Sunday, September 28, 2014

ህወሃቶች “አቅም ግንባታ” የሚሉት፤ እኛ ደግሞ “አቅም አድክም” የምንለው ሂደት

september 27,2014
ህወሃት የመምህራንን፤ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎችንና የመንግስት ሠራተኞችን ”አቅም እገነባለው” ብሎ ተነስቷል። ለዚህ “አቅም ግንባታ” እያሉ ለሚጠሩት አሰለቺ እና አደንቋሪ አቅም አድክም ፕሮፖጋንዳ እየወጣ ያለው ወጪ ለሌላ ተግባር ውሎ ቢሆን ኑሮ የተሻለ ይሆን ነበር። የተሻለ ነገር በህወሃቶች መንደር ይሠራል ብሎ መጠበቅ ግን ሞኝነት ነው። ህወሃት የተፈጠረው አገርን ለማፍረሰና ህዝብን ለማስጨነቅ እንጂ የተሻለ ሥራ ሠርቶ ህዝብን ለማስደስት አይደለም።
ህወሃቶች በአፍቅሮተ ንዋይ አብደው አቅላቸውን የሳቱ፤ ለእውቀትና ከእነርሱ በተሻለ ደረጃ ለሚያውቅ ቅንጣትም ታክል ክብር የሌላቸው፤ ውሸት የመኖሪያቸው ድንኳን ሁኖ ለብዙ ዘመን ያኖራቸው ቡድኖች ናቸው። በዚህ ሁኔታ ራሳቸውን የገነቡ ቡድኖች የሌሎችን አቅም እንገነባለን ብለው የመነሳታቸው ነገር አገራችን የገባችበትን የውርደት አዘቀት ፍንትው አድርጎ የሚያሳየን ነው።
የንዋይ ፍቅር የክፋቶች ሁሉ መሠረት ነው። ህወሃቶች በዚህ በክፋት ሁሉ መሠረት በሆነው በንዋይ ፍቅር ያበዱ በመሆናቸው ህወሃቶችን ከክፋት፤ ክፋትን ደግሞ ከህወሃት ለይቶ ለማየት የማይቻልበት ደረጃ ላይ ተደርሷል። እነዚህ ቡድኖች በአፍቅሮተ ነዋይ አብደው ለእብደታቸውም መድሃኒት ጠፍቶ እኛ ከሌለን አገሪቷን እንበትናታለን በሚል ቅዥት ውስጥ እንደሚኖሩም የታወቀ ነው። ህወሃቶች ገንዘብ ሊያሰገኝ የሚችለውን ማንኛውንም ዓይነት ወንጀል ለመፈፀም የሚያቅማሙ አይደሉም። ህዝቡን በሙሉ በገንዘብ የሚገዛ ቢያገኙ ህዝቡን በሙሉ ለመሸጥ ወደ ኋላ ይላሉ ብሎ ማሰብም አይቻልም። ይህን በመሰለ የሞራል ውደቀት ውስጥ የሚገኙ ህወሃቶች የህዝቡን አቅም እንገነባለን ሲሉ ትንሽም አለማፈራቸው አገራችን ከደረሰችባቸው የሞራል ውደቀቶች መካከል አንዱ ሁኖ ሊጠቀስ የሚችል ዓቢይ ጉዳይ ነው።
ህወሃቶች ለእውቀትና ከእነርሱ በተሻለ ደረጃ ማሰብ ለሚችል ሰው ያላቸው ጥላቻ ወደር የለውም። ለዚህም ነው ከእነርሱ መካከል ይሄ ነው ተብሎ ሊጠቀስ የሚችል የተመሰገን የተማረ ሰው የማይገኘው። ለህወሃቶች የተማረ ማለት ሲጠሩት አቤት ሲልኩት ወዴት እያለ ለሆዱ ያደረ እንጂ ለአገሬ፤ ለህዝቤ፤ ለወገኔ ምን በጎ ተግባር ልፈፀም የሚል አስተሳሰብ ያለው ሰው አይደለም። የህወሃቶች ዋነኛው ችግር የተማረ ሰው መጥላታቸው ብቻ ሳይሆን ሁሉንም እኛ እናውቃለን ማለታቸውም ጭምር ነው።ሁሉን እኔ አውቃለሁ ማለት ደግሞ የድንቁርና ታላቅ ምልክት ነው። ከዚህ ድንቁርና ራሱን ማላቀቅ ያልቻለ ቡድን የዜጎችን አቅም እገነባለው ብሎ መነሳቱ ከአስገራሚ በላይ ሁኖብናል።
ውሸት ጥሩ ነገር እንዳልሆነ ከህወሃቶች በቀር ሌላው ሁሉ የሚስማማበት ነገር ነው። ህወሃቶች ግን ውሸትን እንደ ታላቅ የትግል ስትራቴጂ ይቆጥሩታል።ህወሃቶች በግለሰብ ደረጃ ሳይሆን በአገር ደረጃ ሲዋሹ ቅንጣት ታክል እፍረት አይሰማቸውም። እንዲያውም ውሸታቸውን እውነት እንደሆነ አድርገው ያምናሉ። ለምሳሌ ኢኮኖሚው ከ11% በላይ አድጓል ይላሉ። ይሄ አሃዝ እውነት እንዳልሆነ ይታወቃል። ህወሃቶችና የሰበሰቧቸው ኮተታም ካድሬዎች ይሄን ውሸት እውነት ነው ብለው ያምናሉ። በአጠቃላይ ህወሃቶች ስለራሳቸውም ሆነ ስለሚገዙት ህዝብ እውነቱን መናገር ሞኝነት ነው የሚል ፅኑ ዕምነት አላቸው። ይሄን ከመሰለ ፅኑ ደዌ ራሳቸውን ማላቀቅ ያልቻሉ ደካሞች የሌላውን አቅም እንገነባለን ሲሉ አለማፈራቸው ያሳፍራል።
የሰሞኑ አቅም ግንባታ ብለው የሚጠሩት ግርግር ዓላማው እና ግቡ በተሻለ ደረጃ ማሰብ የሚችሉ ዜጎች ልዩ ልዩ አማራጮችን ማየት አቁመው አካሄዳቸውን በሞራልም ሆነ በእውቀት ውዳቂ ከሆነው ከህወሃት ጋር እንዲያደርጉ ለማድረግ ነው። ብዙ ኮተታም ካድሬዎቻቸው ለራሳቸው እንኳ የማይገባቸውን አብዮታዊ ድሞክራሲ የሚባለውን ፍልስፍና አዘረክርከው ይዘው በተማሪዎችና በመምህራን ፊት ያለምንም ዕፍረት ተጎልተው እየዋሉ ነው። እነዚህ ቡድኖች ከእነርሱ በተሻለ ደረጃ የሚያስብውን ኃይል መፍራት ብቻ ሳይሆን ሥር የሠደደ ጥላቻም አላቸው። በዚህ በሚፈሩትና በሚጠሉት ዜጋ መሃል ተገኝተው ለሚጠየቁት ጥያቄ መልስ መስጠት ሲገባቸው ማስፈራራት ዛቻ እና ስድብን የመልሳቸው ማሳረጊያ አድርገውታል።
በመሠረቱ አቅም ግንባታ ሲባል ዜጎች ራሳቸውንም ሆነ አገራቸውን ወደ ተሻለ ደረጃ ሊያደርሱ የሚችሉበትን ሁኔታ በራሳቸው ማመቻቸት የሚችሉበትን አስተሳሰብ እንዲያሳድጉ የሚያስችል ነው። አቅም የሚገነባው የዜጎችን የመጠየቅ እና የመመራመር ችሎታ አዳብሮ የተሻለ አማራጭ እንዲያፈልቁ እንጂ መንግስት የሚለውን ብቻ አምነው እንዲቀበሉ ለማድረግ አልነበረም። የህወሃቶች አቅም ግንባታ ግን ዜጎች ማሰብ አቁመው መጠየቅንም ፈርተው ምንሊክ ቤተ-መግስት ውስጥ ከተተከሉት ዛፎች እንደ አንዱ ሁነው እንዲኖሩ ለማድረግ ነው። እነዚያ ዛፎች መጥረቢያውን ሥሎ ሊገነድሳቸው ለሚያንዥብበው ዛፍ ቆራጭ ገንድሶ እሰከሚጥላቸው ድረስ ጥላ ይሆኑታል። ያ መጥረቢያውን ስሎ የተከለላቸው ሰው ጠላታቸው መሆኑን የማወቅ አቅም ግን የላቸውም። የህወሃቶች የአቅም ግንባታ ግቡ ዜጎች እንደ ዛፉ እንዳያስቡ እና ጠላትን ከወዳጅ የሚለዩበትን አቅም ማዳከም ነው።
ህወሃቶች ከ11% በላይ አድገናል ይላሉ። እደገቱ እውነት ከሆነ ለምን እንራባለን? ለምንስ ዜጎች ስደትን ይመርጣሉ? ለምንስ የጨው፤ የሳሙና፤ የስኳር፤ የቲማቲም እና የሽንኩርት ዋጋ የማይቀመስ ሆነ? ብሎ የሚጠይቅ ዜጋ ጠፍቶ፤ የውሸቱን የ11% እድገት ተቀብሎ የሚኖር ዜጋ የመፍጠር ብርቱ ቅዥት አላቸው።በዚህ ቅዥት ውስጥ እንዳይኖሩ የሚያጋድቸው የለም፤ ውሸታቸውንም አምኖ መኖር የእነርሱ ችግር ነው። የእነርሱ ውሸት አምኖ መኖር አገር የሚያፍረሰው እና ዜጎችን የሚያሰጨንቀው የእኛን ውሸት እመኑ ብለው ወደ ማስገደድ ደረጃ ሲደርሱ ነው። አሁንም እያደረጉ ያሉት ይሄንኑ ነው። የመንግስት ሠራተኞች፤ መምህራንና ተማሪዎች ተገደው የህወሃቶችንን ውሸት እየተጋቱት ይገኛሉ። ኢትዮጵያዊያን ህወሃቶችን ማመን ካቆሙ ብዙ ዘመን ተቆጥሯል። ህወሃቶች በእንግሊዘኛው “ፓቶሎጂካል ላየርስ” ተብለው የታወቁ ናቸው። ይሄ ደግሞ በሽታ ነው። የህወሃቶች ውሽት ወደ በሽታ የተሸጋገረ ስለሆነ በማንኛውም መድረክና ሁኔታ የሚናገሩትን ማመን አይቻልም።ለምሳሌ የአዜብን ስታይል እንመልከት በስልክ ከጋዜጠኛ ሲሳይ አጌና ጋር ስትነጋገር መጀመሪያ “አዎን እኔ አዜብ ነኝ” አለች ከአንድ ደቂቃ በኋላ ተመልሳ ደግሞ “አይ እኔ አዜብ አይደለሁም“ አለች። ይሄ እንግዲህ ውሸት ወደ በሽታ ተሸጋግሮባቸው የመኖሪያቸው ድንኳን መሆኑን ያሰየናል። እንግዲህ ዜጎች የህወሃቶችን ውሸት አንሰማም፤የእናንተንም አቅም ግንባታ አንፈልግም ማለት የሚችሉበት አገር የላቸውም። ዜጎች ይሄን እሰማለሁ፤ ያንን ደግሞ መስማት አልፈልግም የሚባል መብታቸው በህወሃቶች ተገፏል። ይህ የዜጎችን የመምረጥ መብት የገፈፈ ገዥ ቡድን እያደረገ ያለው የዜጎችን አቅም ማዳከም እንጂ የዜጎችን አቅም መገንባት አይደለም።አቅም በግዴታ አይገነባምና።
ህወሃቶች የሙስና ምንጮች መሆናቸው የታወቀ ነው።ከህወሃት መንደር ከሌብነት የፀዳ ባለስልጣን አይገኝም።ሁሉም ሌቦች፤ ሁሉም ሥነ-ምግባር የጎደላቸው ሰው ምን ይለኛልን የማያውቁ ናቸው። እነዚህ ቡድኖች የሚፈፅሙትን ሙስና ማስቆም አገሪቷ ከገጠሟት ፈተናዎች መካከል አንዱ ቢሆንም መቆም ይኖርበታል። ይሄን ሙስና የማስቆም ኃላፊነት ከህወሃቶች እና ከኮተታም ካደሬዎቻቸው ውጪ ያሉ ዜጎችን ሁሉ ትብብር የሚጠይቅ ነው። በዚህ ረገድ መምህራኑና ተማሪዎች ለህወሃቶች ያነሷቸው ጥያቄዎች ተጠናክረው መቀጠል ይኖርባቸዋል። ህወሃቶች በሙስና መጨማለቃቸውን ከሌቦቹ ህወሃቶች በቀር ሁሉም ያውቃል። ህወሃቶች ከእንቅልፋቸው ሲነቁ በሚሊዮን የሚቆጠር ሃብት በእጃቸው ሲገባ የትግሌ ውጤት ይላሉ እንጂ ሰርቄ ነው የሚል አስተሳሰብ በአእምሯቸው ዝር አይልም። የህወሃቶች ትልቁ ችግር የሚፈፅሙትን ዝሪፊያ ሁሉ የትግላችን ውጤት ነው ይገባናል ብለው ከልባቸው ማመናቸው ነው። በዚህ ዓይነት አስተሳሰብ የተቃኘ ቡድን የዜጎችን አቅም ለመገንባት በሚል እያካሄደ ያለው አደንቋሪ ስልጠና ተብየው የዜጎችን አቅም ያዳክም እንደሆነ እንጂ በምንም መሠፍረት የማንንም አቅም አይገነባም።
እነዚህ ቡድኖች ያለ ምንም ዕፍረት ሙስናን እንታገላለን ይላሉ። በሙስና የተጨማለቁ ባላስልጣናት ሙስናን እንዋጋለን ብለው በድፍረት ሲናገሩም ይደመጣል።በሙስና የተዘፈቁ ባላስልጣናት መኖራቸው እየታወቀ ለምን ህግ ፊት አይቀርቡም ተብለው ሲጠየቁ መልስ የላቸውም። ኢታማዦር ሹሙ ሳሞራ የኑስ ዋና ሌባ መሆኑ ይታወቃል፤ በዘረፈው የህዝብ ሃብት የባንክ ቤት ባለድርሻ እሰከመሆን ደርሷል። መላኩ ፈንቴን እንዲታሠር የበየነው ህግ ሳሞራ የኑስን አይነካም። ሁሉም ኢትዮጵያዊ በህግ ፊት እኩል ነው ቢባልም ሳሞራ የኑስና መላኩ ፈንቴን እኩል የሚያይ ህግ በኢትዮጵያ የለም። በዚህ ዓይነት የሞራል ዝቅጠት ውስጥ የሚገኝ ቡድን የሚገነባው አቅም ምንድ ነው? ዜጎችን በምን አቅጣጫ ወደየት ለመውሰድ ያለመ ስልጠና ነው እየተሰጠ ያለው ተብሎ ቢጠየቅም የሚገኘው መልስ ዜጎች ሁሉ እንደ ህወሃት በጎጥ አስተሳሰብ ተተብትበው፤ ሰው ምን ይለኛል ማለትን ረስተው፤ እግዚአብሄርን መፍራት ትተው፤ ግራና ቀኝ ማየትን አቁመው ከአንድ ማሰብ ከማይችል እንስሳ ሳይለዩ እንዲኖሩ ማድረግ ነው።
የግንቦት ሰባት የፍትህ፤ የነፃነትና የዴሞክራሲ ንቅናቄ ህወሃት የተባለውን ዘረኛና ዘራፊ ቡድን ከተቆናጠጠበት የሥልጣን ኮርቻ ላይ አውርዶ አገሪቷን የሁሉም ለማድረግ የሚችለውን እያደረገ ነው። ለኢትዮጵያ ህዝብ አሁን ባለው ተጨባጭ ሁኔታ ከህወሃት የበለጠ ጠላት የለም። ህወሃት ዋነኛው የኢትዮጵያ ሕዝብ ጠላት መሆኑ ሊሠመርበት የሚገባ ነጥብ ነው። ይሄን ጠላት ሳያቅማሙ በሁሉም መስክ መታገል ግዜው የሚጠይቀው ከዜጎች የሚጠበቅ ተግባር ነው።
ተከብሬ የምኖርበት አገር ያስፈልገኛል የሚል ሁሉ ንቅናቄያችንን እንዲቀላቀል ዛሬም ደግመን የትግል ጥሪያችንን እናቀርባለን። እኛ አገር ያሳጡንን ቡድኖች በሚገባቸው ቋንቋን ለማነጋገር ሳንቅማማ የትግሉን ባቡር ተሳፍረናል። የትግሉን ባቡር አሁኑኑ ተሳፈሩና ለሁላችንም የትሆን አገር እንፍጠር።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!
Source www.ginbot7.org

Friday, September 26, 2014

ስልጠና የሚያስፈልገው ላልሰለጠነው የወያኔ ጉጅሌና ሎሌዎቹ ነው!

september 25,2014
አምባገነኖች በውድም በግድም ህዝብ ስብሰባ ጠርተው ህዝቡ ፊት በቆሙ ቁጥር ሌት ከቀን የሚያባንናቸውን የተመረረ ህዝብ የነጻነት አመጽ የሚያስቀሩ ይመስላቸዋል። የህዝብ ሃብትና ጊዜ በከንቱ እንዳሻቸው እያባከኑ፣ ነጋ ጠባ ስብሰባ፣ ግምገማ፣ “ስልጠና” ወዘተ የሚጠሩት ህዝብ የነሱን ፍላጎትና ውሳኔ የኔ ነው ብሎ የሚቀበላቸው፣ የሚሰማቸው እና ፍርሃታቸውን ያቀለላቸው እየመሰላቸው ነው።
የወያኔ ጉጅሌና ሎሌዎቹ ሰሞኑን ተማሪዎችን፣ መምህራንን፣ ሰራተኞችንና መላውን ለፍቶ አዳሪ ተሰብሰብና እናሰልጥንህ የሚሉት በአገዛዛቸው የተንገፈገፈው ህዝብ ምሬቱ ወደ አመጽ እንዳይገነፍል ያደረጉ እየመሰላቸው ነው። ዲሞክራሲንና የህዝብ ወሳኝነትና ልእልናን በተቀበሉ ሀገሮች እንደወያኔና ቀደም ብሎ እንደነበረው የደርግ ስርአት የመንግስት ስብሰባ የማይዘወተረው ለዚህ ነው። የህዝቡን ፍርድ በስብሰባ እና በስልጠና እንደማያቆሙት ስለሚያውቁ ህዝብን ስለሚያከብሩ ነው።
ሰሞኑን በመላ ኢትዮጵያ እየተካሄደ ያለው ወያኔዎች ‘ስልጠና’ ብለው የሚጠሩት፣ በይዘቱ አያቶቻችንን ድሮ ላውጫጪኝ ይጠቀሙበት የነበረውን አፈርሳታ የመሰለ የመደናቆሪያ ስብሰባ አላማው ግልጽ ነው።
አላማው ህዝብ ሰጥ ለጥ ብሎ እንዲገዛ ቢቻል ለማደንዘዝ ካልተቻለም ለማስፈራራት ነው። ግፍን፣ ፍትህ ጥፋትን ልማት፣ ጭካኔን፣ ርህራሄ ለማስመሰል አፈጮሌ ነኝ ያለ ካድሬ ሁሉ የምላስ ጂምናስቲክ የሚሰራበት ጉባኤ ነው። ከተሰብሳቢው ህዝብ ከረር ያለ ጥያቄ በመጣ ቁጥር መላ ቅጡ የሚጠፋቸውም ለዚህ ነው። እነሱ የተዘጋጁት የህዝብ ጥያቄ ለመመለስ አይደለማ! የህዝቡን ጥያቄ እንደማይመልሱማ ያውቁታል።
ነገሩ መልከ ጥፉን በስም ይደገፉ ሆነና ይህንን ቧልት ‘ስልጠና’ ብለው ይጠሩታል። እነዚህ ራሳቸው መሰረታዊ ስልጣኔ የሌላቸው አሰልጣኞች መምህራኑን ስለትምህርት ጉዳይ ሊያሰለጥኗቸው ሲንጠራሩ አይፍሩም። ባለሙያውን ሁሉ በሙያው ካላ ሰለጠንህ ብለው ግዳጅ ስብሰባ ያጉሩታል። ይህ የወያኔ ተግባር እውቀትና ስልጣን ከተምታታባቸው የወያኔ ጉጅሌዎች ስለመጣ ብዙ ላያስገርም ይችል ይሆናል። እንደ ህዝብና እንደ ዜግነታችን ግን በያንዳንዳችን ላይ እየደረሰ ያለ ውርደት ነው። ወያኔ ካላዋረደንና ሰበአዊ ክብራችን ካላሳነሰ የሚገዛን አልመሰለውም።
ግንቦት 7 ውስጥ ያለን የኢትዮጵያ ህዝብ ልጆች ይህ ዘርፈ ብዙ ውርደት እንዲቆም ነው የምንታገለው። የኢትዮጵያ ህዝብ በዚህ ዘመን ይህን በመሰለ ውርደት ውስጥ ሊኖር የሚገባው ህዝብ አይደለም ብለን እናምናለን። የማያቋርጠው ጥሪያችን ዛሬም ተመሳሳይ ነው። ፈልገናቸው ሳይሆን በሃይል ራሳቸውን የጫኑብንን የወያኔ ጉጅሌዎች ከጫንቃችን ላይ እናራግፋቸው።
በአንድነት እንነሳ! በያለንበት ለዚህ ውርደት እምቢ እንበል። ውርደታችን እምቢ ያልን ቀን ይቆማል። ያን እለት ጨለማው ይገፈፋል። የነጻነታችንና የክብራችን ጎህ ይቀዳል።
በያለንበት እምቢ እንበል! ስለተገፋንና ስለተዋረድን ማመፅ መብታችን ነው። የቻልክ ተቀላቀለን። ያልተመቸህ በያለህበት በራስህ አነሳሽነት ራስህን አደራጅ። የነጻነታችን ቀን ቅርብ ነው።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!!
source www.ginbot7.org

Monday, September 22, 2014

እሪ በይ ሃገሬ

ethiopian flag
Monday ,september 22nd,2014
ከአብርሃም ያየህ
ይህች  “እሪ በይ ኣገሬ” የተሰኘች ኣጭር ስንኝ፤ በኣሰብ ወደብ ያንድ የውጭ ባለሃብቶች የመርከብ ወኪልና የግምሩክ ኣስተላላፊ ትራንዚት ኩባንያ ቅርንጫፍ ስራ ኣስካያጅ በነበርኩበት ወቅት ታሪካቸውን በቅርበት ለማውቅላቸው፤
  • ለኣንጋፋው ኢትዮጵያዊ ስራ ፈጣሪና፥ ታላቅ ኣገር ኣልሚ ለሆኑት፤ 
  • ከትቢያ ኣፈር ተነስተው ዝነኛውን  የኢትዮጵያ ኣማልጋሜትድ ኩባንያ በመመስረት፥ ውድ ዋጋ በማስከፈል ህዝብ ሲበዘብዙ የነበሩትን የውጭ ኣገር ኩባንያዎችን በህጋዊ የዋጋ ውድድር ከገበያ ለማስወጣት ለቻሉት፤ 
  • በዚህ ኩባንያቸው ኣማካኝነትም በብዙ መከራ ያሳደጋቸውን የኢትዮጵያ ድሃ ገበሬን ህይወት ለመለወጥ ሲያኮበክቡ የ66ቱ “ኣብዮት” ደርሶ በሚያሳዝን ሆኔታ ላደናቀፋቸው፤ 
  • “ከኑግ ጋር የተገኘህ ሰሊጥ ኣብረህ ተወቀጥ” እንዲሉ፥ እኒህ ያንድ ድሃ ጭሰኛ ገበሬ ልጅ የሆኑትና፥ ምንም እንከን ሳይኖርባቸው በደርግ ማጎሪያ ቤት ለረጅም ዓመታት ለተሰቃዩት በኋላም ለስደት ለተዳረጉት፤ 
  • የማሌሊት/ወያነ ትውልደ ኤርትራዊያን መሪዎችና ግብረ-በላዎቻቸው ኣምርረው የሚጠሏትን ኢትዮጵያ እንደተቆጣጠሩ፥ የወራሪዎቹን ማንነት በውል ሳያወቁ በየዋህነት ወዳገራቸው ተመልሰው ባላቸው ከፍተኛ የስራ ልምድና እውቀት ኣማካኝነት ላገራችንና ለዝባችንን ከፍተኛ ጥቅም ለማበርከት ታጥቀው ቢነሱም፥ በደርግ እግር በተተኩት የህዝብ ጠላቶች፥ ኣገር ኣስገንጣዮችና ዳር-ድንበር ኣስደፋሪ ወያኔ/ማሌሊቶች እብሪት፥ የሚወዷትን ኣገራቸው ጥለው ለዳግም ስደት ለተዳረጉት፤ 
  • በቀ. ኃይለ-ሥላሴ ዘመነ መንግሥት በኢትዮጵያ ገበሬዎችና በቅርብ በሚያውቋቸው የወቅቱ ፖለቲካ እቀንቃኞች “ተራማጅ ነጋድራስ” የሚል እውቅና ለተሰጣቸው ለክቡር እምክቡራን ላቶ ገብረየስ ቤኛ የክብር ማስታወሻ ትሁንልኝ! 
እሪ በይ ኣገሬ
እሪ በይ ኢትዮጵያ ፥ ቅል ድንጋይ ሰበረ፤
ውሃ ሽቅብ ወጣ ፥ ዘመን ተቀየረ፤
ሌባ እየከበረ ፥ ነጋዴው ከሰረ፤
ኣገር ፈራረሰች ፥ ድንበር ተደፈረ፤
እንደ ቅርጫ ስጋ ፥ እየተመተረ፤
ላረብ ለድርቡሹ ፥ ይታደል ጀመረ፤
ጀግና ኣንገቱን ደፋ ፥ ባንዳ ተወጠረ።
(ግጥም፤ ከኢየሩሳሌም ጀማል Facebook የተወሰደ።)
ኣንጀት የሚያሳርረውና የሚያበግነው፥ ኣቶ ገብረየስ ቤኛ ከኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቪዥን (ኢሳት) ጋር ያደረጉት፥ በኣምስት ክፍል የቀረበ፥ ሰፊ የምስል (የቪዲዮ) ቃለ-መጠይቅ በትዕግስት በመመልከት፥ ኣሁን በኢትዮጵያ ቤተመንግስት የሰፈሩትና ፍፁም ፀረ-ኢትዮጵያ የሆኑት ኣደገኛ የዲያብሎስ ልጆች ምንነትና ኣጥፊ ዓላማ በትክክል ለመረዳት ያስችላል። በወያነ/ማሌሊት ኣመራር ምንነት ኣሁን ያለዎትን መረጃ በማዳበር ቢሆንም ተጨማሪ ኣቅም ይገነባል።  
  

Friday, September 19, 2014

UN experts urge Ethiopia to stop using anti-terrorism legislation to curb human rights

UN News Release
September 19, 2014

GENEVA (18 September 2014) – A group of United Nations human rights experts* today urged the Government of Ethiopia to stop misusing anti-terrorism legislation to curb freedoms of expression and association in the country, amid reports that people continue to be detained arbitrarily.

The experts' call comes on the eve of the consideration by Ethiopia of a series of recommendations made earlier this year by members of the Human Rights Council in a process known as the Universal Periodic Review which applies equally to all 193 UN Members States. These recommendations are aimed at improving the protection and promotion of human rights in the country, including in the context of counter-terrorism measures.


“Two years after we first raised the alarm, we are still receiving numerous reports on how the anti-terrorism law is being used to target journalists, bloggers, human rights defenders and opposition politicians in Ethiopia,” the experts said. “Torture and inhuman treatment in detention are gross violations of fundamental human rights.”
“Confronting terrorism is important, but it has to be done in adherence to international human rights to be effective,” the independent experts stressed. “Anti-terrorism provisions need to be clearly defined in Ethiopian criminal law, and they must not be abused.”
The experts have repeatedly highlighted issues such as unfair trials, with defendants often having no access to a lawyer. “The right to a fair trial, the right to freedom of opinion and expression, and the right to freedom of association continue to be violated by the application of the anti-terrorism law,” they warned.

“We call upon the Government of Ethiopia to free all persons detained arbitrarily under the pretext of countering terrorism,” the experts said. “Let journalists, human rights defenders, political opponents and religious leaders carry out their legitimate work without fear of intimidation and incarceration.”
The human rights experts reiterated their call on the Ethiopian authorities to respect individuals’ fundamental rights and to apply anti-terrorism legislation cautiously and in accordance with Ethiopia’s international human rights obligations.
“We also urge the Government of Ethiopia to respond positively to the outstanding request to visit by the Special Rapporteurs on freedom of peaceful assembly and association, on torture and other cruel, inhuman or degrading treatment or punishment and on the situation of human rights defenders,” they concluded.
ENDS
(*) The experts: Special Rapporteur on the promotion and protection of human rights and fundamental freedoms while countering terrorism, Ben Emmerson; Special Rapporteur on the rights to freedom of peaceful assembly and of association, Maina Kiai; Special Rapporteur on the promotion and protection of the right to freedom of opinion and expression, David Kaye; Special Rapporteur on the situation of human rights defenders, Michel Forst; Special Rapporteur on the Independence of Judges and Lawyers, Gabriela Knaul; Special Rapporteur on torture and other cruel, inhuman or degrading treatment or punishment, Juan Méndez.

Special Procedures is the largest body of independent experts in the United Nations Human Rights system. Special Procedures is the general name of the independent fact-finding and monitoring mechanisms of the Human Rights Council that address either specific country situations or thematic issues in all parts of the world. Currently, there are 38 thematic mandates and 14 mandates related to countries and territories, with 73 mandate holders. 

Special Procedures experts work on a voluntary basis; they are not UN staff and do not receive a salary for their work. They are independent from any government or organization and serve in their individual capacity

Source Ethiomedia.com

Tuesday, September 16, 2014

በአይሳኢታ፣ በዱብቲ፣ በአዋሽ፣ በአሚ ባራ፣ በገዋኔ፣ በአፍዴራ፣ በዶቢና ሚሌ የሚገኙ አፋሮች መሬታቸውን ተቀምተው በርሃብ እየተቆሉ ነው

Tuesday september 16th2014
አኩ ኢብን ከአፋር ለዘሐበሻ እንደዘገበው
የደርግ ስርዓት ወድቆ የኢህአዴግ መንግስት ሲመጣ ብዙ የአፋር መሬት ወደ ትግራይ ክልል እንዲመለስ ተደርጓል። በሰሜናዊው የአፋር ክልል በዳሉል ወረዳ ይተዳደሩ የነበሩ ብዙ የአፋር ህዝቦች በግዴታ በትግራይ ክልል ውስጥ እንዲተዳደሩ ተደርገዋል!
ለምሳሌ፦ ያህል፥ ታላክ፣ ጎደለ፣ ሰሄሎ እና ሰውነ ሲሆን ከዚህ በላይ ስማቸው በተጠቀሱት ቦታዎች ከኢህአዴግ ሰርዓት በፊት ከአጼዎች ዘመን ጀምሮ የአፋር መሬት እንደነበረ ይታወቃል። ታላክ እና ጎደለ እሰከ ሰሄሎ በደጅ አዝማች አህመድ ሲተዳደሩ ሰውነ ደግሞ በኦና ማሕሙድ ይተዳደር ነበር።
afar 1
afar 2
በዚህ አካባቢ የሚተዳደሩ የአፋር ህዝቦች እስካሁን ድረስ በቋንቋቸው የመማር ማስተማር እንዲሁም ባህላቸውን የማሳደግ የሰብዓዊ መብት ያላገኙ ሲሆን በሚኖሩበት የትግራይ ክልል እንኳን የአፋር ብሄረሰብ አይባሉም ኢህአዴግ ይኸው ቆምኩላችሁ መብታችሁን አስከበርኩላችሁ እያለ የአፋር ህዝብ ግን ገና ጭቆና ላይ መሆኑን ለመላው የኢትዮጵያ ወገኖቻችንና ለዴሞክራሲም ሆነ ለሰብዓዊ መብት የሚታገሉ የመብት ታጋዬች ሊያውቁልን ይገባል! ህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ ደርግን ለመዋጋት ወደ ጫካ ሲገቡ ይሄ የአፋር ህዝብ ለትግራይ ህዝብ የቅርብ ጎረቤት ስለነበር ምግባቸውን አብስለው ለተጋዬች ከማቅረብ ጀምሮ ከጎናቸው የቆመ ህዝብ ቢሆንም ዛሬም ከጭቆና ልወጡ አልቻሉም።
ወድ የተከበረችሁ ወገኖቼ ሆይ ይሄን ስናገር ግን የቀረው የአፋር ህዝብ መብት ተክሮለታል ማለት አይደለም! በክልላችን በወያኔ ያልተወረረ የአፋር መሬት የለም። በአይሳኢታ፣ በዱብቲ፣ በአዋሽ ፣በአሚ ባራ፣ በገዋኔ ፣በአፍዴራ ፣በዶቢና ሚሌ የሚገኙ አፋሮች በአሁኑ ጊዜ ከመሬታቸው ተፈናቅለው በረሀብ እየተሰቃዩም ይገኛሉ።
የተንዳሆ የስኳር ፋብሪካ የተጀመረው በ2001 ዓ.ም ቢሆንም እሰከ ዛሬ የኢትዮጵያ ህዝብ ከስኳር ችግር አልወጣም። ፋብሪካው ሙሉ በሙሉ የሚቆጣጠሩት የህወሃት ባለ ስልጣናት ሲሆኑ አብዛኛቸው ከመከላኪያ ሰራዊት በጡረታ የወጡ መኮነኖች ናቸው! የአፋር ክልል መንግስትም ቢሆን ለስራቸው የሚሰጠውን ባጀት ወደ ውጭ ሀገር እየላኩ ማስቀመጥ ብቻ ነው!! ሌላው ቀርቶ በአፋር ክልል በሰላም ሲኖሩ የነበሩ የአማራና የኦሮሞ ብሄር ተወላጆችን በግዳጅ ከአፋር ክልል እያስወጡ ይገኛሉ። በዚህ አመት ብቻ ከ400 ሺ በላይ የትግራይ ተወላጆች በሰፈራ ፕሮግራም ወደ አፋር ክልል ገብተዋል!!
በመጨረሻም:- የአፋር ህዝብ ከኢትዮጵያ ነፃነት ታጋዮች ጋር ለሚደረገው ትግል ከዳር እስከ ዳር ዝግጁ መሆኑን በአፋር ወጣቶች ስም ላረጋግጥላችሁ እወዳለሁ። የአፋር ህዝብ ይህ የአንባገነን ስርዓት አብቅቶ የነፃነት ፀሃይ የምትወጣበት ቀን በጉጉት የሚጠብቅ ጭቁን ህዝብ ነው!
ነፃነት ለኢትዮጵያ
ምንጭ ዘ-ሐበሻ 

Sunday, September 14, 2014

በጋምቤላ ዞን በጎደሬ ወረዳ ነጋዴዎችና ሰፋሪዎች ከአካባቢው ተወላጅ የመዠንገር ጎሳ አባላት ጋር ተጋጩ። በግጭቱ ከ17 ሰባት በላይ ሰዎች ተገድለዋል። በግጭቱ …

september 15,2014

በጎደሬ ወረዳ የዘር ግጭት ተነሳ፤ መከላከያ ገብቷል

የዞንና የወረዳ አስተዳዳሪዎች ከነቤተሰቦቻቸው ተገደሉ
በጋምቤላ ዞን በጎደሬ ወረዳ ነጋዴዎችና ሰፋሪዎች ከአካባቢው ተወላጅ የመዠንገር ጎሳ አባላት ጋር ተጋጩ። በግጭቱ ከ17 ሰባት በላይ ሰዎች ተገድለዋል። በግጭቱ የመዠንገር ዞን አስተዳዳሪና የጎደሬ ወረዳ ዳኛ ከነቤተሰቦቻቸው የግጭቱ ሰለባ መሆናቸው ታውቋል። ግጭቱን ለማብረድ የመከላከያ ሠራዊት የገባ ሲሆን፣ የጋምቤላ ክልል ልዩ ኃይል ግጭቱን ለማብረድ በጉዞ ላይ እንዳለ በተሰጠ መመሪያ እንዲመለስ ተደርጓል
ስማቸው እንዳይገለጽ የፈሩ የአካባቢው ነዋሪዎች ለጎልጉል እንደገለጹት በወረዳው በመሬት ባለቤትነትና በመሬት ይገባኛል ጥያቄ ከመሀል አገር በመጡ ሰፋሪዎችና ነጋዴዎች መካከል አለመግባባት ከተፈጠረ ዓመታትን አስቆጥሯል። የፌዴራል አገዛዙም ሆነ የክልሉ አመራሮች ችግሩ ሳይሰፋ ሰላማዊ መፍትሄ ባለማፈላለጋቸው ችግሩ ሊካረር ችሏል። ኢህአዴግ የሚከተለው በዘር ከፋፍሎ የመግዛት ፖሊሲ ለችግሩ መባባስ በዋንኛነት ተጠቃሽ ነው።
ባለፈው ሃሙስ በአንድ የመሃል አገር ሰፋሪና የአካባቢው ተወላጅ በሆነ አርሶ አደር መካከል ድንገተኛ ጸብ ተነስቶ ነበር። በጸቡ የመዠንግር ጎሳ አባል የሆነው አርሶ አደር ህይወት አለፈ። በጎሳ አባላቸው መገደል የተበሳጩ ዘመዶች ውሎ ሳያድር በወሰዱት የበቀል ርምጃ አንድ ሰፋሪ የመሃል አገር ሰው ህይወት አለፈ። እንደ ዜናው አቀባዮች ከሆነ በዚሁ በመሬት ጉዳይ በተከሰተው የሁለት ግለሰቦች ህልፈት ተከትሎ ችግሩ ተካረረ።
በተመሳሳይ ቀን ማምሻው ላይ ከመሃል አገር የመጡት ሰፋሪዎች የዞኑን አስተዳዳሪ፣ ባለቤታቸውንና ሁለት ልጆቻቸውን መኖሪያ ቤታቸው በመሄድ በስለት ገደሉ። በተመሳሳይ አንድ የጎደሬ ወረዳ አስተዳዳሪ ከባለቤታቸውና ከልጃቸው ጋር ተገደሉ። በደቦ የተጀመረው የስለት ግድያ እየሰፋ የሟቾችን ቁጥር 17 እንዳደረሰውና በስለት የቆሰሉ ሰዎች ቁጥር ከ40 በላይ መሆኑን በስልክ የገለጹት ያካባቢው ነዋሪዎች “አሁን ፍርሃቻ አለ። ቤት ለቤት የተካሄደው ግድያ የት ጋር ያቆማል? የመከላከያ ሠራዊት ሚናም ግልጽ አይደለም” ብለዋል።
የጋምቤላ ዞን ልዩ ኃይል ግጭቱን ለማብረድ እየገሰገሰ ባለበት ወቅት ከአዲስ አበባ በተሰጠ ትዕዛዝ ወደ ጋምቤላ እንዲመለሱ መደረጉን ያመለከቱት እኚሁ ክፍሎች፣ “የጋምቤላ ልዩ ኃይል ግጭቱ ያለበት ቦታ ሲደርስ በራሱ ክልል ሰዎች ላይ መጤዎች ጉዳት ማድረሳቸውን ሲመለከት ከመከላከያ ሠራዊት ጋር ግጭት ሊፈጠር ይችላል” በሚል ስጋት የልዩ ኃይሉ ወደ ጋምቤላ የተመለሰበትን ምክንያት ነዋሪዎቹ ተናግረዋል።
በገጀራና በተለያዩ የስለት መሳሪያዎች የተካሄደው ግድያ የሚዘገንን እንደነበር፣ ቀን ጠብቆ ተጎጂው አካል ከመበቀል ወደኋላ እንደማይል፣ በስለታማ ቁሶች የሚከናወነው ግድያ ሊሰፋ እንደሚችል ስጋታቸውን አክለው የገለጹት ነዋሪዎች ኢህአዴግ ሰላማዊ መፍትሄ ሊፈልግ እንደሚገባ ከወዲሁ ጠይቀዋል። በጋምቤላ ክልል በሳንቲም የሚቸበቸበውና የተፈጥሮ ደን እያወደመ ያለው ኢንቨስትመንት የተወሳሰበ ችግር ማስከተሉ አይዘነጋም። በዚሁ ሳቢያ በርካታ ንጹሃን ህይወታቸው ማለፉ የሚታወስ ነው። ክልሉን ከላይ ሆነው የሚመሩት አቶ አዲሱ ለገሰ መሆናቸው ይታወቃል።
የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ (አኢጋን) ዋና ዳይሬክተር አቶ ኦባንግ ሜቶ ጉዳዩን አስመልክቶ ከኦስሎ ለጎልጉል አስተያየት ሲሰጡ “ባሰቃቂ ሁኔታ ህይወታቸው ላለፈ ወገኖች የሰላም ረፍት ይሁን፣ ፍትህ በልጅ ልጆቻችሁ ትፈርድላችኋለች፣ ፍትህ ሩቅ አይሆንም” በማለት ነበር የጀመሩት። አያይዘውም “ምንም እንኳ ባል ፖለቲከኛ ቢሆን ሚስትና ልጆች ምን አደረጉ? ህጻናትና ሴቶች በማያውቁት ጉዳይ ለምን ሰላባ ይሆናሉ? ቀደም ሲል አብረው የሚኖሩ ሰዎች ዛሬ ለምን ይጋጫሉ?” ሲሉ ችግሩ ሁሉ የሚመነጨው ኢህአዴግ ከሚከተለው ጎሳን መሰረት ያደረገ የከፋፍለህ ግዛው መርህ አንደሆነ ገልጸዋል።
“መመሪያ ሰጪው፣ ገዳዩ፣ አስገዳዩ፣ ቆሞ ተመልካቹ፣ … ሁሉም ከፍትህ አደባባይ አያመልጡም” ያሉት አቶ ኦባንግ “ዘርን እየለየ የሚከናወን ግድያ “ጄኖሳይድ” ነው። አኙዋኮች ላይ በጅምላ ከተከናወነው ጭፍጨፋ ለይተን አናየውም” ሲሉ በጉዳዩ ክፉኛ ማዘናቸውን አመልክተዋል።
የሚመሩት ድርጅት ጉዳዩን በቅርብ እየተከታተለና አስፈላጊ ነው የሚለውን ስራ እያከናወነ እንደሆነ ያመለከቱት አቶ ኦባንግ፣ ሁሉም ያካባቢው ነዋሪዎች ሰፋሪም ሆነ የቀዬው ተወላጆች እንደቀድሞ በፍቅር ሊኖሩ የሚያስችላቸውን እሴቶች እንዲጠብቁ መክረዋል። በተለያዩ ያገሪቱ ክፍሎች ጎሳን እየለየ የሚካሄደው ግድያና ማፈናቀል እየሰፋ እንጂ እየቀነሰ ባለመሆኑ ስጋቱ ከፍተኛ እንደሆነም ገልጸዋል። በዚህ ከቀጠለና ህወሃት የቀበራቸው የጎሳ ፈንጂዎች ሲነዱ እሳቱ ሁሉንም ስለማይምር ሁሉም ዜጎች ጥንቃቄ እንዲወስዱ አሳስበዋል። ኢህአዴግም ችግሮችን ከማስፋት ይልቅ የሚቃለሉበትን አግባብ ለራሱ ሲል ሊከተል እንደሚገባ ጠቁመዋል። ጎልጉል የዞኑንና የወረዳውን አስተዳደር ለማነጋገር ያደረገው ጥረት አልተሳካም። ይሁን እንጂ የክልሉ ፖሊስ ዝርዝር መግለጫ ባይሰጥም የተባለው ቀውስ ስለመፈጠሩ አልካደም።
source http://www.goolgule.com

በዶ/ር ብርሃኑ ነጋ አዲሱን ዓመት አስመልክቶ ለኢትዮጵያ ህዝብ የተላለፈው መልዕክት በጽሑፍ!!!

September13,2014
እንደምን አመሻችሁ!
በዚህች መላዉ የኢትዮጵያ ሕዝብ ከቤተሰቦቹና ከወዳጆቹ ጋር ሆኖ አዲሱን አመት ለመቀበል በሚዘጋጅባት ምሽት በግንቦት 7 የፍትህ፤ የነጻነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ስም እንኳን ለአዲሱ አመት በሠላም አደረሳችሁ ስል ከፍተኛ ክብርና ትልቅ ደስታ ይሰማኛል። መቼም በባህላችን ለሠላም ያለን ቦታ ከፍተኛ ስለሆነ አዲስ አመት በመጣ ቁጥር እንኳን በሠላም አደረሳችሁ እንባባላለን እንጂ ኢትዮጵያ ዉስጥ ሠላም ከጠፋ ብዙ አመታት ተቆጥረዋል።
ዉድ የአገሬ የኢትዮጵያ ሕዝብ-
እኛን ለመሰለ ከሁለት አስርተ አመታት በላይ በዘረኛ አምባገነኖች ለተረገጠ ሕዝብ የአዲስ አመት ዋዜማ አሮጌዉን አመት ሸኝተን አዲሱን የምንቀበልበት የሆታና የጭፈራ ምሽት ሆኖ ማለፍ የሚገባዉ አይመስለኝም። ይልቁንም በዚህ አሮጌዉን 2006ትን ተሰናብተን አዲሱን 2007ትን በምንቀበልበት ምሽት ባሳለፍነዉ የትግል አመት የገጠሙንን ችግሮችና መሰናክሎች መርምረንና ከድክመታችን ተምረን በ2007 ዓም ለምናደርገዉ ወሳኝ ትግል እራሳችንን ማዘጋጀት ያለብን ይመስለኛል።
እኛ ኢትዮጵያዉያን ረጂም የነጻነት ታሪክና በየዘመኑ የዘመቱብንን ወራሪዎች በተከታታይ ያሸነፍን የጥቁር ሕዝብ የነጻነትና የአልበገር ባይነት ተምሳሌቶች ነን። ያለፉት ሃያ ሦስት አመታት ታሪካችንን ስንመለከት ግን እነዚህ አመታት እፍኝ በማይሞሉ የአገር ዉስጥ ጠላቶቻችን ተሸንፈን ክብራችንንና ፈጣሪ ያደለንን ነጻነታችንን ተቀምተን የኖርንባቸዉ አሳፋሪ አመታት ናቸዉ። በ1983 ዓም አምባገነኑን ደርግ በትጥቅ ትግል ያስወገዱት የወያኔ መሪዎች እነሱ እራሳቸዉ ከደርግ የከፉ አምባገነኖች ሆነዉ አሁንም ድረስ አገራችን ኢትዮጵያን እየገዙ ይገኛሉ።
የወያኔ ስርዐት በየቀኑ በአገርና በሕዝብ ላይ የሚፈጽመዉን ግፍ፣ በደልና ሰቆቃ ስርዐቱን አምባገነን ነዉ ብሎ በመጥራት ብቻ መግለጽ የሚቻል አይመስለኝም። አገራችን ኢትዮጵያን ጨምሮ አለማችን ብዙ አምባገነን መንግስታትን አስተናግዳለች ዛሬም እያስተናገደች ነዉ። ወያኔ ግን እመራዋለሁ የሚለዉን ሕዝብና የሚመራዉን አገር በግልጽ የሚጠላ ከሌሎች አምባገኖች ለየት ያለ አምባገነን ነዉ። ወያኔ ሥልጣን ይዞ በቆየባቸዉ አመታት ሁሉ ኢትዮጵያዊነትን ሽንጡን ገትሮ ተዋግቷል፤ የኢትዮጵያን ደሃ ገበሬ አፈናቅሎ መሬቱን የኔ ለሚላቸዉ ታማኞቹና ለዉጭ አገር ቱጃሮች በርካሽ ዋጋ ሽጧል።ደቡብ ኢትዮጵያ ዉስጥ ለረጂም አመታት ከአካባቢዉ ሕዝብ ጋር ተግባብteዉ ይኖሩ የነበሩትን የአማራ ተወላጆች ይህ የእናንተ አገር አይደለም ብሎ ከገዛ አገራቸዉ ተፈናቅለዉ እንዲወጡ አድርጓል። በ 2005ና በ2006 ዓም በኦሮሚያ፤ በአማራ፤ በአፋርና በሶማሌ ክልሎች ከመሬታችን አታፈናቅሉን ብለዉ የመብት ጥያቄ ያነሱ አያሌ ሠላማዊ ዜጎችን በግፍ ጨፍጭፎ ገድሏል። ባጠቃላይ ወያኔ በዘር የተደራጀ፤ ሕዝብን በዘር የሚከፋፍልና የሚቃወመዉን ሁሉ በጅምላ እያሰረ በጅምላ የሚገድል ድርጅት ነዉ።
ይህም ሁሉ ሆኖ የወያኔ መሪዎች ከሕዝብና ከራሳቸዉ ጋር ታርቀዉ፤ በአገርና በሕዝብ ላይ የፈጸሙት ዝርፊያና ያደረሱት በደል በይቅርታ ታልፎ በኢትዮጵያ ዉስጥ እዉነተኛ ዲሞክራሲያዊ ስርዐት የሚገነባበትን መንገድ እንዲያመቻቹ የኢትዮጵያ ሕዝብ ተደጋጋሚ ዕድል ሰጥቷቸዉ ነበር። ለምሳሌ ከ1997ቱ ምርጫ በኋላ ተቃዋሚ ድርጅቶች የምርጫዉ ዉጤት እንደተጭበረበረ እያወቁ የወያኔ አገዛዝ አገሪቱን ለሚቀጥሉት አምስት አመታት ያለምንም ተቀናቃኝ እንዲመራና እነዚህን አምስት አመታት የተራራቀ ሕዝብን ለማቀራረብ፤ የዲሞክራሲ ተቋሞች መሠረት ለመጣልና አገራችን ዉስጥ መሪዎች በሀቀኛ ህዝባዊ ምርጫ ብቻ ወደ ስልጣን የሚመጡበትን መንገድ ለማመቻቸት እንዲጠቀምበት ዕድል ተሰጥቶት ነበር። ከዚህ በተጨማሪ ተቃዋሚ ድርጅቶች እራሳቸዉም በዚህ አገርን የማዳን ጥረት ዉስጥ ሙሉ በሙሉ ከወያኔ ጎን በአጋርነት እንደሚቆሙና እንደሚተባበሩት ቃል ገብተዉለት ነበር። ሆኖም የወያኔ መሪዎች አስተዋይነትን እንደ በታችነት፤ ትዕግስትን እንደ ፍርሃት መቻቻልን ደግሞ እንደ ሞኝነት በመቁጠር በወዳጅነት ላቀረብንላቸዉ የአገራችንን እናድን ጥሪ ምላሻቸዉ እስር፤ ግድያና ከአገር እንድንሰደድ ማድረግ ብቻ ነበር።
በአገራችን በኢትዮጵያ አንድነትና በህዝባቿ የወደፊት ዕድል ላይ የተደቀነዉ መጠነ ሰፊ አደጋ ከወዲሁ የታያቸዉ የተለያዩ ኢትዮጵያዉያን በተለያየ መልኩ ከወያኔ ጋር ብዙ እልህ አስጨራሽ ድርድሮችን አካሂደዋል። ከዚህም አልፈዉ የኢትዮጵያ አንድነት የሚረጋገጥበትንና ህዝበቿ ሠላም፤ ፍትህና እኩልነት በነገሱበት አገር የሚኖሩበትን መንገድ ለማመቻቸት ከወያኔ መሪዎች ጋር ረጂምና አድካሚ መንገዶችን ተጉዘዋል። ሆኖም አገራችንን ከዉድቀት ለማዳን እነዚህን ሁሉ ተደጋጋሚ ጥረቶች ስናደርግ የወያኔ መሪዎች በግልጽ የነገሩን ነገር ቢኖር ፍላጎታቸዉና የረጂም ግዜ ዕቅዳቸዉ የኢትዮጵያን ሕዝብ አዋርደዉ መግዛት እንጂ ፍትህ፤ ነጻነት፤ ዲሞክራሲና እኩልነት በፍጹም አጀንዳቸዉ እንዳልሆነ ነዉ። የወያኔ መሪዎች ዕብሪትና ማን አለብኝነት በዚህ ብቻም አላበቃም፤ የጫኑብንን የባርነት ቀንበር አሜን ብላችሁ ተቀበሉ፤ አለዚያም ድፍረቱ ካላችሁና እኛ የመጣንበትን መንገድ የምትችሉት ከሆነ “መንገዱን ጨርቅ ያድርግላችሁ” ብለዉ አሹፈዋል።
የወያኔ መሪዎች ከ1997ቱ ምርጫ የተማሩት ትምህርት ቢኖር ኢትዮጵያ ዉስጥ ነጻና ፍትሃዊ ምርጫ ቢኖር እነሱና ፓርቲያቸዉ በፍጹም ወደ ሥልጣን እንደማይመጡና ኢትዮጵያንም እንዳሰኛቸዉ መዝረፍ እንደማይችሉ ነዉ። ሰለሆነም ከምርጫ 97 በኋላ በነበሩት ሦስትና አራት አመታት የወሰዷቸዉ እርምጃዎች በሙሉ ነጻ ምርጫ የሚፈልጋቸዉን ተቋሞች የሚያሽመደምዱና ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎችን ባሰኛቸዉ ግዜ ሁሉ መወንጀል የሚያስችላቸዉ ህጎች ነበሩ ። ለምሳሌ የሜድያ ህግ፤ የበጎ አድራጎት ድርጅቶችና ማህበራት ህግና የሽብርተኝነት ህግ የወያኔ መሪዎች የሚቃወማቸውንና ሀሳቡን በነጻነት የሚገልጸዉን ዜጋ ሁሉ ለመኮነን ያወጧቸዉ ህጎች ናቸዉ። እነዚህ ህጎች ከወጡ በኋላ ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ፤ የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎቹ አንዱአለም አራጌና በቀለ ገርባ፤ ጋዜጠኛና መምህርት ርኢዮት አለሙና ሌሎችም ብዙ ሠላማዊ ዜጎች የግንቦት 7 አባላት ናችሁ በሚል ቃሊቲ ወርደዋል።
የወያኔ እስርና አፈና በአገር ዉስጥ ብቻ ተወስኖ አልቀረም። የወያኔ አገዝዝ ከሱዳን፤ ከኬንያና ከጂቡቲ መንግስታት ጋር በመመሳጠር አያሌ ኢትዮጵያዉያን ስደተኞችን ሽብርተኞች ናቸዉ እያለ አገር ቤት አስመጥቶ ሰቆቃ ፈጽሞባቸዋል። በመጨረሻም ባለፈዉ ሰኔ ወር አጋማሽ ዕብሪተኞቹ የወያኔ መሪዎች የንቅናቄያችንን ዋና ፀሐፊ አቶ አንዳርጋቸዉ ጽጌን ፍጹም ህገወጥ በሆነ መንገድ አግተዉ እስከዛሬ ድረስ እያሰቃዩት ነዉ። እኛ የወያኔን መሪዎች እስሩን፤ ግድያዉን፤ ዝርፊያዉንና የዘረኝነት ፖሊሲያችሁን አቁማችሁ አገራችን ዉስጥ ፍትህ፤ሠላምና እኩልነት የሰፈነበት ስርዐት አንገንባ ብለን ስንወተዉታቸዉ እነሱ ግን አፈናቸዉንና ዉንብድናቸዉን በስደት የምንኖርበት አገር ድረስ ይዘዉ በመምጣት ለሰላም የከፈትነዉን በር ዘግተዋል። በዚህም የወያኔ መሪዎች እነሱ እራሳቸዉ በመረጡልን የትግል ስልት ገጥመናቸዉ ከአገራችን ምድር ጠራርገን ከማስወጣት ዉጭ ሌላ አማራጭ እንዳይኖረን አድርገዋል።
ዉድ ኢትዮጵያዉያን ወገኖቼ!
የወያኔ አገዛዝ እኛን ኢትዮጵያዉያንን ያዋረደዉ አገር ዉስጥ ብቻ አይደለም። በዉጭ አገሮችም ባለቤትና ጠያቂ የሌለዉ ዜጋ አድርጎናል። በባዕድ አገሮች ጥቃት ሲደርስብን የራሱ ፓርቲ አባላት ወይም ደጋፊዎች ካልሆንን በዜግነታችን ምንም ነገር ለማድረግ ፈቃደኛ ሆኖ አያዉቅም። ዛሬ ከወያኔ ግፍና አፈና ለማምለጥ የሚሰደደዉ ኢትዮጵያዊ ከብዛቱ የተነሳ ቁጥሩ በዉል የሚታወቅ አይመስለኝም። የአፍሪካና የአረብ አገሮችን እስር ቤቶች የሞሉት ኢትዮጵያዉያን ስደተኞች ናቸዉ። ሴቶች እህቶቻችን አገር ዉስጥ የስራ ዕድል ስለማያገኙ በየአረብ አገሩ እየተሰደዱ የሚደርስባቸዉን ዉርደት በአፋችን ደፍረን መናገር ያቅተናል። ባለፈዉ አመት ከሳዑዲ አረቢያ ስንትና ስንት መከራና ፍዳ አይተዉ ወደ አገራቸዉ የተመለሱ ወገኖቻችን ሳዑዲ ይሻለናል እያሉ ለሁለተኛ ግዜ እየተሰደዱ ነዉ። ይህ ሁሉ የሚያሳየን ወያኔ የዛሬዋን ብቻ ሳይሆን የነገዋንም ኢትዮጵያ እገደለ መሆኑን ነዉ።
ዉድ የአገሬ የኢትዮጵያ ሕዝብ!
የወያኔ ዘረኞች ባለፉት ሃያ ሦስት አመታት ያደረሰብንን በደል፤ ዉርደት፤ ስደትና ስቃይ ላንተ የችግሩ ገፈት ቀማሽ ለሆንከዉ በዝርዝር መናገሩ የአዋጁን በጆሮ ነዉና አላደርገዉም፤ ሆኖም ይህ ስርዐት ምን ያክል ዘረኛ፤ ጨካኝና አረመኔ መሆኑን ማሳየት ስርዐቱን ንደን ለመጣል ለምናደርገዉ ወሳኝ ትግል ይጠቅማል ብዬ አጥብቄ ስለማምን ወያኔ ዛሬ በምንሰናበተዉ በ2006 ዓም ብቻ በሕዝብና በአገር ላይ የፈጸማቸዉን አንዳንድ ወንጀሎች መጥቀስ እፈልጋለሁ።
  1. የወያኔ የጸጥታ ሃይሎች የእስልምና እምነት ተከታይ ወገኖቻችንን የአምልኮ ቦታቸዉ ድረስ ሰርገዉ በመግባት ለፈጣሪያቸዉ ፀሎት በማድረስ ላይ እንዳሉ በቆመጥ ደብድበዋል፤ አያሌ ምዕመናንን አስረዉ በሽብርተኝነት ከስሰዋle
  2. በመልካም ብዕራቸዉ ሕዝብን ከማስተማርና ከማሳወቅ ዉጭ ከሽብርተኝነት ጋር ቀርቶ ከተራ ወንጀል ጋር እንኳን የማይተዋወቁትን ዞን ዘጠኝ ጦማሪያንና ጋዜጠኞች ከሁለት ወር በላይ ያለ ማስረጃ በግፍ አስረዉ በቅርቡ በሽብርተኝነት ወንጀል እንዲከሰሱ አድርገዋል
  3. 2006 ወያኔ የለየለት የነጻ ፕሬስ ጠላት መሆኑን እንደገና ያረጋገጠበት፤ አያሌ ጋዜጠኞች የታሰሩበትና አገር ለቅቀዉ የተሰደዱበት፤አገራችን ኢትዮጵያ ደግሞ የአለማችን ቀንደኛ የጋዜጠኞች ጠላት ተብላ የተሰየመችበት አመት ነዉ
  4. ግፈኞቹ የወያኔ መሪዎች ጉዳዩ በቀጥታ የሚመለከተዉን ሕዝብ ሳያማክሩ lezerefa endimechachew የአዲስ አበባን ከተማ የመሬት ይዞታ ለማስፋፋት የወሰዱትን እርምጃ በህጋዊ መንገድ የተቃወሙ ተማሪዎችን በጠራራ ፀሐይ በጥይት የጨፈጨፉትም በዚሁ በ2006 ዓም ነበር
  5. ወያኔ እራሱ የጻፈዉ ህገመንግስት የሰጣቸዉን መብት ተጠቅመዉ ሀሳባቸዉን የገለጹ አገር ዉስጥ የሚገኙ የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎችን ከሽብርተኞች ጋር ተባብራችኋል የሚል ሰንካላ ምክንያት ፈጥሮ አስሮ እያሰቃያቸዉ ነዉ
  6. ባለፈዉ አመት ወያኔ አንዱን ማህበረሰብ ከሌላዉ የማጋጨት እርምጃዎች በኦሮሚያ፤ ጋምቤላና ቤኒሻንጎል ወስዷል፤ በተለይ የአማራዊንና የኦሮሞን ህዝብ ማጋጨትን እንደ ቋሚ ስራዉ ወስዷል።
ዉድ ወገኖቼ! እነዚህ የዘረዘርኳቸዉ ወንጀሎች በሕዝብ ተመረጥኩ የሚለዉ ወያኔ በ2006 ዓም ከፈጸመብን ወንጀሎች በጣም ጥቂቶቹ ናቸዉ። የዛሬዉ ቁም ነገሬ ግን ወያኔ የፈጸማቸዉ ወንጀሎች ብዛትና ማነስ ላይ ማተኮር አይደለም። የዛሬዉ ቁም ነገሬ እንደ ሕዝብና እንደ አገር ለምን በገዛ መሪዎቻችን ወንጀል ይፈጸምብናል – እኛስ እስከመቼ ነዉ ለጆሮ የሚሰቀጥጥ ወንጀል በየቀኑ ሲፈጸምብን ዝም ብለን የምናየዉ? የሚለዉ መሠረታዊ ጥያቄ ላይ ነዉ።
በዚህ ምድር ላይ በዳይና ተበዳይ፤ አሸናፊና ተሸናፊ ነበሩ ለወደፊትም ይኖራሉ። ሲበደል በደሉን አሜን ብሎ ተቀብሎና ሁሌም ተሸናፊ ሆኖ የሚኖር አገርና ሕዝብ ግን በፍጹም የለም። በዛሬዉ ምሽት የኛ የኢትዮጵያዉያን ጀግንነት ድንበር ጥሰዉ ሊወርሩን በሚመጡ ጠላቶቻችን ላይ ብቻ ሳይሆን በአገር በቀል ጠላቶችም ላይ መሆኑን በግልጽ ተነጋግረን መግባባት አለብን። ወያኔ ደግሞ አገር በቀል ጠላት ብቻ ሳይሆን ከወጭ ወራሪዎች ባልተናነሰ መንገድ የአገራችንን አንድነት የሚዋጋ ኃይል ነዉ። በ2007 ወጣቱ፤ ገበሬዉ፤ ሰራተኛዉና የመከላከያ ሠራዊቱ አባላት እጅ ለእጅ ተያይዘዉ ይህንን አገር በቀል ጠላት ማስወገድ አለባቸዉ ብሎ ግንቦት ሰባት በጽኑ ያምናል።
ግንቦት 7 የፍትህ፤ የነጻነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ወያኔንና ወያኔ የገነባዉን ዘረኛ ስርዐት አስወግዶ ፍትህ፤እኩልነትና ዲሞክራሲን ለማስፈን በሚደረገዉ ህዝባዊ ትግል ዉስጥ ወጣቶች፤ ሴቶችና የመከላከያ ሠራዊት አባላት እጅግ በጣም ቁልፍ የሆነ ሚና ይጫወታሉ ብሎ ያምናል። ይህንን ደግሞ ወያኔም ስለሚረዳ ለዘረኝነት አላማዉ ከጎኑ ለማሰለፍ በጥቅማጥቅም የሚደልለዉና አለዚያም በሽብርተኝነት ፈርጆ እያሰረ የሚያንገላታዉ እነዚሁኑ ሦስት የህብረተሰብ ክፍሎች ነዉ።
የአገሬን ዳር ድንበር ከወራሪዎች እጠብቃለሁ ብለህ የመከላያ ሠራዊቱን የተቀላቀልክ የአገር መከላከያ ሠራዊት አባል ሆይ! አንተ የለበስከዉ ዪኒፎርም ጀርባህ ላይ ተቀድዶ ፀሐይና ብርድ ሲፈራረቁብህና የወለድካቸዉ ልጆችህና የወለዱህ እናትና አባትህ ደግሞ የሚላስና የሚቀመስ አጥተዉ በችግር አለንጋ ሲገረፉ፤ በየክልሉ እየሄድክ የገዛ ወገኖችህን እንድትገድል ትዕዛዝ የሚሰጡህ የወያኔ አለቆችህ ግን በኮንትሮባንድና በግልጽ የመሬት ዝርፍያ በዋና ዋና የአገራችን ከተሞች ከገነቧቸዉ ሰማይ ጠቀስ ህንፃዎች ዉጭ ካንተና ከሕዝብ የዘረፉት በቢሊዮኖች የሚቆጠር ገንዘብ ትላልቆቹን የዉጭ አገር ባንኮች አጨናንቋል። አንተና ቤተሰቦችህ ነገ ምን እንሆናለን የሚል የችግር እንባ ስታነቡ ጥጋበኞቹ አለቆችህ ግን የጥጋብ ግሳት ያገሱብሃል።
ዉድ የአገሬ መካላከያ ሠራዊት አባል ሆይ!
ምትክ የሌላትን አንድ ህይወትህን ልትሰጣት ቃል በገባህላት አገር ዉስጥ እንዲህ አይነቱ የሚዘገንን በደል ባንተና በወገኖችህ ላይ ሲፈጸም ዝም ብለህ የምትመለከትበት ግዜ ማብቃት አለበት። መጪዉ አዲስ አመት ግንቦት 7 ለኢትዮጵያ ሕዝብ የገባዉን ቃል ተግባራዊ ማድረግ የሚጀምርበት አመት ነዉ። ይህንን መከላከያ ሠራዊቱን ጨምሮ መላዉን የኢትዮጵያ ሕዝብ ከወያኔ ባርነት ነጻ የሚያወጣ ተግባራዊ እንቅስቃሴ ጀምረን ከወያኔ ጋር ትንቅንቅ ዉስጥ ስንገባ የመከላከያ ሠራዊት አባላት ከታጠቁት መሳሪያ ጋር ወደምንገኝበት ቦታ ሁሉ እየመጡ እንዲላቀሉንና በምንም ሁኔታ የዘረኞችን ትዕዛዝ ተቀብለዉ በገዛ ወገኖቻቸዉ ላይ ክንዳቸዉን እንዳያነሱ በግንቦት 7 ንቅናቄ ስም አገራዊ ጥሪዬን አስተላልፋለሁ።
የኢትዮጵያ ሕዝብ ሆይ!
ከእያንዳንዱ መቶ የአገራችን ሕዝብ ዉስጥ 64ቱ ዕድሜዉ ከ25 አመት በታች ነዉ፤ወያኔ እርስ በርሱ እንዳይገናኝ፤ አንዳይደራጅና በአገሩ ጉዳዮች ላይ እንዳይወያይ አፍኖ የያዘዉ ይህንኑ የአገራችን የወደፊት ተስፋ የሆነዉን ወጣት ነዉ፤ በሌላ በኩል ደግሞ በሚገባ በእዉቀት ተኮትኩቶ ካደገ የወደፊቷን ኢትዮጵያ ተረክቦ አገሩን ከድህነትና ከኋላ ቀርነት ያላቅቃል ተብሎ ከፍተኛ ተስፋ የmiጣለበትም ይሄዉ ወጣት ነዉ። ሆኖም ባለፉት ሁለትና ሦስት ሳምንቶች በግልጽ እንዳየነዉ ወያኔ የአገሪቱን ዩኒቨርሲቲዎችና ኮሌጆች የራሱን የከሰረ አስተሳሰብ ማስፋፊያና የፓርቲ አባላት መመልመያ ጣቢያ አድርጓቸዋል። በተለይ በአሁኑ ወቅት በእረፍት ላይ የሚገኙትን የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ለሥልጠና ካልመጣችሁ ወደ ትምህርት ገበታችሁ መመለስ አትችሉም ብሎ እያስፈራራ የተፈጥሮና የማህበራዊ ሳይንስ መማር ያለባቸዉን ተማሪዎች ተራ የካድሬ ስልጠና እየሰጣቸዉ ነዉ።
በየዘመኑ የተነሳዉ የኢትዮጵያ ወጣት አገሩን ከወራሪዎች በመከላከልም ሆነ የአገር ዉስጥ ፈላጭ ቆራጭ የገዢ መደቦችን ፊት ለፊት በመጋፈጥ የረጂም ዘመን አኩሪ ታሪክ ያለዉ ወጣት ነዉ። እኔ በኢትዮጵያ ወጣቶች ላይ ያለኝ እምነት እጅግ በጣም ከፍተኛ ነዉ፤ የዚህ ትዉልድ ወጣትም የወያኔን ዘረኞች የገቡበት ገብቶ አይቀጡ ቅጣት ቀጥቶ የእናት አገሩን አንድነትና የወገኖቹን ነጻነት ያስከብራል።
ዉድ የአገሬ ወጣቶች – መጪዉ አዲስ አመት እስከዛሬ ያጎነበሰዉን አንገታችንን ቀና አድርገንና ከዳር እስከ ዳር ተደራጅተን ወያኔን በህዝባዊ እምቢተኝነና በህዝባዊ አመጽ ከስልጣን ለማስወገድ ወደ ወሳኙ ፊልሚያ የምንገባበት አመት ነዉ። ወያኔ ስልጣን እንደያዘ በቆየ ቁጥር ከማንኛዉም የህብረተሰብ ክፍል በላይ ተስፋዉ የሚደበዝዘዉና የወደፊት ኑሮዉ የሚጨልመዉ ያንተ የወጣቱ ትዉልድ ነዉና ወያኔ ለራሱ ጥቅም የፈጠረልህን አደረጃጀት በመጠቀም ከምታምናቸዉ ጓደኞችህ ጋር ሆነህ እራስህን አደራጅ፤ የነጻነት ሃይሎች ለሕዝብ የሚያሰራጯቸዉን መረጃዎች በየቀኑ ተከታተል፤ የወያኔን ዕድሜ የሚያሳጥሩ እርምጃዎችንም በያለህበት አካባቢ መዉሰድ ጀምር። በዚህ መራራ ትግል ዉስጥ ያንተ የወጣቱ ትዉልድ ትልቁ ጉልበት መደራጀትህና በድርጅታዊ ዲሲፕሊን መታነጽህ ነዉና እነዚህ ሁለት እሴቶች ምን ግዜም እንዳይለዩህ።
ዉድ የአገሬ ወጣት!
ዛሬ ኢትዮጵያ ዉስጥ ስራ የሚያስገኘዉ ትምህርትና ችሎታ ሳይሆን የወያኔ ድርጅቶች አባል መሆን ነዉ፤ እሱ ደግሞ እራስን መሸጥ ነዉና ኢትዮጵያዊ ስለሆንክ ብቻ እንደማታደርገዉ እርግጠኛ ነኝ። ያለ የሌለ ጥሪትህን አፍስሰህ ንግድ ልጀምር ብትልም መንገዱን ይዘጉብሃል ወይም አብዛኛዉን ትርፍህን ለወያኔ ሙሰኞች ካልገበርክ መነገድ አትችልም ይሉሀል። እneዚህን የጠቀስኳቸዉን ሁለት ፍትህ አልባ አሰራሮች ተቃዉመህ አደባባይ ስትወጣ ደግሞ የአግዓዚ አልሞ ተኳሾች ደረት ደረትህን ይሉሀል። ከዚህ ሁሉ ዉጣ ዉረድ በኋለ ያለህ አማራጭ ወይ ለወያኔ ዘረኞች እየሰገድክ መኖር አለዚያም እናት አገርህን ጥለህ መሰደድ ነዉ። እስከዛሬ የተንገላታኸዉ፤ የታሰርከዉ፤ የተገረፍከዉና የጥይት እራት የሆንከዉ ዉድ የአገሬ ወጣት ሆይ – በዚህ አዲስ አመት ዋዜማ ግንቦት 7 ላንተ፤ ለቤተሰቦችህና ለአገርህ የሚበጅ ሦስተኛ አማራጭ ይዞልህ መጥቷል። ከአገርህ አትሰደድም፤ ለወያኔ ዘረኞችም እየሰገድክ አትኖርም ! ወያኔን ፊት ለፊት ተጋፍጠህ አንተንም ወገኖችህንም ነጻ ታወጣለህ። ገና ዋና ዋና ስራዉን ሳይጀምር መኖሩን በማሳወቁ ብቻ ወያኔን ያርበደበደዉ የሕዝባዊ አመጽ ኃይል ዬት እንዳለ ታዉቃለህና በትናንሽ ቡድኖች እራስህን እያደራጀህ ዛሬ ነገ ሳትል ናና ተቀላቀለን። ለግዜዉ ወደ ጫካዉና ወደ ዱሩ መጥተህ መቀላቀል የማትችለዉ ደግሞ ወያኔን በዝቅተኛ ወጪ በፍጥነት ማስወገድ የምንችለዉ ከዉስጥም ከወጭም ስናጣድፈዉ ነዉና የነጻነት ኃይሎች በተከታታይ የሚሰጡህን መረጃ በመከተል እራስህን አደራጅተህ በየአካባቢህ የወያኔ ስርዐት የቆመባቸዉን መሠረቶች አፍርስ።
ውድ የኢትዮጵያ ሕዝብ ሆይ!
የአዲስ አመት ዋዜማ እንደ ግለሰብ በአሮጌዉ አመት በዕቅድ ይዘን ያላከናወንናቸዉን ቁም ነገሮች በአዲሱ አመት ለማከናወን ለራሳችን ቃል የምንገባበት፤ እንደ መሪ ደግሞ ለሕዝብና ለአገር አዲስ ራዕይና አዲስ ተስፋ የምንፈነጥቅበት፤ ከስህተታችን የምንታረምበትና ጠንካራ ጎናችንን ይበልጥ የምናጎለብትበት መልካም አጋጣሚ ነዉ። በዚህ አዲስ አመት ከሃያ ሦስት አመት ስህተታቸዉ ታርመዉና የበደሉትን የኢትዮጵያ ሕዝብ ይቅርታ ጠይቀዉ የፍትህና የነጻነት ትግላችንን አንዲቀላቀሉ የትግል ጥሪ የምናደርግላቸዉ ብዙ ድርጅቶች አሉ። ከእነዚህ ዉስጥ አንዱና ዋነኛዉ አራት ድርጅቶችን ያቀፈዉ ኢህአዴግ የሚባለዉ ድርጅት ነዉ። ወገናችንን እንጠቅማለን ብላችሁም ሆነ በሌላ ሌላ ምክንያት ከጠላታችሁ ከወያኔ ጋር የተቆራኛችሁ የኦህዴድ፤ የባዕዴንና የደኢህዴግ አባላትና መሪዎች ሁሉ በዚህች የአዲስ አመት ዋዜማ ምሽት የበደላችሁትን የኢትዮጵያን ሕዝብ የምትክሱበት መልካም አጋጣሚ መፈጠሩን ሳብስርላችሁ እጅግ በጣም ደስ እያለኝ ነዉ። ልቦና ያላቸዉ ወገኖች በህወሓትም ዉስጥ ይኖራሉ ብለን እናምናለን። ህወሓትን ለቆ ለመዉጣትም የመጨረሻዉ ሰዐት ደርሷልና አሁኑኑ እየለቀቃችሁ ዉጡ። ለአገራቸዉ አንድነትና ዲሞክራሲያዊ እኩልነት የሚታገሉት የደሚሂት ወንድሞቻችን ከሌሎች ወገኖች ጋር አብረዉ እየታገሉ ነዉ። ለሀቅና ለእኩልነት ብለህ ወያኔን የተቀላቀልክ ታጋይ በሙስና የተጨማለቁ ወራዳ መሪዎች ጀሌ መሆንህ ማብቃት አለበት።
በኢህአዴግና በሌሎቹም የወያኔ አጋር ድርጅቶች ዉስጥ የምትገኙ ዉድ ኢትዮጵያዉያን ወገኖቼ – እስከ ዛሬ እራሱን “የትግራይ ሕዝብ ነጸ አዉጭ ግንባር” እያለ የሚጠራዉ ድርጅት ጥቂት ዘራፊ መሪዎች የኢትዮጵያን ሕዝብ ከሃያ አመታት በላይ ረግጦ መግዛት የቻለዉ በቅርጹ ኢትዮጵያዊ በይዘቱ ግን ፍጹም ፀረ ኢትዮጵያ የሆነ ድርጅት ፈጥሮ መንቀሳቀስ በመቻሉ ነዉ። “የአገሩን ሠርዶ በአገሩ በሬ” እንደሚባለዉ ወያኔ “ኢህአዴግ” በሚል ሽፋን የኦሮሚያን፤ የአማራንና የደቡብ ሕዝብ ክልሎችን ተቆጣጥሮ አገራችንን መዝረፍ ባይችል ኖሮ የኢትዮጵያን ሕዝብ እንኳን ሃያ ሦስት አመት አንድ ወርም ተደላድሎ መግዛት አይችልም ነበር። ስለዚህ ከዚህ የሕዝብና የአገር አንድነት ጠላት ከሆነዉ ድርጅት እራሳችሁን እያገለላችሁ ህዝባዊ ትግሉን እንድትቀላቀሉና የኢትዮጵያን ሕዝብ ለማይቀረዉ ድል እንድታበቁት በዚህ ጀግና ሕዝብ ስም እማፀናችኋለሁ።
የኢትዮጵያ ሕዝብ ሆይ! ታታሪ ሠራተኛ ሕዝብና ለሌሎች የሚተርፍ ለምለም አገር ይዘን ዛሬም ስማችን የሚጠቀሰዉ ከድህነት፤ ከኋላ ቀርነትና ከሰብዓዊ መብት ረጋጮች ተርታ ነዉ። ወያኔ ገነባሁ ብሎ የሚነግረን የኃይል ማመንጪያ ግድቦች ብዛት እንኳን ለኛ ለጎረቤቶቻችንም የሚተርፉ ናቸዉ። ነገር ግን አብዛኛዉ የከተማ ነዋሪ በሳምንት ከአንድ ግዜ በላይ መሠረታዊ የመብራት አገልግሎት አያገኝም፤ እራሱን ልማታዊ መንግስት እያለ የሚጠራዉ ወያኔ የአገሪቱ ኤኮኖሚ በድርብ አኀዝ እያደገ ነዉ ማለት ከጀመረ አስር አመታት ተቆጥረዋል፤ ሆኖም የአገራችንና የአፍሪካ መዲና የሆነችዉና ወደ አራት ሚሊዮን የሚጠጋ ሕዝብ የሚኖርባት አዲስ አበባ የዉኃ ያለህ እያለች መጮህ ከጀመረች አመታት ተቆጥረዋል። የወያኔ መሪዎች ይህንን ግዙፍ ማህበረሰባዊ ችግር እያወቁ ችግሩን ለመቅረፍም ሆነ በየቀኑ እያደገ ለሚሄደዉ የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪ የመጠጥ ዉኃ ዘላቂ ዋስትና ለመስጠት የሰሩት ወይም ያቀዱት ምንም ነገር የለም።
ወያኔ የተከተላቸዉ ብልሹ የኤኮኖሚ ፖሊሲዎች አገራችን ዉስጥ የሸቀጥ ዋጋ በየቀኑ እንዲያድግ አድርጓል። ይህ የዋጋ ንረት የፈጠረዉ የኑሮ ዉድነት ደግሞ ወላጆች ልጆቻቸዉን በፈረቃ እንዲመግቡ ከማስገደዱም በላይ በአዲስ አበባና በሌሎቹም ከተሞቻችን ለወትሮዉ የፍቅርና የመቀራረብ ምልክት የነበረዉ ጉርሻ ዛሬ በችርቻሮ የሚሸጥ ሸቀጥ ሆኗል። ኢትዮጵያ ዉስጥ ዕንቁጣጣሽ የሚከበረዉ ቅርጫዉ፤ በጉና ዶሮዉ ተገዝቶ ከቤተሰብና ከወዳጅ ዘመድ ጋር አንድ ላይ በመሆን ነበር፤ ዛሬ ግን የኑሮ ዉድነቱና የዋጋ ንረቱ የኢትዮጵያ ሕዝብ ትላልቅ አመት በአሎቹን ከባህሉና ከወጉ ዉጭ በባዶ ቤት ለብቻዉ እንዲያከብር አስገድዶታል።
ግብር ከፋዩ የኢትዮጵያ ሕዝብ ይህ ሁሉ ችግርና መከራ እየተፈራረቀበት የወያኔ ሹማምንትና ምስለኔዎቻቸዉ ግን በፎቅ ላይ ፎቅ ይሰራሉ፤ የቅንጦት መኪና በየአመቱ ይቀያይራሉ ወይም ቅምጥል ልጆቻቸዉን በሕዝብ ገንዘብ አዉሮፓና አሜሪካ እየላኩ ያስተምራሉ። የኢትዮጵያ ሕዝብ በቀላሉ ሊወገዱ በሚችሉ በሽታዎች አንደ ቅጠል እየረገፈ እነሱና ቤተሰቦቻቸዉ ግን ጉንፋን በያዛቸዉ ቁጥር በሕዝብና በአገር ገንዘብ አዉሮፓና አሜሪካ እየሄዱ ይታከማሉ። ይህ ሁሉ በሕዝብ ላይ የሚያደርሱት በደል አልበቃ ብሏቸዉ በየከተማዉ ቤቶችን እያፈረሱ መሬቱን እነሱ ለሚፈልጉት ባለኃብት ይሸጣሉ። ዉድ የአገሬ ሕዝብ – ለመሆኑ እስከመቼ ነዉ በገዛ አገራችን እፍኝ በማይሞሉ ሰዎች እንደዚህ እየተዋረድን የምንኖረዉ? እስከመቼ ነዉ እነሱ ልጆቻችንን እየገደሉ እኛ እየቀበርን የምንኖረዉ? እስከመቼ ነዉ ግብር ከፋዩ የኢትዮጵያ ሕዝብ ደሞዝ በሚከፍላቸዉ ሰራተኞቹ እየተናቀ፤ እየተዋረደ፤ እየታሰረ፤ እየተገደለና ከአገሩ እየተሰደደ የሚኖረዉ? ለመሆኑ ኢትዮጵያ የነማን አገር ናት? እኛስ የነማን ልጆች ነን?
ዉድ አባቶቼ፤ እናቶቼ፤ እህቶቼና ወንድሞቼ -
እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ለእነዚህ ጥያቄዎች ተገቢዉን ምላሽ የሚሰጥበት ወሳኝ የትግል ምዕራፍ ፊት ለፊታችን ተደቅኗል። 2007 እንደሌሎቹ አመቶች “ዕንቁጣጣሽ በያመቱ ያምጣሽ” ብለን ተቀብለን የምንሸኘዉ አመት አይሆንም፤ መሆንም የለበትም። ነገ የምንቀበለዉ አዲስ አመት ሲገድሉን ዝም ብለን የማንሞት፤ ሲያሳድዱን አገራችንን ትተንላቸዉ የማንሰደድ፤ ሲንቁንና ሲያዋርዱን ደግሞ ክብር፤ ልዕልናና የረጂም ግዜ ታሪክ ያለን ታላቅ ሕዝብ መሆናችንን ለጠላትም ለወዳጅም የምናረጋግጥበት አመት ነዉ። ይህ አመት የአገራችንን የፍትህ፤ የደህንነትና የመከላከያ ተቋሞች እንደ ማጥቂያ መሳሪያ እየተጠቀመ ሲያስረን፤ ሲያዋርደንና ሲገድለን የከረመዉን ዘረኛ አገዛዝ ለማስወገድ ተግባራዊ እርምጃዎችን መዉሰድ የምንጀምርበት የድልና የመስዋዕትነት አመት ነዉ። ይህ አመት እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ከወያኔ ጋር በሚደረገዉ የነጻነት ትግል ዉስጥ የኔ ድርሻ ምንድነዉ የሚለዉን ጥያቄ እራሱን ጠይቆ መልሱንም እሱ እራሱ የሚመልስበት አመት ነዉ። ነጻና ፍትሃዊ በሆነችዉ ኢትዮጵያ የሚጠቀመዉ ሁሉም ኢትዮጵያዊ እንደሆነ ሁሉ ኢትዮጵያን ነጻና የእኩሎች አገር ለማድረግ በሚደረገዉ ትግልም እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ የነቃ ተሳትፎ ማድረግ አለበት።
የኢትዮጵያ ሕዝብ ሆይ!
ወያኔዎችን በድርድር ሞከርናቸዉ፤ በምርጫ ሞከርናቸዉ በሠላማዊ መንገድም በሁሉም አቅጣጫ ሞከርናቸዉ፤ ለእነዚህ ሁሉ ሙከራዎቻችን የሰጡን ምላሽ አርፋችሁ ተገዙ፤ ትታሰራላችሁ ወይም ኢትዮጵያን ለቅቃችሁ ዉጡ የሚል የዕብሪትና የንቀት መልስ ነዉ። ግንቦት 7 የፍትህ፤ የነጻነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ከሎሎች አጋር ድርጅቶች ጋር በመሆን አንገዛም፤ ከህግ ዉጭ አንታሰርም፤ አገራችንንም ለቅቀን አንወጣም የሚል ጽኑ አላማ አንግቦ ታግሎ ሊያታግላችሁ ዝግጅቱን አጠናቅቆ ኑና ተቀላቀሉኝ እያለ ነዉ ። ንቅናቄያችን የኢትዮጵያን አንድነት፤ ሠላምና ብልጽግና ለማረጋገጥ የወያኔ ስርዐት መወገድ አለበት ብሎ ያምናል፤ ይህ እምነታችን፤ ለእናት አገራችን ኢትዮጵያ ያለን ፍቅርና፤ የነጻነት ጥማታችን ወደትግሉ ሜዳ እንድንገባ አድርጎናል። ይህ ትግል ወያኔን ለማስወገድ ብቻ የሚደረግ ትግል ሳይሆን የተረጋጋ፤ ጤናማና በዲሞክራሲ መሠረቶች ላይ የቆመ አስተማማኝ የፖለቲካ ስርዐት ለመፍጠርም ጭምር የሚደረግ ትግል ነዉ።
የኢትዮጵያ ሕዝብ ሆይ!
ማለት የሚገባንን ሁሉ ብለን ጨርሰናል፤ ካሁን በኋላ ማድረግ የሚገባንን ሁሉ ማድረግ አለብን። ሁለገብ ትግሉ ተጀምሯል። ይህ አመት የትግል አመት ነዉ፤ ይህ አመት የመስዋዕትነት አመት ነዉ፤ ይህ አመት ድል የምናሸትበት አመት ነዉ። ይህ ትግል የገበሬዉን፤ የሠራተኛዉን፤ የወጣቱን፤ የሴቶች እህቶቻችንና የመከላከያ ሠራዊቱን የቀን ከቀን ተሳትፎና መስዋዕትነት ይጠይቃል። እኔም የትግሉን ወደ አዲስና ወሳኝ ምዕራፍ መድረስ እያበሰርኩ ኑና ለክብራችንና ለነጻነታችን እንታገል የሚል የትግል ጥሪ ለእያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ አስተላልፋለሁ።
የጀመርነዉን ትግል በድል እንደምንወጣዉ ጥርጥር የለኝም !!!!
መልካም አዲስ አመት -


    ደህና እደሩ
    source ginbot7.org

    Thursday, September 11, 2014

    2007 ወሳኝ የትግል ዓመት!!!

    September 11,2014
    ሁለት ሺህ ስድስት ዓመተ ምህረት ለኛ ለኢትዮጵያዊያን በአብዛኛው በመጥፎ የሚታወስ ዓመት ነው። 2006፣ በመካከለኛው ምስራቅም ሆነ በአፍሪቃ በስደት ላይ የሚገኙ ወገኖቻችን ላይ የሚደርሰው ስቃይ ከፍተኛ ደረጃ ላይ የደረሰበት ዓመት ነበር። 2006፣ ቀደም ባሉ ዓመታት አገራቸዉን ለቅቀዉ የተሰደዱ ሳይደላቸው በርካታ አዳዲስ ስደኞች ከአገር ወጥተው በበረሃዎችን ቀልጠው፤ በባህር ሰጥመው ያለቁበት አሳዛኝ ዓመት ነው። 2006፣ ጥንቃቄ በተሞላበትና በተቆጠበ መንገድም ቢሆን የተቃውሞ ድምጽ ያሰሙ ወገኖቻችን ወደ እስር ቤቶች የተጋዙበት ዓመት ነው። 2006፣ በአምቦ፣ በለቀምት፣ በጅማ በሀረር በርካታ የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች የተገደሉበት፤ በአስር ሺዎች የሚገመቱት ደግሞ የታሰሩበት ዓመት ነው። 2006፣ በአፋር፣ በኦሮሚያ፣ በደቡብ፣ በቤንሻንጉል፣ በጋምቤላ፣ በአዲስ አበባና አካባቢው በ100 ሺዎች የሚገመት ኢትዮጵያዊ የተፈናቀለበት ዓመት ነው። 2006 ቁጥራችው ቀላል ያልሆኑ የነፃነት ታጋዮች ከጎረቤት አገራት ታፍነው ወደ እስር ቤቶች የተጋዙበት ዓመት ነው። 2006 የንቅናቄዓችን ዋና ፀሐፊ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በጉዞ ላይ እያለ በትራንዚት አውሮፕላን ለመቀየር ባረፈበት በየመን ዋና ከተማ ሰንዓ በየመን መንግሥት ወንበዴዎች ታፍኖ ለሸሪካቸው ህወሓት በህገወጥ መንገድ አስተላልፈው ለስቃይ እንዲዳረግ የተደረገበት ዓመት ነው። በእነዚህ ሁሉ ምክንያቶች ነው 2006 “ጥቁር ዓመት” የሚል ስያሜ ያገኘው።
    ጭንቅላት የሚባል ነገር ያልፈጠረባቸው ድኩማን ሰላዮችና ፈንጋዮች የመጨረሻውን የመንግሥት ሥልጣን የያዙበትና ውሳኔያቸው “እሰረው፣ ክሰሰው፣ ግረፈው፣ ግደለው …” ብቻ የሆነበት ዓመት መሆኑ የ2006 ልዩ መታወቂያው ሆኖ ይቆይ ይሆናል። ይሁን እንጂ በ2006 ጨለማ ውስጥ የታዩ የብርሃን ጨረሮችም እንደነበሩና እንዳሉም መርሳት አይገባም።
    በሁለት ሺህ ስድስት ዓመተ ምህረት የኢትዮጵያ ሕዝብ ከመቸውም በላይ በህወሓት አገዛዝ አምርሯል፤ በሁለገብ ትግል የህወሓትን አገዛዝ ለመፋለም የቆረጡ ወገኖች ትብብር ተጠናክሯል። በ2006፣ ኢትዮጵያ ዉስጥም ከኢትዮጵያም ውጭም የንቅናቄዓችን የግንቦት 7 ድርጅታዊ መዋቅር ተጠናክሯል። በ2006፣ ከህወሓት አገዛዝ ጋር ያለው መፋጠጥ ከሯል። እነዚህ ሁኔታዎች 2007 አገራችን በለውጥ ማዕበል የምትናጥበት ዓመት ሊሆን እንደሚችል ያመለክታሉ።
    በአዲሱ ሁለት ሺህ ሰባት ዓመተ ምህረት፣ የግንቦት 7 አባላትና ደጋፊዎች ትልቁ ሥራ ድርጅታዊ አቅምን ማጎልበት ነው። በተለይ ወጣቶች በአምባገነን ሥርዓቶች ውስጥ ሕዝባዊ የትግል ድርጅቶችን እንዴት መመሥረት እንደሚቻል ማጥናት እና መፈተሽ ይኖርባቸዋል። ትናንሽ የግንቦት 7 ድርጅታዊ ቋጠሮዎች በመላው አገሪቱ መሠራጨት ይኖርባቸዋል። ወጣቶች ትናንሽ ኢ-መደበኛ ስብስቦችን ቶሎ መፍጠር እና አደጋ ሲያጋጥም ቶሎ ማፍረስ መልመድ ይኖርባቸዋል። ይህንን ክህሎት ደግሞ በቀጥታ ከሌሎች አገራት ከመዋስ ሀገር በቀል ቢሆን ይመረጣል።
    በሁለት ሺህ ሰባት ዓመተ ምህረት፣ የጽዋ ማኅበሮች፣ መድረሳዎችና ጀማዎች፣ የስፓርት ቡድኖችና ደጋፊዎች፣ የመንደር ደቦዎችና የቡና ተርቲቦች፣ ስም ያላቸውም፣ ስም የሌላቸውም ስብስቦች የግንቦት 7 አባላት መገናኛዎች ይሆናሉ። በ2007 የግንቦት 7 አባል መሆን የምርጥ ዜግነት ምልክት መሆኑ በስፋት ተቀባይነት የሚያገኝበት ዓመት ይሆናል ብለን ተስፋ እናደርጋለን። በ2007 በህወሓት ካድሬዎች “ሽብርተኛ” መባል የሚያስደስትና እንደ ሽልማት ተደርጎ የሚወሰድበት ዓመት ይሆናል ብለንም ተስፋ እናደርጋለን። በ2007 እስር ማስፈራሪያ መሆኑ ያከትማል። በ2007 የኢትዮጵያ ወጣቶች በአርበኝነታቸው ይታወቃሉ። በ 2007 እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ የህወሓት ሹማንምትን ዘረፋ የሚያጋልጥበት ዓመት ይሆናል። 2007 ዳኞች “እንቢ፣ በሀሰት አንፈርድም”፤ የመንግሥት ጋዜጠኖች “እውነቱን ደብቀን አንዋሽም”፤ ፓሊሶች “ወገናችንን አንደበድብም፣ አናስርም፣ አንገርፍም”፤ ወታደሮች ደግሞ “በወገናችን ላይ አንተኩስም” የሚሉበት ዓመት ይሆናል ብለን ተስፋ እናደርጋለን።
    በዚህም ምክንያት 2007ን የምንቀበለው በታላቅ ተስፋና ዝግጅት ነው። በ 2007 ነፃነትና አምባገነንነት፤ ዘረኛነትና አንድነት፤ እውነትና ውሸት፤ አድርባይነትና አርበኝነት፤ ዝርፊያና ንጽህና፤ ድህነትና ብልጽግና የሚፋጠጡበት ዓመት ይሆናል ብለን እንጠብቃለን። በአጭሩ 2007 የወሳኝ ትግል ዓመት ይሆናል።
    ሁለት ሺህ ሰባት ዓመተ ምህረት፣ የኢትዮጵያ መፃዒ እድል የሚወሰንበት ዓመት በመሆኑ ሁላችንም በተነሳሳ የአርበኝነት መንፈስ እንድንቀበለው ግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ጥሪ ያደርጋል።
    መልካም አዲስ ዓመት!
    ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ !
    source ginbot7.org

    ሚሊየነሩ ጄ/ል (ከኢየሩሳሌም አርአያ)

    (በፎቶው ጄ/ል ዮሃንስ ገ/መስቀል)
    September 11,2014
    የሕወሐት ታጋይ ጄ/ል ዮሃንስ ገ/መስቀል ቦሌ ቴሌ መድሃኒያለም ባለ6 ፎቅ ህንፃ እንዳስገነቡ የቅርብ ምንጮች አጋለጡ።
    ከ95ሚሊዮን ብር በላይ በሚደርስ ወጪ እንደተገነባ የተነገረለት ይኸው ባለ6 ፎቅ ዘመናዊ ህንፃ ለተለያዩ የግልና የመንግስት ባንኮች፣ ኢንሹራንስ ድርጅቶች፣ ንግድ ቤቶችና የተለያዩ ድርጅት ቢሮዎች እንደተከራየ የጠቆሙት ምንጮቹ በወር ከ2.1 ሚሊዮን ብር የሚገመት ኪራይ ጄኔራሉ እንደሚሰበስቡ አስታውቀዋል።
    ሌ/ጄ ዮሃንስ በግላቸው ባለ6 ፎቅ ዘመናዊ ህንፃ በከፍተኛ ወጪ በማስገንባትና ከፍተኛ የኪራይ ሂሳብ በየወሩ በመሰብሰብ ከሌሎቹ በቢዝነስ ከተሰማሩ የሕወሐት/ኢህአዴግ ጄኔራል መኮንኖች የተለየ እንደሚያደርጋቸው ምንጮቹ አመልክተዋል። በአገር መከላከያ ሚኒስቴር የመረጃ ዋና መምሪያ ሃላፊ ሆነው ለረጅም አመታት ሲሰሩ የቆዩት የህወሐቱ ጄኔራል ዮሃንስ ገ/መስቀል ከ1995ዓ.ም ጀምሮ ከጄ/ል ሳሞራ የኑስ ጋር የከረረ ቅራኔ ውስጥ ገብተው እንደቆዩና በሁለቱ የህወሀት ጄኔራሎች መካከል የተፈጠረው ቅራኔ እየተባባሰ ሄዶ ጄ/ል ዮሃንስ ከሃላፊነት እንዲነሱ መደረጉን ያስታወሱት ምንጮቹ የሁለቱ ቅራኔ ሙስናን መሰረት ያደረገ እንደነበረ አስረድተዋል። (በወቅቱ ስለግጭታቸውና መለስ ዜናዊ ዘንድ ቀርበው ስለተነጋገሩት በኢትኦጵ ጋዜጣ መረጃው ይፋ ተደርጐዋል)  ጄ/ል ዮሃንስ ከመከላከያ ሃላፊነታቸው እንዲነሱ የተደረጉት በጄ/ል ሳሞራ መሆኑን ያስታወሱት ምንጮቹ በወቅቱ “ጡረታ” በሚል እንደተነሱና ሲነሱም በሜ/ጄኔራል ማእረግ እንደነበሩ አስታውቀዋል።
    በሙስና ባገኙት በመቶ ሚሊዮን የሚገመት ገንዘብ ሕንፃ ወደማስገንባት የግል ቢዝነስ የተሰማሩት ጄ/ል ዮሃንስ ከአራት አመት በኋላ በመከላከያ የሌተና ጄኔራልነት ማእረግ ባሳለፍነው ሰኔ ወር ተሰጥቷቸው በደቡብ ሱዳን የሚሰማራውን የተመድ ሰላም አስከባሪ ሰራዊት በጦር አዛዥነት እንዲመሩ መመደባቸው አስገራሚ ነው ያሉት ምንጮቹ ምክንያቱም ጡረታ ተብለው የተሰናበቱት ዮሃንስ የሌተና ጄኔራል ማእረግ እድገት ተሰጥቷቸው መመለሳቸው በመከላከያ ታሪክ የመጀመሪያው ሊያደርጋቸው ስለሚችል ግርምት ሊፈጥር ችሏል ብለዋል። ዮሃንስ የአገር መከላከያ ሚ/ር የሌ/ጄኔራል ማእረግ እንዲሰጣቸውና በተመድ እንዲመደቡ የተደረገው በአሜሪካ ትእዛዝ መሆኑን ምንጮቹ አመልክተዋል። በቦሌ ለንደን ካፌ ፊት ለፊት ዘመናዊ መኖሪያ ካስገነቡት ጄኔራሎች አንዱ ናቸው።
    ምንጭ የኢትዮጵያ ሜዲያ መድረክ


    Free Andargache​w – New website launched



    Friends and families of  Andargachew Tsege have created a new website to help the campaign to free Andargachew Tsege from Ethiopian prison.
    Here is the link to the Website dedicated to Andargachew. :  http://www.freeandargachew.com
    source ethioforum.org

    Sunday, September 7, 2014

    የለውጡ አካል መሆኛው ግዜው አሁን ነው

    september 7,2014
    እኔም አንዳርጋቸው ነኝ የሚል ድምፅ ከአጥናፍ እስከ አጥናፍ እያሰተጋባ ነው። ይሄን ድምፅ የሚያቆመው አንዳችም ምድራዊ ኃይል አልተገኘም። ኢትዮጵያዊ ባለበት ሥፍራ ሁሉ ይሄ ድምፅ ከፍ ብሎ እየተሰማ ነው። ይህንንም ተከትሎ “ላንቺ ነው ኢትዮጵያ፤ ላንቺ ነው ኢትዮጵያ” የሚለው መዝሙር በኢትዮጵያ ተራሮች እናት ላይ እየተዘመረ ነው። ፍትህ ተዋርዳለች፤እኩልነት ጠፍቷል፤ ነፃነት የለም ያሉ ምርጥ ኢትዮጵያዊያን ሳያቅማሙ አያቶቻቸው በተመላለሱበት ተራሮች ላይ ተሠማርተዋል። ሞትንም ንቀው ጋሻ አንስተዋል፤ ሰይፋቸውንም መዘዋል። ለፍትህ፤ ለዕኩልነት እና ለነፃነት የተመዘዘው ሰይፍ ከእንግዲህ ወደ ሰገባው እንደማይመለስ ህወሃቶች እንዲያውቁት እንፈልጋለን።
    በኢትዮጵያችን ፍትህ ከጠፋ ብዙ ዘመን ሁኖታል። ከሁሉም ዘመን የህወሃቶች ዘመን ግን የተለየ ነው። ህወሃቶች ህግን ዜጎችን የማጥቂያ መሣሪያ አድርገው መጠቀማቸው ከሌሎች እንዲለዩ ያደርጋቸዋል። እነዚህ ቡድኖች ሥፍር ቁጥር የሌላቸው ቂም መወጣጪያ ህጎችን አውጥተዋል። እንዲህ በማድርጋቸውም ሠላም እናገኛለን ብለው ያስባሉ። የህወሃቶች አስተሳሰብ ደካማና እርባና ቢስ መሆኑን ከሚያሳዩ ተግባሮቻቸው መካከል አንዱ ይሄው በፍትህ ሳይሆን በህግ ብዛት ሠላም እናገኛለን ብለው ተስፋ ማድረጋቸው ነው። የህግ ብዛት ሠላምን አያስገኝም፤ ፍትህንም ማስፈን አይችልም። እንዲያውም ህግ በበዛ ቁጥር ፍትህ እየጎደለች እንደምትሄድ የህወሃቶች ድርጊት ደህና ምስክር ነው። እነርሱ ዜጎችን ለመበቀያ ብለው የሚያወጧቸው ጥቃቅን ህጎች እነርሱ “ህገ መንግስት” ብለው የሚጠሩትን የሚንዱ እና ፍትህን ዋጋ የሚያሳጡ ሁነው እያየናቸው ነው። የፀረ ሽብር ህጉ በህገ መንግስቱ የተቀመጠውን የዜጎችን የመናገር የመደራጀትና በሰላማዊ መንገድ የመንግስትን እኩይ ተግባራት የመቃወምን መብት የገፈፈ ነው። የፀረ ሙስና ህጉም ቢሆን እንዲሁ ነው። በፀረ ሙስና ህጉ የሚጠየቁ በህወሃት የተጠሉ ብቻ ስለመሆናቸው በሙስና የተጨማለቁት የህወሃት ሹማምንት ህያው ምስክሮች ናቸው። በህወሃቶች ህግ ሁሉም ዜጎች እኩል አይደሉም። ህወሃቶች ከሌሎች ይበልጣሉ። የህወሃቶች ምኞት እነርሱ ከህግ በላይ፤ ሌላው ህዝብ ከህግ በታች ሁነው ህወሃትን ተሸክመው እንዲኖሩ ነው። እንዲህ ዓይነቱን ኢ-ፍትሃዊነት መታገል ግዜው የሚጠይቀው ታሪካዊ ግዴታ ነው። መሪያችን አንዳርጋቸው ፅጌ የተነሳውም ህወሃቶች መሣቂያ መሳለቂያ ያደረጓትን ፍትህ ወደ ሚገባት ክብር ለመመለስ ነው። በአገራችን የህግ የበላይነት ሠፍኖ ጥቂቱ ብዙሃኑን ሳይጫን፤ ማንም ማንንም ሳይሸከም ሁሉም በህግ እና በፍትህ እኩል ሁኖ የሚኖሩባት ሠላም የበዛላት ሥፍራ እንድትሆን የመሪያችን የአንዳርጋቸው ምኞት ነው። ይሄን ምኞት ሚሊየኖች አንግበው ተነስተዋል።
    ህወሃቶች አገራችንን አደጋ ላይ ከጣሉባቸው አንኳር ድርጊቶቻቸው መካከል አንዱ በዜጎች መካከል እየፈጠሩ ያሉት ግልፅ ልዩነት ነው። ህወሃቶች ከሌሎች ኢትዮጵያውያን ጋር እኩል ነን የሚል እምነት የላቸውም። የህወሃቶች ዕምነት እነርሱ ከሌላው ኢትዮጵያዊ ከፍ እንደሚሉና በዚያች አገር ውስጥ የተለየ መብት እንዳላቸው ነው። ለመገድልም፤ ለመዝረፍም፤ዜጎችን ለማሳቃየት እና ከአገር ለማባረርም መብቱ የእኛ ነው የሚል ጅላጅል እምነት አላቸው። ይህ የሞኝ እምነታቸው በዜጎች መካከል ቂመ በቀል ሊያተርፍ የሚችል አድሎዎ እንዲፈጥሩ አድርጓቸዋል። አድሎአቸውንም ይበልጥ የከፋ የሚያደርገው ህወሃቶች ሁሉን አድራጊ እኛ ነን ብለው ሲያበቁ የህወሃት የበላይነት የለም ብላችሁ እምኑ ብለው ዜጎችን መጫናቸው ነው። ይህ ድርጊታቸው ብዙ ዜጎችን አስቆጥቷል። ህወሃቶች ግን የዜጎችን ቁጣ የሚያይ ዓይን፤ የሚያስተውል ሂሊና ርቋቸዋል። በኢትዮጵያችን በህወሃቶች አማካኝነት እየተፈጠረ ያለው ግልፅ አድልዖ ለአገራችን ህልውና ከፍተኛ አደጋ ነው። በህዝብ መካከል አድልዖ መፈፀም እና ቂምና በቀልን መትከል የህወሃቶች የመኖሪያ ድንኳናቸው ሁኗል። መከፋፈልና አድልዖ ባለበት አገር ውስጥ ሠላም ይኖራል ማለት አይቻልም። አድልዎ የታላላቅ ግጭቶችና ለውጦች ጥሩ ምክንያት መሆኑን መርሳት አይገባንም።መሪያችን አንዳርጋቸውም ሆነ ግንቦት ሰባት ንቅናቄ የተነሳው እንዲህ በዜጎች መካከል የሚፈፀመውን አድልዖ ለማስቆምና ዜጎች በገዛ አገራቸው በእኩልነት የሚኖሩበትን ሁኔታ ለመፍጠር ነው። ይህ የእኩልነት ጥያቄ የግንቦት ሰባት ንቅናቄ ብቻ ሳይሆን የሁሉም ዜጎች ጥያቄ ሁኖ ከኢትዮጵያ እስከ ውጪ አገራት ድረስ እያሰተጋባ ነው።
    ሌላው ህወሃቶች አገሪቷን እያዋረዱ ካሉበት ነገሮች መካከል አንዱ የነፃነት ጥያቄ ነው። እኛ ከመጣን በኋላ በኢትዮጵያ ነፃነት ሰፈነ እያሉ ያላዝናሉ። ህወሃቶች ከነፃነት ጋር ተያይዞ ሊመጣ የሚችለውን ኃላፊነት ለመረዳትና ለመሸከም ከፍተኛ የሆነ የአስተሳሰብ ድክመት አለባቸው። ከነፃነት ጋር የሚመጣውን ኃላፊነት ለመሸከም ብቻ ሳይሆን የነፃነትንም ትርጉም ለመረዳት ከፍተኛ የሆነ የእውቀት ማነስ ችግር ያለባቸው መሆኑም ይታወቃል። ራሳቸውን ከታሰሩበት የድንቁርና ሰንሰለት ማስፈታት ሳይችሉ ከሰሞኑ የከፍተኛ ተቋም ተማሪዎችን ሰብስብው የእኛን አብዮታዊ ዲሞክራሲ ካልስተማርናችሁ ትምህርታችሁን አትቀጥሉም ሲሉ ማሰብ ማቆማቸውን ቁልጭ አድርጎ የሚያሳየን አንድ እውነት ሁኖ አግኝተነዋል። ማሰብ የሚችሉ ቢሆኑማ ኑሮ ነፃነት ማለት ‘የእናንተን አብዮታዊ ዲሞክራሲ መስማት አልፈልግም ማለትን’ እንደሚጨምር ያውቁ ነበር። ነፃነትን የማያውቁት ነፃ አውጪዎች ነን ባዮቹ ህወሃቶች ግን ተማሪው መስማት የማይፈልገውን አብዮታዊ ዲሞክራሲ አስገድደው እየጋቱት ይገኛሉ። ለሚቀጥለውም አርባና ሃምሳ ዓመት ስልጣኑን ለማንም አሳልፈን የምንሰጥ አይደለንም ሲሉ በድፍረት ተናግረዋል። የዚህ ሁሉ ድፍረት ምንጭ ህወሃቶችን የተፀናወታቸው እኔ ብቻ ከሚል ከንቱ አስተሳሰብ የመነጨው ስግብግብነታቸው መሆኑን መገነዘብ ያስፈልጋል።
    እንግዲህ ፍትህ መቀለጃ ሁናለች፤ እኩልነት ተጓድሏል፤ ነፃነት ጠፍቷል የሚሉ ዜጎች ከሁሉም አቅጣጫዎች ድምፃቸውን እያሰሙ ነው። የህዝቡ ብሶትም ፅዋውን ሞልቶ እየፈሰሰ ነው፤ ቁጭቱም ከመቸውም ግዜ በላይ ግሏል። ከሰሞኑ በሃያ ስድስት ታላላቅ ከተሞች የተደረጉት ውይይቶችም ያሳዩን አንድ እውነት ህዝቡ ይበልጥ መቆጣቱን ነው። ቁጣውም የተገለፀበት መንገድም ሌላው አስደማሚ ጉዳይ ነው።“እኛም አንዳርጋቸው ነን” ሲሉ ድምፃቸውን ከፍ አድርገው አሰምተዋል። ከእንግዲህ ፍርሃት ሆይ መወጊያህ ወዴት አለ የሚሉ ኢትዮጵያዊያን ድምፃቸውን ከፍ አድርገው ላንቺ ነው ኢትዮጵያ፤ ላንቺ ነው ኢትዮጵያ እያሉ ዘምረዋል። ይሄ ለፍትህ፤ ለእኩልነትና ለነፃነት ለሚታገሉ ታጋዮች ተስፋ ሰጪ ምልክት ነው።
    ህወሃቶች በሠላማዊ መንገድ ለሚደረገው ትግል መንገዱን ሲያደናቅፉ እሰከ ዛሬ ዘልቀዋል። አሁን ጭራሹን ገና ሃምሳ የመከራ ዘመን እየተመኙልን ነው። ይሄ ምኞታቸው ቅዥት ሁኖ እንደሚቀር እኛ ልናስታውሳቸው እንፈልጋለን። በዚያች አገር ለውጥ መምጣት አለበት። ለውጡ በዛፍ ላይ የተንጠለጠለ የጎመራ ፓፓያ አይደለም በራሱ ወደ ምድር የሚወርድ፤እኛ ራሳችን ልናወርደው የሚገባን እንጂ። ተፈላጊውን ለውጥ ለማምጣት እያንዳንዱ ዜጋ በቻለው መሣሪያና ባለው አቅም ሁሉ ለልውጡ ሳያቅማማ መታገል ይኖርበታል። ህወሃቶች ነፃነታችንን አይሰጡንም፤ ፍትህም ከእነርሱ እጅ የምትገኝ አይደለችም፤ እኩልነትንም የሚያውቁ አይደሉም እነዚህ ወርቃማ እሴቶች በትግል የሚገኙ ናቸው። እነዚህን ክቡር ስጦታዎች አስነጥቆ ዝም ያለ ወደ መታረጃው ሥፍራ የሚነዳ ከብትን ይመስላል። ብዙ ኢትዮጵያዊያን እንዲህ መሆንን የሚምርጡ አይደሉም። በየከተሞቹ በተደረገው ውይይት ከተገነዘብናቸው እውነቶች መካከል አንዱ ዜጎች ለፍትህ፤ለእኩልነት እና ለነፃነት አስፈላጊውን መሥዋዕትነት ለመክፈል ዝግጁ መሆናቸውን ነው።
    በህወሃት ዘመነ መንግስት የመከራ እንባችሁን በመዳፋችሁ የምታፍሱ፤ ህወሃት በአገሪቷ ላይ እያደረሰ ያለው የጥፋት ድርጊት የሚያነገበግባችሁ እና ምን እናድርግ መሪ አጣን የምትሉ ስሙን! መሪ ካጣችሁ እንዲህ አድርጉ “ራሳችሁ ተነሱና መሪ ሁኑ!”። ከምታምኗቸው ጥቂት ወዳጆቻችሁ ጋር ሁናችሁ ተደራጁ፤ አንዳችሁ አንዳችሁን አድምጡ፤ ጥሩ ተመሪ መሆን ከቻላችሁ ጥሩ መሪ ወጥቷችኋል ማለት ነው። የአገራችን ፈርጀ ብዙ ችግር በጥቂት ዜጎች ብቻ የሚቀረፍ አይደለም።የሁሉንም ቁርጠኛ ዜጎች ትግል የሚጠይቅ ነውና በየመንደራችሁ ተደራጅታችሁ የጎበዝ አለቃ መርጣችሁ ዘረኞችን፤ ዘራፊዎችንና አድሎዋዊ ሥርዓት የዘረጉባችሁን ታገሏቸው። እንዲህ ካደረጋችሁ ከእኛ ጋር ለመገናኘት መንገዱ ቀላል ይሆናል።
    የግንቦት ሰባት ንቅናቄ ጥያቄ አጭርና ግልፅ ነው። ፍትህ፤ ነፃነትና እኩልነት በኢትዮጵያችን ይሰፈን ነው። የህወሃትን ዘረኝነትና አምባገነንነት የሚፀየፍ ሁሉ የንቅናቄያችን ደጋፊ ነው። እነዚህን ነገሮች በኢትዮጵያ ለማስፈን በሚችለው ሁሉ ርምጃ መውሰድ የጀመረ የንቅናቄያችን አካል ነው። እኛም ከጎኑ አለን። እንዲህ በማድረግ የማይቀረውን ለውጥ አናመጣለን። ለውጡ ይመጣል አንድም የተፈጥሮ ህግ ስለሆነ፤ አንድም ደግሞ እኛ ሳናቅማማ የፈለግነውን ለውጥ ለማምጣት ስለተነሳን።
    ህወሃቶች መስልጠን የማይችሉ፤ ከአዲስ አስተሳሰብ ጋር ራሳቸውን ማዋሃድ የማይሆንላቸው ፍፁም ግትሮች መሆናቸውን በተዳዳጋሚ አይተናል። ይሄን ግትርነታቸውን እንደ ጀግንነት ይቆጥሩታል። በአገራችን ደህና አባባል አለች እንዲህ የምትል “ሞኝ አሸነፈ ምን ብሎ? እምቢ ብሎ” ይባላል። ህወሃቶችን በዚህ አባባል መግለፅ ሞኝ ያስመስላቸዋል እነርሱ ግን ሞኞች አይደሉም ጨካኞች እንጂ። የጭካኔያቸው ምንጭ ደግሞ በራሳቸው የማይተማመኑ ደካሞች መሆናቸው ነው። እነርሱ ከዛሬ ሠላሳ ዓመት በፊት በመስታወት ውስጥ ያዩትን የራሳቸውን ምሥል ዛሬም መልሰው ያንኑ ምሥል እያዩት ነው። ከሠላሳ ዓመት በኋላም ሊቀየሩ አልቻሉም። ከዚያ ካረጀው ምሥላቸው ላይ ዓይናቸውን ነቅለው ግዜው እና ሁኔታው የፈጠረውን በአካባቢያቸው ያለውን አዲስ ምሥል ለማየት አቅቷቸውል። ስለዚህ ህወሃቶችን ማስወገድ ግድ ነውና ሁሉም በያለበት ለሚመጣው ለውጥ ራሱን ያዘጋጅ፤ የለውጡም አካል ይሁን እንላለን።
    ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ !
    source www.ginbot7.org