Wednesday, July 17, 2013

ኢትዮጵያዊነት ሁሌም ጀግንነት ነው

ኢትዮጵያዊ ሆኖ መፈጠር በራሱ ኩራት ነው ይህን ለማለት ያስቻልኝ ቅደምትና ስመገናና የሆነቸውን ሀገራችንን ለማጥፋት
በተለያዩ ዘመናቶች ጠላቶች ተነስተዋል ሆኖም ግን ሁሌም ነፃነት ፈላጊው ህዝብ ሁሉንም እንዳአመጣጠቻው ምክተው
ደማቸውን አፍስሰው አጥንታቸውን ከስክስው ድልአድርገዋል የአባቶቻችን ደማቅ ታሪክ እና የስንደቃ ዓላማ ያነገባው
ትውልድ አሁንም ታሪኩን እየደገመ እያሳየ ነው።
 ከምርጫ 97 በኃላ የታፈነው ህዝባችን ከ8 ዓመት በኃላ
የስላማዊ ትግሉን በስማያዊ ፓርቲ መሪነት በአዲስ አበባ ተጀምሮ በአንድነት ፓርቲ አስተባባሪ ነት በጎንደር እና በደሴ
የቀጠላው ሰላማዊ ሰልፍ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት በቀጣይም ህዝቡን የማነሳሳት ተግባራት ወደ
ባህርዳር፣ድሬደዋ፣ጅማ፣ነቀምት፣አዋሳ፣ስሜን ሽዋ ደብረብርሃን እና ሌሎችም ከተሞች ማስፋፋት ይገባል አንባገነኖችን
ከስልጣን የማውርድ የትግሉ ሂደት አንዱ አማራጭ ነው ከግብፅ መማር ያልበን አብይ ጉዳይ ነው በአንድ አመት ወስጥ
ሁለት መንግስት ከስልጣን ለማውረድ ያስቻላቸው የህዝብ በአንድነት የመቆምና ነፃነቱን በሰላማዊ ተቃውሞ በመገለፅ ነው።
       በተለይም የዘርና የጎጥ እርኩስ መንፈስ መርዙን የሚረጭብን የወያኔ አንባገነናዊ አገዛዝ ከስር መሰርት ገልብጠን ህዝባዊ መንገስት የመመስርቻው ግዚው አሁን ነው በሀገሩስጥ ያሉት ወገኖቻችን ፊት ለፊት ወያኔ በሚጋፈጡበት ሁኔታ
በተለያዩ አገራት የምንኖር ኢትዮጵያዊያን ከጎናቸው በመስለፍ ወገናዊነታችንን በማሳየት ትግሉን ማፋፋም እና ወያኔን
ግራማጋባት ነው።
  ዳዊት ወንድሙ

No comments:

Post a Comment