጣቢያ ወስደዋቸው ነበር፡፡

    በወቅቱም ከአንድ ካሜራ ባለሙያ ባልደረባዬ ጋር ለቅስቀሳ የወጡት የአንድነት ፓርቲ የደቡብ ወሎ ዞን ኃላፊዎች አቶ ብስራት አቢ፣አቶ መኳንንት፣ አቶ ሰይድ እና አቶ አንዋር በክልሉ ፖሊስ ወደ ተወሰዱበት ደሴ 1ኛ ፖሊስ ጣቢያ ሄደን ስለጉዳዩ ስንጠይቃቸው ፖሊሶቹ እኛ አላሰርናቸውም፣ ነግር ግን ከበላይ አካል ቅስቀሳውን አስቁሙ ብለው ትዕዛዝ ሰጥተውን ነው፤ ለዚህም ልናናግራቸው እንጂ ልናስረዳቸው አይደለም ሲሉ ምላሽ ሰጥተውናል፡፡ እኛም ያዘዛችሁ የበላይ አካል ማን ነው? የፀጥታው ዘርፍ ኃላፊ አቶ ሙሉጌታ በላይን ስንጠይቃቸው እኮ እኛ አልከለከልንም፣ ከልክሉም አላልንም፣ የሚከለክልም የለም ብለውናል፣ እናንተስ በምን የህግ አግባብ ነው ቅስቀሳውን የምትከለክሉት ስል ጥያቄ አቅርቤላቸው ነበር፡፡

    ፖሊሶቹ በበኩላቸው ያዘዘንን አካል ማንነት መግለፅ አንፈልግም፣ ይሄ እኮ ምስጢር ነው፣ ከፈለጋችሁ የከተማው ፖሊስ መምሪያ ጠይቁ ሲሉ ምላሽ ከሰጡ በኋላ የያዟቸውን የአንድነት ፓርቲ አመራሮች ለቀዋቸዋል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ የፓርቲው አመራሮችና አባላት ለነገ ሐምሌ 7ቱ ህዝባዊ ሰላማዊ ሰልፍ ዛሬ ቅዳሜም በራሪ ወረቀቶችን በመበተንና ፖስተር በመለጠፍ የቅስቀሳ ስራ እያደረጉ እንደሚገኙ ለማይት ችለናል፡፡

    በተመሳሳይ ዜና በሰሜን ጎንደር ዞን ጎንደር ከተማ ነገ እሁድ ሐምሌ 7 ቀን 2005ዓ.ም. ለሚደረገው ተመሳሳይ ሰላማዊ ሰልፍ ከአዲስ አበባ የሄዱት የአንድነት ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች አቶ አስራት ጣሴ፣ አቶ ዘካርያስ የማነብርሃን፣አቶ አበበ አካሉ፣አቶ ሀብታሙ አያሌው፤ እንዲሁም የሰሜ ጎንደር ዞን የአንድነት ፓርቲ አመራሮች አቶ አለላቸው አታለል፣ አቶ ጀማል አብደላ፣ አቶ አማረ ስጦታውና የቀጠናው ኃላፊ አቶ አእምሮ አወቀን ጨምሮ አባላቱና ደጋፊዎች የቅስቀሳ ስራ እንዳያደርጉ በፖሊስ ተከበው እየተከለከሉ የነበረ ቢሆንም በመጨረሻ ዛሬ ተፈቅዶላቸው የፓርቲው ሰዎች ቅስቀሳውን አጠናክረው መቀጠላቸው ታውቋል፡፡ እዛው ጎንደር በትናንትናው ዕለት ከአዲስ አበባ ለመረጃ ስራ የተላኩት የፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ ባልደረባ አቶ ወንደሰወሰን ክንፈ እንቅስቃሴውን ሲቀርፁበት የነበረውን ካሜራ ከተማው ፖሊሶች ነጥቀው ክስ መመስረቱ ይታወቃል፡፡

    በሁለቱም በጎንደርና በደሴ ከተማ ነገ እሁስ ሐምሌ 7 ቀን 2005ዓ.ም. ከጠዋቱ 3 ሰዓት የሚደረገውን ህዝባዊ ሰላማዊ ሰልፍ ለመዘገብ ፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ እና የኢትዮጵያ ቴሌቪዥንን ጨምሮ የተለያዩ የሀገር ውስጥና ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙኃን መግባታቸውን ለማየት ችለናል፡፡ የሁለቱም የደሴና የጎንደር ከተማ ነዋሪዎች ሰላማዊ ሰልፉን ለመውጣት እንደተዘጋጁ እየገለፁ ሲሆን መንግስት ሰልፉን ልከልክል ቢል እንኳ ወደ ሰላማዊ ሰልፉ ከመውጣት ወደ ኋላ እንደማይሉ ያነጋገርኳቸው አንዳድ የከተማው ነዋሪዎች አረጋግጠውልኛል፡፡የነገው ጎንደር እና የደሴው ሰላማዊ ሰልፍ ቅስቀሳ ተጠናክሮ ቀጥሏል

    በደሴ ከተማ በትናንትናው ዕለት ሐምሌ 5 ቀን 2005ዓ.ም. የአንድነት ፓርቲ ሐምሌ 7 ቀን 2005ዓ.ም. ጠዋት ከአራዳ የፓርቲው የደቡብ ወሎ ዞን ጽህፈት ቤት ለሚጀምረው ሰላማዊ ሰልፍ ፓርቲው ከፍተኛ አመራሮች አቶ ግርማ ሰይፉ፣ አቶ በላይ ፈቃዱ፣ አቶ ዳንኤል ተፈራ፣አቶ ፍቃዱ ሰጠኝ ከአዲስ አበባ፤ አቶ ብስራት አቢ፣ አቶ መኳንንት፣ አቶ አንዋር፣ አቶ ከበደ፣ አቶ ሰይድ እና ሌሎች አንድነት ፓርቲ የደሴ ነዋሪዎች በራሪ ወረቀት ሲበትኑ በአማራ ክልል ልዩ ፖሊስና በአድማ በታኝ እንዲያቆሙ በማድረግ ወደ ፖሊስ ጣቢያ ወስደዋቸው ነበር፡፡

    በወቅቱም ከአንድ ካሜራ ባለሙያ ባልደረባዬ ጋር ለቅስቀሳ የወጡት የአንድነት ፓርቲ የደቡብ ወሎ ዞን ኃላፊዎች አቶ ብስራት አቢ፣አቶ መኳንንት፣ አቶ ሰይድ እና አቶ አንዋር በክልሉ ፖሊስ ወደ ተወሰዱበት ደሴ 1ኛ ፖሊስ ጣቢያ ሄደን ስለጉዳዩ ስንጠይቃቸው ፖሊሶቹ እኛ አላሰርናቸውም፣ ነግር ግን ከበላይ አካል ቅስቀሳውን አስቁሙ ብለው ትዕዛዝ ሰጥተውን ነው፤ ለዚህም ልናናግራቸው እንጂ ልናስረዳቸው አይደለም ሲሉ ምላሽ ሰጥተውናል፡፡ እኛም ያዘዛችሁ የበላይ አካል ማን ነው? የፀጥታው ዘርፍ ኃላፊ አቶ ሙሉጌታ በላይን ስንጠይቃቸው እኮ እኛ አልከለከልንም፣ ከልክሉም አላልንም፣ የሚከለክልም የለም ብለውናል፣ እናንተስ በምን የህግ አግባብ ነው ቅስቀሳውን የምትከለክሉት ስል ጥያቄ አቅርቤላቸው ነበር፡፡

    ፖሊሶቹ በበኩላቸው ያዘዘንን አካል ማንነት መግለፅ አንፈልግም፣ ይሄ እኮ ምስጢር ነው፣ ከፈለጋችሁ የከተማው ፖሊስ መምሪያ ጠይቁ ሲሉ ምላሽ ከሰጡ በኋላ የያዟቸውን የአንድነት ፓርቲ አመራሮች ለቀዋቸዋል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ የፓርቲው አመራሮችና አባላት ለነገ ሐምሌ 7ቱ ህዝባዊ ሰላማዊ ሰልፍ ዛሬ ቅዳሜም በራሪ ወረቀቶችን በመበተንና ፖስተር በመለጠፍ የቅስቀሳ ስራ እያደረጉ እንደሚገኙ ለማይት ችለናል፡፡

    በተመሳሳይ ዜና በሰሜን ጎንደር ዞን ጎንደር ከተማ ነገ እሁድ ሐምሌ 7 ቀን 2005ዓ.ም. ለሚደረገው ተመሳሳይ ሰላማዊ ሰልፍ ከአዲስ አበባ የሄዱት የአንድነት ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች አቶ አስራት ጣሴ፣ አቶ ዘካርያስ የማነብርሃን፣አቶ አበበ አካሉ፣አቶ ሀብታሙ አያሌው፤ እንዲሁም የሰሜ ጎንደር ዞን የአንድነት ፓርቲ አመራሮች አቶ አለላቸው አታለል፣ አቶ ጀማል አብደላ፣ አቶ አማረ ስጦታውና የቀጠናው ኃላፊ አቶ አእምሮ አወቀን ጨምሮ አባላቱና ደጋፊዎች የቅስቀሳ ስራ እንዳያደርጉ በፖሊስ ተከበው እየተከለከሉ የነበረ ቢሆንም በመጨረሻ ዛሬ ተፈቅዶላቸው የፓርቲው ሰዎች ቅስቀሳውን አጠናክረው መቀጠላቸው ታውቋል፡፡ እዛው ጎንደር በትናንትናው ዕለት ከአዲስ አበባ ለመረጃ ስራ የተላኩት የፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ ባልደረባ አቶ ወንደሰወሰን ክንፈ እንቅስቃሴውን ሲቀርፁበት የነበረውን ካሜራ ከተማው ፖሊሶች ነጥቀው ክስ መመስረቱ ይታወቃል፡፡

    በሁለቱም በጎንደርና በደሴ ከተማ ነገ እሁስ ሐምሌ 7 ቀን 2005ዓ.ም. ከጠዋቱ 3 ሰዓት የሚደረገውን ህዝባዊ ሰላማዊ ሰልፍ ለመዘገብ ፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ እና የኢትዮጵያ ቴሌቪዥንን ጨምሮ የተለያዩ የሀገር ውስጥና ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙኃን መግባታቸውን ለማየት ችለናል፡፡ የሁለቱም የደሴና የጎንደር ከተማ ነዋሪዎች ሰላማዊ ሰልፉን ለመውጣት እንደተዘጋጁ እየገለፁ ሲሆን መንግስት ሰልፉን ልከልክል ቢል እንኳ ወደ ሰላማዊ ሰልፉ ከመውጣት ወደ ኋላ እንደማይሉ ያነጋገርኳቸው አንዳድ የከተማው ነዋሪዎች አረጋግጠውልኛል፡፡(ምንጭ ፍኖተ ነፃነት አዲስ አበባ ጁላይ 13,2013)

    Friday, July 12, 2013

    Delay in return of asylum children

    Norwegian authorities have introduced temporary suspension of the return of unaccompanied asylum children to other European,
    Norwegian authorities have introduced temporary suspension of the return of unaccompanied asylum children to other European countries. Norwegian practice has since 2008 been sending unaccompanied asylum seeking children back to the European country where they applied for asylum and was first registered on arrival in Europe. But after the European Court of Justice in June-defined practices illegal, Norway has temporarily stopped sending children back to the first European country they came from,( Norwegian Broadcast) NRK reported. Justice Ministry stated that the government will see an impact of practice change. Meanwhile celebrate Save the Children.
    This is a very important step in the right direction for the kids involved. It will lead to kids who need it,that they get a really good and thorough consideration of their case in Norway. We are very happy and it is absolutely right of Norway to do so, says Janne Raanes, head of Norway program for Save the Children. Asylum Lawyer Arild Humlen means that the return stop only  could be short-lived. He urged politicians to establish clearer guidelines to ensure the rights of children in immigration law. Figures from the Norwegian Directorate of Immigration (UDI) shows that one in ten unaccompanied minor asylum seekers coming to Norway without parents, also registered in other countries in Europe.
     
    Source : NTB scanpix / Photo Utrop / Norway Today 

    Wednesday, July 10, 2013

    የ35 ሀገራት አምባሳደሮች የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበርን ጠርተው አነጋገሩ

    በዘሪሁን ሙሉጌታ
    በኢትዮጵያ የሚገኙ የ35 ሀገራት አምባሳደሮች የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር የሆኑትን ኢንጂነር ይልቃል ጌትነትን ጠርተው አነጋገሩ። ትናንት በአሜሪካን ኤምባሲ በተካሄደው የአምባሳደሮቹ ስብሰባ ላይ በቅርቡ የተመሰረተውንና በአዲስ አበባ ከተማ በርካታ የህብረተሰብ ክፍሎች የተገኙበትን ሰላማዊ ሰልፍ ማካሄድ የቻለውን ሰማያዊ ፓርቲ ብቻ ጠርተው አነጋግረዋል። በተለምዶ ‘‘የኢትዮጵያ ለጋሾች ቡድን’’ የሚል መጠሪያ ያለውና የአሜሪካንን ጨምሮ በርካታ የአውሮፓ ሀገራት አምባሳደሮች በአባልነት የሚገኙበት የለጋሾች ቡድን በተለያዩ ጊዜያት በሀገሪቱ የሚንቀሳቀሱ ከፍተኛ የተቃዋሚ አመራሮች ጋር በሀገሪቱ ወቅታዊ የፖለቲካ ጉዳዮች ላይ እንደሚወያይ ይታወቃል። የአምባሳደሮቹ ቡድን ትናንት በአሜሪካ ኤምባሲ ባካሄደው ስብሰባ ላይ ሰማያዊ ፓርቲ በተለየ ሁኔታ ተጋብዟል። የፓርቲው ሊቀመንበርም ከአምባሳደሮቹ ጋር አንድ ሰዓት ተኩል የፈጀ ውይይት ማድረጋቸውን በተለይ ለሰንደቅ ጋዜጣ ገልፀዋል። ከአምባሳደሮቹ ጋር በተደረገው ውይይት ላይ የፓርቲው ፖሊሲ ምንነት፣ ፓርቲው በወጣቶች ላይ ከማተኮሩ አንፃር በስራ ዕድል ፈጠራ ላይ ምን አይነት ፕሮግራም እንዳለው፣ የኢኮኖሚ ፖሊሲው ምን እንደሆነ፣ የፌዴራሊዝምና የመሬት ፖሊሲው ምን እንደሚመስል፣ እንዲሁም በኢትዮጵያ የሰሜን አፍሪካና የአረብ ሀገራት አይነት አብዮት ይነሳ ይሆን የሚለው ጨምሮ ሌሎች ፓርቲውን በተመለከቱ ጉዳዮች ላይ ውይይት መደረጉን ኢንጂነር ይልቃል ተናግረዋል። በተጨማሪም የፓርቲው ሊቀመንበር የፓርቲውን ራዕይ የሚያመለክት 10 ገፅ ያለው ፅሁፍ ለአምባሳደሮቹ እንዲደርሳቸው ማድረጉንም ገልፀዋል። ፓርቲው በአምባሳደሮቹ ቡድን ስብሰባ ላይ እንዲገኝ ከአንድ ወር በፊት ጥሪ እንደተደረገለት የጠቀሱት ኢንጂነር ይልቃል፤ 70 ከመቶ የኢትዮጵያ ወጣት ዕድሜው ከ35 በታች እንደመሆኑ፣ ፓርቲው ለወጣቶች የተለየ ትኩረት እንደመስጠቱ፣ የዲፕሎማሲ እውቅና መሰጠቱ ተገቢ መሆኑን የፓርቲው ሊቀመንበር አያይዘው ገልፀዋል። ፓርቲው ከተመሰረተ ጀምሮ በተናጠል ከኤምባሲዎቹ ጋር ሲሰራ መቆየቱን ያስታወሱት ኢንጂነር ይልቃል፤ ነገር ግን በለጋሾች ቡድን አመታዊ ስብሰባ ላይ በይፋ ንግግር እንዲያደርጉ መጋበዛቸው ለፓርቲው ከፍተኛ የፖለቲካ ጥቅም እንዳለውም ገልፀዋል። በተያያዘ ሰማያዊ ፓርቲ በየሳምንቱ ቅዳሜ በሀገሪቱ ፖለቲካ ላይ የወጣቶች ክርክር መድረክ ማዘጋጀት መጀመሩንና ባለፈው ቅዳሜና እሁድ በአዲስ ቪው ሆቴል ከፓርቲ አደረጃጀት ጋር በተያያዘ በፓርቲው የአደረጃጀት ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ 35 ለሚሆኑ የአሰልጣኞች ስልጠና መሰጠቱን የፓርቲው የሕዝብ ግንኙነት አስታውቋል። የአሰልጣኞች ስልጠናው ፓርቲው በቅርቡ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶችን ለመክፈት የቅድመ ዝግጅት ስራ አካል መሆኑንም የፓርቲው የሕዝብ ግንኙነት በላከው መግለጫ አስታውቋል።
    (ምንጭ ሰንደቅ ጋዜጣ አዲስ አበባ ጁላይ 10 2013)
    Short URL: http://www.zehabesha.com/amharic/?p=5130