Tuesday, October 29, 2013

ስለማህበረ ቅዱሳን ታሪክ ዝርዝር መረጃ የጠየቃችሁን የተዋህዶ ልጆች እንደሚከተለው እናቀርባለን:: የተዛባ አመለካከት የማይጋርደው ገሐድ እውነታ!!!!!

ስለማህበረ ቅዱሳን ታሪክ ዝርዝር መረጃ የጠየቃችሁን የተዋህዶ ልጆች እንደሚከተለው እናቀርባለን::
የተዛባ አመለካከት የማይጋርደው ገሐድ እውነታ
ማኅበረ ቅዱሳን ማን ነው? ምንስ እየሠራ ነው? ክፍል አንድ

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሊቃውንት ብራና ዳምጠው፤ ቀለም በጥብጠው፣ ብዕር ቀርጸው በየአብያተ ክርስቲያናቱ የመቃብር ቤቶች ውስጥ በማስተማር ትውልዱ የሀገር መሪ፣ የቤተክርስቲያን አለኝታ፣ የእግዚአብሔር ቅን አገልጋይ እንዲሆን ያበረከቱት አገልግሎት ከዘመን ዘመን እየተሸጋገረ ለትውልድ ሲተላለፍ የኖረና የሚኖር ነው፡፡

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ለሀገራችን ሥልጣኔ በር ከፋች ሆና የኖረች ከመሆኗም በላይ ዛሬ ላለው ዘመናዊ ሥልጣኔም መሠረት የጣለች ባለውለታ ናት፡፡ ቀደምት የቤተክርስቲያን አበው ደከመን፣ ሰለቸን ሳይሉ ዐረፍተ ዘመን እስከገታቸው ድረስ ሲያገለግሉ ኖረው ቤተክርስቲያኒቱ አሁን ከምትገኝበት የዕድገት ደረጃ አድርሰዋታል፡፡
በዚህ ዘመንም የሚገኙ የቤተክርስቲያኒቱ ልጆች ሁሉ ይህን ከአበው የተማሩትን ሃይማኖትና ሥርዓት ጠብቀውና አስጠብቀው ለሚመጣው ትውልድ የማቆየት ሓላፊነት ያለባቸው መሆኑ ግልጽ ነው፡፡

በመሆኑም ይሔንን አባቶች ወዛቸውን አንጠፍጥፈው፣ ዐይናቸውን አፍዘው፣ ደማቸውን አፍስሰውና አጥንታቸውን ከስክሰው በሰማዕትነትና በተጋድሎ ያቆዩትን ሃይማኖት ለማስጠበቅና ለቀጣዩም ትውልድ በተመቻቸ ሁኔታ ለማስተላለፍ በእግዚአብሔር ፈቃድ በቅዱስ ሲኖዶስ ሙሉ ድጋፍና ዕውቅና የተመሠረተው ማኅበረ ቅዱሳን በውጪ በአጽራረ ቤተክርስቲያንና በአሕዛብ፣ በውስጥ ዓላማውን ባልተረዱ፣ ዓላማውን ተረድተው የኑፋቄ ትምህርታቸውን እንደልብ በቤተክርስቲያኒቱ ውስጥ ለማስረግ ሌት ተቀን በሚተጉ አንዳንድ ግለሰቦችና ቡድኖች ከተመሠረተበት ጊዜ ጀምሮ እየተከሰሰ እየተወቀሰና ያለ ስሙ ስም እየተሰጠው ይገኛል፡፡

እነዚህ በውስጥና በውጭ የሚገኙት የቤተክርስቲያን ጠላቶች ቤተክርስቲያን ላይ በየዘመኑ በሚነሳው ፈተና እየተጠቀሙና በምክንያት እየተሳቡ ለቤተክርስቲያን ወዳጅ መስለው እየቀረቡና እያስቀረቡ ማኅበረ ቅዱሳንን ቢቻላቸው እንዲፈርስ፣ ባይቻላቸው ደግሞ የቤተክርስቲያኒቱን ሥርዓት ለማፍረስ በገንዘብ፣ በቁሳቁስ የሚያስታጥቋቸው መናፍቃን ሴራና ዓላማ እንዳይጋለጥ እና በቤተክርስቲያኒቱ ላይ እንደፈለጋቸው እንዲሆኑ ማኅበሩ አገልግሎቱ ተገድቦ እንዲዋቀር ለማስደረግና ለማድረግ የጥፋት ዘመቻዎችን በመክፈት ላይ ናቸው፡፡

እነዚህ የቤተክርስቲያን ጠላት ወዳጆች በማኅበረ ቅዱሳን ላይ ጊዜ በሰጣቸው ጊዜ ሁሉ በመጠቀም ማኅበሩን ለማሳጣትና ለማጥላላት የሚጠቀሙባቸው ስልቶች በርካቶች ናቸው፡፡

ከብዙ በጥቂቱ ለመጥቀስ ያህል «ማኅበረ ቅዱሳን ሲኖዶስ ከሰጠው ደንብና መመሪያ ውጪ እየሠራ የሚገኝ፣ ፖለቲካዊ ዓላማ ያለውና ገቢና ወጪው የማይታወቅ ማኅብረ» እንደሆነ አድርገው» ሚያናፍሱት አሉባልታ ከብዙ በጥቂቱ የሚጠቀስ ነው፡፡

ማኅበረ ቅዱሳን ግን ባለፉት 17 ዓመታት እነዚህ የውስጥና የውጪ የቤተክርስቲያን ጠላቶች በየጊዜው ማኅበሩ ላይ የሚያናፍሱትን ወሬ ችላ በማለት ከወሬ ሥራ ይቀድማል በማለት ከቅዱስ ሲኖዶስ የተቀበለውን ዓላማ በዓይን በሚታይ፣ በእጅ በሚዳሰስ መልኩ ሲሠራ ቆይቷል፡፡ ነገር ግን «ውሸት ሲደጋገም እውነት ይመስላል» እንዲሉ ማኅበረ ቅዱሳን ማን ነው? እንዴትስ ተመሠረተ? ዓላማውስ ምንድን ነው? ቅዱስ ሲኖዶስ የሰጠውን ሓላፊነት እንዴት እየተወጣ ነው? ለ17 ዓመታትስ ምን ሠራ? የሚሉትን ጥያቄዎት በስፋት ማቅረቡ አስፈላጊ መሆኑን ለምእመናን መግለጽ ግድ ብሎናል፡፡

ማኅበረ ቅዱሳን ማን ነው? እንዴትስ ተመሠረተ?

ማኅበረ ቅዱሳን ማን ነው? እንዴትስ ተመሠረተ የሚለውን ጥያቄ ከመመለሳችን በፊት አጽራረ ቤተክርስቲያንና ዓላማቸውን ለማስፈጸም የሚንቀሳቀሱት ተላላኪዎቻቸው የውስጥ ዐርበኞች ማኅበረ ቅዱሳንን በሰው ውስጥ የጥላቻ መንፈስ እንዲያድር ከሚጣጣሩበት መንገድ አንዱ ማኅበሩ የሚጠራበትን ስያሜውን በማዛባት ነው የሚጀምሩት፡፡ ከዚህ አንጻር ማኅበረ ቅዱሳን ሲባል ምን ማለት ነው? የሚለውን ነገር ማብራራት ያስፈልጋል፡፡ ስለዚህ ስያሜው ላይ አጭር ትንታኔ በመስጠት ወደ ማንነቱና አመሠራረቱ እንለፍ፡፡

የማኅበሩ ስያሜ

አንዳንድ ሰዎች ስያሜውም ግራ ያጋባቸዋል፡፡ ከላይ እንደጠቀስነው አባላቱ ለራሳቸው ያወጡት አስመስለው የሚነግሯቸው ሰዎች አሉና የዋሀኑ ግራ ቢጋቡ አያስደንቅም፡፡ ነገር ግን የማኅበሩ ስያሜ እኩያኑ ማኅበሩን ለማጥላላት ከሚጠቀሙት ፕሮ­ጋንዳ በእጅጉ የተለየ ነው፡፡ ማኅበረ ሚካኤል «የሚካኤሎች ስብስብ»፣ ማኅበረ ማርያምም «የማርያሞች ስብስብ» ካልሆነ /እንዳልሆነ/ ማኅበረ ቅዱሳንም «የቅዱሳን ሰብስብ» አይደለም፣ ሊሆን አይችልም፤ ወይም ማኅበረ ጊዮርጊስን የመሠረቱ ሰዎች ራሳቸውን «ጊዮርጊሶች»ነን እንደማይሉት፤ እንዳልሆኑትም፣ ማኅበረ ቅዱሳንም ቅዱሳን ነን የሚሉ ሰዎች ስብስብ አይደለም፡፡ ይልቁንም ማኅበረ ማካኤል የሊቀ መላእክት የቅዱስ ሚካኤል አማላጅነት፣ ተራዳኢነት የሚታሰብበት ማኅበር እንደሆነው ሁሉ ማኅበረ ቅዱሳንም የቤተክርስቲያኒቱን ትምህርተ ሃይማኖትና ሥርዐት ከመጠበቅና ከማስተማር በተጨማሪ በቤተ ክርስቲያኒቱ ትምህርተ ሃይማኖት መሠረት የቅዱሳን ጻድቃንና ሰማዕታት እንዲሁም የቅዱሳን መላእክት ክብ ራቸው፤ ገድላቸውና ትሩፋታቸው፣ አማላጅነታቸውና በረከታቸው፤ በሰፊው እንዲታወቅና ትውልዱም የዚህ ተጠቃሚ እንዲሆን ትምህርት የሚሰጡበት ማኅበር ነው፡፡ ምእመናን በነዚህ ቅዱሳን አማላጅነትና ረድኤት እየታገዙ ለመንግሥተ ሰማያት እንዲበቁ ማድረግም ቀዳሚ ተግባሩ ነው፡፡

ከዚህ የተነሣ የእነዚያ ብዙ ማኅበራት ኅብረት የሆነው ማኅበር የነቢያት፣ የሐዋርያት፣ ጻድቃን ሰማዕታትና የቅዱሳን መላእከት ሁሉ መታሰቢያ ይሆን ዘንድ ማኅበረ ቅዱሳን ተባለ፡፡

ማኅበረ ቅዱሳን እንዴትስ ተመሠረተ?

ዘመኑ የኮምዩኒዝም ርዕዮተ ዓለምና አስተሳሰብ የሰፈነበት፤ ስመ እግዚአብሔርን መጥራት አስቸጋሪ የሆነበትና ወደ ቤተ እግዚአብሔር መሔድ እንደ ኋላቀርነት የሚቆጠርበት ዘመን ነበር 1977 ዓ.ም፡፡

በተለይም በየከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ /ዩኒቨርሲቲዎችና ኮሌጆች/ በሚገኙ ተማሪዎች ዘንድ ቃለ እግዚአብሔርን በግልጽ መነጋገርም ሆነ መሰማት የማይታሰብበት ወቅት ነው፡፡

ቀደም ባሉት ጊዜያት በተለይም በንጉሠ ነገሥት ዐፄ ኃይለሥላሴ ዘመነ መንግሥት በዩኒቨርሲቲና ኮሌጆች እንዲያስተምሩ ከምዕራባውያኑ ሀገሮች መጥተው የነበሩ ሚሲዮናውያን የኑፋቄ ትምህርታቸውን ያሠራጩ የነበረውም በእነዚሁ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ነው፡፡

በዚህ ሁኔታ ትውልዱ በየአቅጣጫው በሚሲዮናውያኑ የኑፋቄ ትምህርት እንዲሁም በኮምዩኒዝም ርዕተ ዓለምና አስተሳሰብ እየተነጠቀ ከኦርቶዶከሳዊት ተዋሕዶ እምነት የኮበለለበት ከቤተክርስቲያን የራቀበት ዘመን ነበር፡፡

በዚህ ጊዜ ነው፤ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ስድስት ኪሎ ዋናው ግቢ ከፍተኛ ትምህርታቸውን ይከታተሉ የነበሩ አምስ

ምንጭ ድምጻችን ይሰማ ዘኦርቶዶክስ

Monday, October 28, 2013

ሠላይና ተሠላይ፤ ወዳጅና ጠላት

አሜሪካዊ እንደራሴና የሥለላ ጉዳይ አዋቂ ፔተ ሆክስትራን የሚያስደንቀዉ ግን የአሜሪካ ሰላዮች የጀርመንዋ መራሒተ-መንግሥትን ስልክን መጥለፋቸዉ አይደለም።የነፍሬድሪሽ ቁጣና ብስጭት እንጂ።ሆክስትራ እንደሚሉት ካስደነቀ-የሚያስደንቀዉ የጀርመን መሪ ሥልክ መጠለፉን ፍሬድሪሽ የሚመሩት የጀርመን የስለላ ድርጅት አለማወቁ ነዉ።
ARCHIV - US-Präsident Barack Obama und Bundeskanzlerin Angela Merkel unterhalten sich am 18.06.2012 in Los Cabos, Mexiko, beim Familienfoto. Merkel setzt bei der Aufklärung der millionenfachen Datensammlung des Geheimdienstes NSA nun auf eine Reise von Vertretern der Bundesregierung und deutscher Geheimdienste in der nächsten Woche nach Washington. Foto: Peer Grimm dpa (zu dpa Merkel verspricht größtmögliche Offenheit bei US-Ausspähaffäre vom 05.07.2013) +++(c) dpa - Bildfunk+++
ወዳጁ ናቸዉ
ለካሳትሮ፥ ለብሬዥነቭ፥ ለማኦ፥ ለ ደጎል፥ ለንጎ በርግጥ አዲስ አልነበረም።አይደለምም።የኤንርኮ ፔና ኔቶ ኢሜል መጠለፍ- ጉድ አሰኝቶ ነበር።የዲልማ ሮሴፍ-ኢሜል መጠለፍ-አስደንቆ ነበር።የሜርክል ሥልክ መጠለፍስ? ጉዱን ጉድ ዘለቀዉ-እንበል ይሆን።የስላላዉ ቅሌት መነሻ፥ዳራዉ ማጣቃሻ፥ የፖለቲካዉ እድምታዉ መድረሻችን ነዉ-ላፍታ አብራችሁኝ ቆዩ።


ሚዚያ ሃያ-አንድ 1943 (ዘመኑ በሙሉ እንደ ጎርጎሮሳዉያኑ አቆጣጠር ነዉ።) ፈረንሳይን ከናዚ ጀርመኖች አገዛዝ ነፃ ለማዉጣት የሚዋጋዉ ጦር አዛዥ ጄኔራል ሻርል ደጎል የነፃዋ ፈረንሳይ ባሕር ሐይል ጦርን ለመጎብኘት ከተጠጉባት ብሪታንያ በብሪታንያ አዉሮፕላን ተሳፈሩ።ቆፍጣናዉ፥ ቁጡዉ፥ እልሐኛዉ ረጅሙ ጄኔራል ከትንሿ አዉሮፕላን እንደተሳፈሩ አብራሪዉ (ፓይለቱ) አዉሮፕላንኗን እንደማስነሳት ትንሽ አንገጫገጨና ወዲዚያዉ አቆማት።ጉዞዉ ተዘረዘ።

አዉሮፕላንኗ ስትፈተሽ የሞተሯ አካል በአሲድ መበላሸቱ ታወቀ።አሲዱን አዉሮፕላንዋ አካል ላይ የረጨዉ ወገን ማንነት-እስካሁን ሚስጥር ነዉ።ጄኔራሉ ግን ያኔዉኑ «የብሪታንያ ሰላዮች ሻጥር» ለማለት አላመነቱም።የአዉሮጳ እብሪተኞች የለኮሱት ጦርነት ዓለምን በሚያነድበት በዚያ ዘመን ወዳጅን ከጠላት መለየቱ-ከባድ ነበር።በዚሕም ሰበብ ደ ጎል እንደጠረጠሩት ብሪታንያዎች አድርገዉት ከነበር-ብዙዎችን ብዙም አላስደነቀም ነበር።
ARCHIV - US-Präsident Barack Obama (r) wischt sich am 19.06.2013 den Schweiß von der Stirn neben Kanzlerin Angela Merkel auf einem Podium vor dem Brandenburger Tor am Pariser Platz in Berlin. Foto: Marcus Brandt/dpa (zu dpa Obama war angeblich in NSA-Abhörattacken gegen Merkel eingeweiht vom 27.10.2013) +++(c) dpa - Bildfunk+++ተሠላይና አሰላይ


ከብዙ አመታት በሕዋላ የደጎልን ቤተ-መንግሥት የተረኩቡት ፕሬዝዳት ኒኮላ ሳርኮዚ ከጀርመንዋ መራሒተ-መንግሥት ከወይዘሮ አንጌላ ሜርክል ጋር የነበራቸዉ ግንኙነት ከመሪዎች-ወዳጅነትም ጠንከር፥ ጠለቅ ያለ-ነበር ይባላል።ሳርኮዚ ከሜርክል ጋር ሥላላቸዉ ግንኙነት ሥለሚያደርጉት ዉይይት ሲጠየቁ፥«ሁሌ እንገናኛለን፥ በስልክ፥ እንነጋገር፥ ኤስ ኤም ኤስ እንለዋወጣለንም» እያሉ የግንኙነት ዉይይታቸዉ ደረጃ ዘርዝረዉ ነበር።

የሜርክል መልዕክት ከሳርኮዚ አይን-ጆሮ በሚደርስበት ፍጥነት ከአሜሪካ ሰላዮች ኮምፒዉተር ላይ ይዘረገፍ ነበር።ይሕን በርግጥ ሳርኮዚም፥ ሜርክልም ከኛ እኩል ያወቁት ሰሞኑን ነዉ።NSA በሚል ምሕፃረ-ቃል የሚጠራዉ የአሜሪካ ብሔራዊ የሥለላ ድርጅት ባልደረባ የነበሩት ቶማስ ድራክ እንደሚሉት ሜርክልን መሠለል ዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲን መጣስ ነዉ።

«ይሕ ዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲን ክፉኛ መጣስ ነዉ።ይሕ ለመራሒተ-መንግሥት ሜርክል የግል ጉዳይ ነዉ።የግላቸዉ ተንቀሳቃሽ ሥልክ ነዉ።(ያን መጥለፍ) ለምን አስፈለገ።ከእዉነኛ ጠላትሕ ጋር በምታደርገዉ ዉጊያ የቅርብ ተባባሪሕን?»
ILLUSTRATION - Ein iPhone, auf dem der fiktive Name Angela Merkel zu sehen ist, liegt am 25.10.2013 in München (Bayern) auf einem Logo der NSA (National Security Agency). Nach Hinweisen auf eine Überwachung des Handys von Bundeskanzlerin Merkel (CDU) durch US-Geheimdienste haben Politiker aller Parteien umgehende Aufklärung gefordert. Foto: Sven Hoppe/dpa
ዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲ፥ ዓለም አቀፍ ሕግ በቀዝቃዛዉ ጦርነት ወቅት ነበር።ዛሬም አለ።አንዴም ግን ተከብሮ አያዉቅም።ሕግ፥ ደንብ፥ ሥምምነቱን የሚጥሰዉ ደግሞ ሕግ-ደንቡን ካወጣዉ፥ አስከብረዋለሁ ከሚለዉ ሐያል ዓለም ሌላ ማንም አይደለም።

በቀዝቃዉ ጦርነት ወቅት ልክ እንደ ዓለም አቀፉ ሕግ ደንብ ሁሉ የሞስኮ፥ ቤጂንግ ተባባሪዎች፥ የለንደን-ዋሽግተን፥የቦን ፓሪስ ተሻራኪዎች ጎራ ለይተዉ አንዱ የሌላዉን ሚስጥር ማጭለጉ የፖለቲካዉ ፈሊጥ፥ የስለላዉ ወግ ነበር።

የሐገር መሪዎችን እንቅስቃሴ መከታተል አይደለም መግደል ማስገደልም የፖለቲካ መርሕን የማጠናከር፥ ርዕዮተ-ዓለምን የማዳን-ማስፋፋት ሥልት አካል ነበር።የአሜሪካዉ ማዕከላዊ የሥለላ ድርጅት CIA ሹም ኮሎኔል ጄ ሲ ኪንግ የኩባዉን ኮሚንስታዊ መሪ ፊደል ካስትሮ-ከማስገደል ሌላ ሌላ አመራጭ እንደለሌ የጠቆሙት በ1959 ነበር።

ያኔ ዓለም አቀፍ ማሕበር ዲፕሎማሲ፥ ሕግም ነበር።ዲፕሎማሲ ሕግ፥ ደንቡ የሚረቀቅ፥ የሚወሰን የሚበየነዉ ደግሞ ከኒዮርክ ነበር፥ ከዩናይትድ ስቴትስ ኦፍ አሜሪካ።የአሜሪካዊ ማዕከላዊ የሥለላ ድርጅት CIA ካስትሮን ለማስገደል ስድስት መቶ ሰላሳ-ስምንት ጊዜ ያደረገዉ ወይም አድርጓል የተባለዉ ሙከራ የብዙ መፅሐፍት፥ የዝነኛ ፊልም ርዕሥም ሆኗል።

አያቱላሆች የቴሕራንን ቤተ-መንግሥት ከተቆጣጠሩበት ከ1979 ጀምሮ ኢራን የእስራኤልም፥ የአሜሪካኖችም አሜሪካኖችን የሚመሩት የምዕራቡ ዓለምም ቀንደኛ ጠላት ናት።በሕዝብ የተመረጡት የኢራን ጠቅላይ ሚንስትር መሐመድ ሞስዳቅሕን በ1953 ከስልጣን ያስወገደዉ ማን ነበር? ፓትሪስ ሉምባ እንዴት-እና ማን ገደላቸዉ።ራፋኤል ሊኒዳስ ትሩሔሎስ፥ ንጎ ዲንሕ ዲየምንስ?
US-Bürger demonstrieren am 24.10.2013 nahe dem Kapitol in Washington DC gegen die Überwachung durch Geheimdienste wie die NSA. (Foto: Monika Griebeler / DW) - eingestellt von Andreas Grigoተቃዉሞ


ጥያቄዉ-ጥያቄ ይወልዳል እንጂ ማብቂያ የለዉም።ዓለምን የሚመራዉ ግን ዓለም አቀፉ ሕግ ዲፕሎማሲ ሳይሆን የሐያላን ፍላጎትና ፍቃድ መሆኑ ሐቅ ነዉ።የሐያላኑን ፍላጎት ለማስከበር ደግሞ በግልፅ የሚታወቀዉ ሐያላኑ ወዳጅ ከሚሉት ጋር መተባበር መሻረክ መወዳጀታቸዉ ነበር።እስከ 2007 ድረስ በዩናይትድ ስቴትስ ምክር ቤት የስለላ ጉዳይ ኮሚቴ ሊቀመንበር የነበሩት ፔተ ሆክስትራ እንደሚሉት ግን በስለላዉ ዓለም ከወዳጅም-መሐል ተጠርጣሪ ወዳጅ አለ።

«ይሕ ሊሆን የሚችል ይመስለኛል።በስለላዉ ዓለም ፈረንሳዮች፥ ጀርመኖች፥ እስራኤሎች አሜሪካኖች ሁላችንም ጥሩ ወዳጆች ነን።ግን አንዳችን ሌላችንን የምንሠልልበት ጊዜ ሊኖርም ይችላል-የሚል መግባባት ያለ ይመስለኛል።ይሕ (በሰላዮች ዘንድ) በጣም በጣም የታወቀ ነዉ።»

ኮሚንስቶች የሐቫና፥ የሳንዲያጎ፥ የማናጉዋ የሌሎችንም የደቡብ አሜሪካ ሐገራት አብያተ-መንግሥታትን ሲቆጣጠሩ ወይም ለመቆጣጠር ሲያሰጉ የዩናይትድ ስቴትስዋ የቅርብ ጎረቤት፥ ታማኝ፥ ታዛዥነቷን አጓድላ አታዉቅም።ሜክሲኮ።

ከቀዝቃዛዉ ጦርነት በሕዋላ እነ-ሑጎ ሻቬዝ አሜሪካኖችን የሚቃወም ግንባር ለመፍጠር ሲፍጨረጨሩም ያቺ-የአሜሪካ የቅርብ ጎረቤት በታማኝ ታዛዥነቷ እንደፀናች ነበር።ነዉም።ኤንሪክ ፔና ኒቶ ለፕሬዝዳትነት ሲወዳደሩ-ሲመረጡም እንደ ብዙ ቀዳሚዎቻቸዉ ሁሉ ለሐያል፥ ሐብታም፥ ታላቅ ጎረቤታቸዉ ታማኝ ታዥነታቸዉን እንደጠበቁ ነዉ።

በእጩነት ከተመዘገቡ ጀምሮ በምርጫዉ ካሸነፉ-ለሚንስትርነት የሚሾሙ የሚሽሩትን ፖለቲከኛ ስብዕና ማንነት፥ የሚዘረዝር፥ የምርጫ ዘመቻቸዉን ሥልት የሚያትት መልዕክት ለወዳጅ ተከታዮቻቸዉ ኢሜይል ይፅፋሉ። የNSA ሰላዮች ዋሽግተን ቁጭ ብለዉ የሜክሲኮዉን ፕሬዝዳት ኢሜይል ከፕሬዝዳንቱ ደጋፊ፥ተከታዮች እኩል ያነቡ ነበር።የብራዚሏ ፕሬዝዳት የወይዘሮ ዲልማ ሮሴፍ ኢሜዬልም-እንደዚያዉ ነዉ።

አሜሪካዊዉ ሠላይ ኤድዋርድ ስኖደን ሐገር መስሪያ ቤቱን ክዶ ከኮበለለ ወዲሕ የማይሰማ ጉድ የለም።አንዳድ ዘገቦች እንደሚጠቁሙት የሶቬት ሕብረት ኮሚንስቶች በስታሊን ዘመን የሶቬት ሕብረት ሕዝብ ከሚሠልሉት በላይ የአሜሪካ መንግሥት አሜሪካዉያንን ይሰልላል።ለአሜሪካ ሕዝብ ያልራራ ሥርዓት የፈረንሳይ ኩባንያዮችን፥ የስጳኝ ፖለቲከኞችን፥ የዓለምን ሕዝብ የሜክሲኮ፥ የብራዚል፥ የሌሎች ከሰላሳ በላይ መሪዎችን ቢሰልል-በርግጥ ሊያስደንቅ አይገባም።

ያምሆኖ የጀርመንዋ መራሒተ-መንግሥት የሥልክ መልዕክት መጠለፉን ከአዉሮጳ ሕብረት አባል ሐገራት እስከ ሩሲያ መሪዎች ተቃዉመዋል።የጀርመን ፖለቲከኞች የሜርክል ደጋፊም ሆኑ ተቃዋሚዎችም እኩል አዉግዘዉታል።

«እንደሚመስለኝ ይሕ በጀርመን-አሜሪካኖችን ግንኙነት ያለዉን መተማመን ክፉኛ የሚጎዳ ነዉ።መተማመኑ ዳግም ሊገነባ የሚችለዉ እዉነታዉ በግልፅ ወጥቶ ማየን ከቻልን በኋላ ነዉ።

ይላሉ፥-የዋነኛዉ ተቃዋሚ ፓርቲ የSPD የምክር ቤት እንደራሴዎች አስተባባሪ ቶማስ ኦፐርማን ።ሥለ ጀርመን እና ጀርመንን የሚመለከቱ መረጃዎችን የመሰብሰብ መከታተሉ ሐላፊነት የጀርመን የሥለላ ድርጅት ነዉ።ቡንደስ ናሕሪሽተን ዲንስት።BND በጀርመንኛ ምሕፃሩ። የስለላዉን ድርጅት በበላይነት የሚያስተዳድርና የሚመራዉ ደግሞ የጀርመን ፌደራዊ የሐገር ዉስጥ ጉዳይ ሚንስቴር ነዉ።

የሐገር ዉስጥ ጉዳይ ሚንስትር ሐንስ ፔተር ፍሬድሪሽ ግን የመሪያቸዉን መሰለል እንደማንኛዉም ሰዉ ከመገናኛ ዘዴዎች የሰሙ ያክል ነዉ-የተቆጡት።

«ከአሜሪካኖች ጋር በዚሕ ሁኔታ አንሰራም።መተማመኑ ተበላሽቷል።እና እንደሚመስለኝ የተበላሸዉን መተማመን ለመጠገን ሁነኛ እርምጃ መወሰድ አለበት።»

አሜሪካዊ እንደራሴና የሥለላ ጉዳይ አዋቂ ፔተ ሆክስትራን የሚያስደንቀዉ ግን የአሜሪካ ሰላዮች የጀርመንዋ መራሒተ-መንግሥትን ስልክን መጥለፋቸዉ አይደለም።የነፍሬድሪሽ ቁጣና ብስጭት እንጂ።ሆክስትራ እንደሚሉት ካስደነቀ-የሚያስደንቀዉ የጀርመን መሪ ሥልክ መጠለፉን ፍሬድሪሽ የሚመሩት የጀርመን የስለላ ድርጅት አለማወቁ ነዉ።

«የዋሕነት ይመስለኛል።የጀርመን መንግሥት (ባለሥልጣናት) በወዳጆቻቸዉ ሊሰለሉ እንደሚችሉ ማወቅ ነበረባቸዉ።ነገሩ ከተፈፀመ አስደናቂዉ ነገር የሚመስለኝ፥ (ሥለላዉን) ለማስቆም የጀርመን የስለላ ማሕበረሰብ አስፈላጊዉ አፀፋ-እርምጃ አለመዉሰዱ ነዉ።»
Titel: Demonstration #stopwatchingus gegen NSA und Überwachung in Washington, DC, USA
Schlagworte: NSA, Überwachung, Demonstration, stopwatchingus
Wer hat das Bild gemacht?: Monika Griebeler
Wann wurde das Bild gemacht?: 26.10.2013
Wo wurde das Bild aufgenommen?: Washington, DC, USA
ተቃዉሞ
የጀርመንዋ መራሒተ-መንግሥት ስልክ መጠለፉ-መሰላላቸዉም እርግጥ ነዉ።ሜርክል መሰለላቸዉን ፕሬዝዳት ባራክ ኦቦማ ያዉቃሉ-አያዉቁም እያነጋገረ ነዉ።ካወቁ ከመቼ ጀምሮ የሚለዉም ያጠያይቃል። እራሳቸዉ ሜርክል እና የፈረንሳዩ ፕሬዝዳት ፍራንሷ ኦሎንድ የአዉሮጳ ሕብረት ወክለዉ ለኦባማ አቤቱታ ያቀርባሉ። ወደ አንድ ሺሕ የተገመቱ አሜሪካኖች በመንግሥታቸዉ መሠለላቸዉን በአደባባይ ሠልፍ አዉግዘዋል።አቤቱታ፥ ተቃዉሞ፥ ዉግዘት፥ ሰልፉ ምናልባት ይቀጥል ይሆናል፥ መሳለል-መጠላለፉ ያስቆመዋል ባይ ግን የለም።ምክንያት፥-ድሮ እንዲያ ነበር፥ ዛሬ እንዲያ ነዉ።ነገም።በዚሕ ዝግጅት ላይ ያላችሁን አስተያየት ላኩል። ማሕደረ ዜና ቢቃኘዉ ጥሩ ነዉ ብላችሁ የምትገምቱትን ወቅታዊ፥ ብሔራዊ፥ዓለም አቀፋዊ ጉዳይ በተለመደዉ አድራሻችን ጠቁሙን።ለዛሬዉ ነጋሽ መሐመድ ነኝ ቸር ያሰመን።
ነጋሽ መሐመድ
አርያም ተክሌ

AUDIOS AND VIDEOS ON THE TOPIC

  • ቀን 28.10.2013  www.dw.de

አደባባዩ ምን ያህል ይርቃል?

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ
እነሆ ይቺ ሀገር ኢትዮጵያ ናትና የመብት (የለውጥ) ጥያቄዎች፣ እንደ አህጉር ተጋሪዎቿ ሁሉ መልስ
የሚያገኙት ከአደባባይ ጩኸት ብቻ ይሆን ዘንድ ባህል ሆኖአል፡፡ ትውልድ ተሻጋሪ ታሪኳም የሚነግርህ
በየወቅቱ ከተፈራረቁ ገዥዎቿ አንዳቸውም እንኳ ለህዝብ ፍላጎትና ውሳኔ ተገዝተው አለማወቃቸውን ነው፤
ጠመንጃ አሊያም ተፈጥሮ ወደ ግብአተ መሬት ካልሸኛቸው በቀር፡፡ የሩቁን (የጨለማውን ዘመን) ትተን፣
የቅርቡን እንኳን ብንመለከት በወጡበት መንገድ፣ ቁልቁል ተምዘግዝገው መውደቃቸውን መረዳቱ
አይቸግርም፡፡ አዛውንቱ አፄ ኃይለስላሴ፣ ‹‹ቆራጡ›› ኮሎኔል መንግስቱ ኃይለማሪያም እና ‹‹ታጋዩ›› አቶ መለስ
ዜናዊ እጅ የሰጡት ለህዝብ ፍላጎት ሳይሆን ለጠመንጃና ለተፈጥሮአዊ ኃይል ነው፡፡ የሶስቱም የአመፃ ‹‹የዳቦ
ስም›› ደግሞ ተመሳሳይ ነበር፡- ‹‹ለሀገርና ህዝብ ጥቅም››፡፡
ንጉሰ ነገስቱ ልጅ እያሱን ያስወገዱበት ምክንያት ‹‹ሀገርን ከሚያጠፉ ጋር በማበሩና ህዝብን ከማስተዳደር ይልቅ፣ ለግላዊ ምቾት ጊዜውን
በዋል ፈሰስ በማዋሉ ነው›› የሚል ሰበብ እንደነበረ ይታወሳል፡፡ በግልባጩ እርሳቸውም ከግማሽ ክፍለ ዘመን በኋላ አደባባይ ባናወጠ
ንቅናቄ ተገፍተው፣ ገደል አፋፍ በቆሙባት በዛች ዕለት፣ የሠራዊቱን መለዮ ባጠለቀ አንጋች የተነበበላቸው የክስ ደብዳቤ፡- ‹‹ሀገርን
ለቆሞ-ቀር፣ ሀብትን ለቤተሰብና ለግለሰቦች ጥቅም መመዝበር፣ ህዝብን ለከፋ ጭቆናና ሰቆቃን ላዘነበ ረሀብ መዳረግ…›› የሚል እንደነበረ
ስናስታውስ ‹ታሪክ ራሱን ደገመ› ያሰኛል፡፡ በዚህ መልኩ ‹‹በደልና ግፍ ከምሽግ አስወጣን›› ባሉ ወታደራዊ መኮንኖች የተመሰረተው
የደርግ መንግስትም አስራ ሰባት ዓመት ሙሉ እንዳሻው ሲገድል፣ ሲፈልጥ፣ ሲሸልል… ቆይቶ ‹‹ብሶት ከትምህርት ገበታ አፈናቀልን›› ባሉ
በረኸኞች ፍፃሜው ይሆን ዘንድ ግድ ሆነበት፡፡ ታሪክም የሚነግረህ ይህንኑ ነው፤ ሌላ የለም፡፡ ያገዛዝ ጭቆናና መከራ ያስመረረው
አደባባዩን በኃይል ሲነጥቅ-ሲነጥቅ ዛሬ ላይ መድረሱን፡፡ በርግጥ ይህ እርግማን አይደለም፤ ለጨቋኞች በልክ የተሰፋ ፍትሀዊ ፍርድ
የሚተላለፍበት አማራጭ መንገድ እንጂ፡፡
የሆነው ሆኖ ዛሬም ቢሆን ትውልድ እንጂ ታሪክ አልተቀየረምና፣ የለውጥ መንገዶች በሙሉ ሄደው ሄደው ወደ አደባባይ የሚገፉ
ሆነዋል፡፡ በኢትዮጵያ ምድር ‹የነፃነት በር በብላሽ አይከፈትም› ያለው ማን ነበር? ...ርግጥ ነው መለስ ዜናዊም በርሃ ሳለ ‹‹ምኹሕዃሕ
ዘይፍለዮ ማዕፆ›› (ማንኳኳት ያልተለየው በር) በተሰኘ ታንክ ተደግፎ በፃፈው መፅሀፉ ላይ የደርጉን ፋሺስትነት ከመተንተኑ
በተጨማሪም ከጓደኞቹ ጋር ተስፋ ሳይቆርጥ ባደረገው ትግል ነፃነቱን ተቀዳጅቷል፡፡ ይሁንና በለስ ቀንቶት በትረ-ስልጣን ከጨበጠ
በኋላ ግን፣ የአስተዳደር ዘይቤውን የወረሰው ታግሎ ከጣለው ስርዓት ዶሴ እንደነበር ለመረዳት ብዙ አላስጠበቀም፤ ቀድሞ
የተተገበረውን አሻሽሎ፣ በከፋ መልኩ ደጋግሞ ተግብሮታል፡፡ የመፅሀፉ ዋና ገፅ-ባህሪ ‹‹እነይ ስላስ›› በእንባ እንደታጠቡት፣ በድህነት
እንደጎበጡት ሁሉ ዛሬም የኢትዮጵያ እናቶች በደህነት አጥንታቸው ገጥጧል፤ ለእስርና ለስደት በተዳረጉት ልጆቻቸው ጉልበታቸውን
ታቅፈው በሀዘን እንዲወዛወዙ ተፈርዶባቸዋል፤ ሥራ-አጥ ጎረምሳ ልጆቻቸውን ለመቀለብ ላይ-ታች ከመማሰን አልተገላገሉም፤
‹‹ለግርድና›› ወደ አረብ ሀገር የተሰደዱትን ሴት ልጆቻቸውን እያሰቡ በስጋት እየተናጡ ነው… እናም በኢህአዴግና እነርሱ ‹‹ፋሺስት››
በሚሉት በደርጉ ስርዓት መካከል የታየው የአስተዳደር አይነት የጊዜና የሰዎች ልዩነት ብቻ እስኪመስል ድረስ የአንድ ሳንቲም ግልባጭ
መምሰሉ ‹‹ነፃ አውጪ››ነቱን ምፀት አድርጎታል፡፡ በበረሃ የተደረሰው መዝገበ ቃላትም ‹‹ህዝብ በሁለት ይከፈላል›› ይላል-በ‹‹ደጋፊ›› እና
‹‹ተቃዋሚ›› ጎራ፡፡ ተቃዋሚ የተባለውንም የምድር እርግማን ሁሉ ይፈፀምበት ዘንድ ያዝዛል፤ ጭቆና፣ ግፍ፣ ጭካኔን… በህዝብ
ደህንነትና ሰላም ስም ማንበር፤ በህገ-መንግስት ትከሻ ማንጠልጠል፤ ህልምን፣ ምርጫን፣ ህዝበ-ውሳኔን… በክንደ-መሳሪያ መተርጎም…
በዚህ የተነሳ የለውጥ ሃዋርያት ወደ አደባባዩ ይጎርፉ ዘንድ ወቅቱ ግድ ብሏል፤ በርግጥም ስርዓቱ በደልን ዘርተው፣ በደልን በሚያፀድቁ፤
ጭቆናን ከዳር ዳር በሚያዳርሱ፤ በፍትሕ በሚዘባበቱ፤ ከመልካም አስተዳደር በእጅጉ በራቁ፤ በሀገር ሀብት ራሳቸውንና ዘመዶቻቸውን
ባበለፀጉ፤ ስቃይንና መከራን የአገዛዝ ስልት ባደረጉ፤ በአማላይ ዕቅድና ፖሊሲ በሚሸነግሉ፤ የምርጫን ውጤት እንደፍቃዳቸው
ማገለባበጥ በተካኑ… የተዋቀረ በመሆኑ እነሆ ሕዝቡ ለድፍን ሃያ ሁለት ዓመታት አሳር መከራውን እንዲቆጥር ተፈርዶበታል፡፡
መቼስ ከሁለት አስርተ ዓመታት በላይ በሥልጣን ስለቆየው የኢህአዴግ አስተዳደር ክስረትና ሽንፈት በእንዲህ አይነቱ የመፅሄት ፅሁፍ
ተንትኖ ለመጨረስ ቀርቶ፣ ጠቅሶ እንኳን ማለፍ የሚቻል አይመስለኝም፡፡ ምክንያቱም የድርጅቱ ገመና በዜጎች መሀል አለመተማመን
ከመፍጠር አንስቶ በሀገር ጥቅም መደራደር፣ ህግን የፖለቲካ መጠቀሚያ ማድረግ፣ ሰላዮችን አለቅጥ በሕዝብ መሀል መሰግሰግ፣
የሠብዓዊም ሆነ የፖለቲካ መብቶችን መጨፍለቅ፣ የሀገር ሀብትን መዝረፍና ማዘረፍ፣ በሥልጣን መባለግ፣ የልማት አጀንዳን
ለፕሮፓጋንዳ መሳሪያነት ብቻ መጠቀም፣ በዚህም የሥራ-እጥ ቁጥርን ማናር፣ የኑሮ ውድነትን ማሻቀብ፣ ዜጎችን ማፈናቀል፣ በሠላማዊ
ህዝብ ላይ የታጠቀ ኃይል ማዝመት፣ ፍርሃትን ማንገስ… እያለ ይቀጥላልና ስንቱን ዘርዝሮ መጨረስ ይቻላል? ይህ ተቆጥሮ የማያልቅ ሃያ
ሁለት ዓመታትን ያስቆጠረ አሳረ-መከራም ነው ብዙሃኑን ‹አደባባዩ ምን ያህል ይርቃል?› የሚል ጥያቄ እንዲያንሰላሰል ገፊ ምክንያት
የሆነው፡፡ ተቀራራቢው መልስም ከሚከተሉት አንዱ ሊሆን ይችላል፡- የሞትን ያህል፣ በእስር ቤት የመበስበስን ያህል፣ በስደት
የመንከራተትን ያህል ወይም ለተጨማሪ ሃያ፣ ሰላሳ፣ አርባ… የጭቆናን ዓመታት ያህል?
ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ካገዛዙ ባህሪይ አንፃር ከላይ የተዘረዘሩት በሙሉ ለጥያቄው መልስ ሊሆኑ እንደሚችሉ አንድ እንኳ የሚጠራጠር ያለ አይመስለኝም፡፡
ምክንያቱም የስርዓቱ ስር የሰደደ ሴራ ‹ግደል› ሲባል የሚገድል፣ ‹ተኩስ› ሲባል የሚተኩስ፣ ‹አፍን› ሲባል ‹ለምን?› ብሎ የማይጠይቅ
የታጠቀ ኃይልን ማሰልጠኑ እና በሀሰት ለመክሰስ የማያመነታ ህሊና ቢስ ዓቃቢ ህግን፣ በሀሰት ለመፍረድ የማያቅማማ ዳኛን፣
በአጠቃላይ ሰጥ-ለጥ ብሎ የሚገዛ ሎሌ ትውልድ… ለመፍጠር አቅዶ መስራቱ ነውና፡፡
በአናቱም የምሁራኖቻችን አድርባይነትም ሆነ ዝምታ ለከፋፋይ አገዛዙ ጉልበት ሆኖታል፡፡ አብዛኛዎቹም ነገን አጥብቀው የሚፈሩ፣
ከሀገርና ህዝብ ጥቅም በላይ የግል ምቾታቸው የሚያስጨንቃቸው መሆንን መርጠዋል፡፡ የተቀሩት (ገቱ ያላቸው) ጥቂት ታላላቆችም
ቢሆኑ ኃላፊነታቸውን አልተወጡም፤ ወይም ሞክረው አልተሳካላቸውምና ለዛሬቷ ኢትዮጵያ ‹‹የቁልቁለት መንገድ›› የድርሻቸውን
ማንሳታቸው አከራካሪ አይሆንም፡፡
ሌላው ትልቁ እንቅፋት ደግሞ የአገዛዙ ቂመኝነት ከዕለት ዕለት፣ ከዓመት ዓመት እየከፋ መምጣቱ ነው፡፡ ሌላው ቀርቶ በአስከፊዎቹ
የሀገሬ እስር ቤቶች የከረቸመባቸውን እነዛን (ራሳቸውን መከላከል የማይችሉትን) የህሊና እስረኞች ‹ማኪያቬላዊ በቀል› በተሰኘው
መፅሀፉ ምሪት ፍዳቸውን ከማስቆጠር አልተመለሰም፡፡ እስክንድር ነጋ፣ አንዱአለም አራጌ፣ በቀለ ገርባ፣ ርዕዮት አለሙ፣ ውብሸት ታዬ…
የድርጊቱ ጥሩ ማሳያ ናቸው፡፡ ርግጥ ነው መንግስት ሰዎቹን ያሰረው ለሕዝብ ጥቅም ሲል እንደሆነ ዛሬም ድረስ ለማሳመን እየለፈለፈ
ነው፤ ይሁንና እስካሁን ያልነገረን ማሰቃየቱ፣ ፍትህ መንፈጉና ጠያቂ መከልከሉ… ለማን ጥቅም ሲባል እንደሆነ ነው፤ ለሕዝብ ይሆን?
ከሁሉም በላይ ግራ የሚያጋባው ነገር ደግሞ የእስረኞቹ ጠባቂዎች ልበ-ደንዳናነት ነው፤ የእነርሱን ያህል የተጎሳቆሉ፣ የእነርሱን ያህል
የተገፉ፣ የእነርሱን ያህል የተበደሉ ታሳሪዎችን ለማንገላታትና ለማሰቃየት ያላቸው ሞራል የበዛ ነውና፡፡
መቼም በዚህ ዘመን የእኛዎቹን እስር ቤቶች ያህል አስከፊ የሰቆቃ ቦታዎች በየትኛውም የዓለም ክፍል ያሉ አይመስለኝም (ለካስ! እንዲህ
ዘመን የተጣላት፣ ታሪክ የተቃረናት ሀገር ዜጋ መሆን የከፋ ስቃይ ኖሯል!!) …ይህ ሁኔታም ይመስለኛል ከስርዓቱ አጋፋሪና አጫፋሪዎች
ይልቅ ጨካኙን በሽር አልአሳድን በሶሪያ ጎዳናዎች የሚፋለሙት ነፃነት ናፋቂዎች በሥጋ የተዛመዱህ ያህል እንድትቆረቆርላቸው
ያደረገው፤ ከጨቋኝ የሀገርህ ገዥዎችም ይልቅ፣ በየትኛውም ክፍለ ዓለም ያሉ ጭቁን ህዝቦችን ‹ወገኔ› እንድትል ያደረገው፤ ከእነርሱ
የመንፈስ አንድነትን፣ የነፍስ ትስስርን በፅኑ ስለምትጋራ ነው፡፡ አንተም ጭቁን ነህና የተጨቋኞች አበሳ ይቆጠቁጥሀል፤ አንተም
መብትህና ክብርህ ተገፏልና፣ ተመሳሳዩ ከተፈፀመባቸው ሕዝቦች ጎን መቆምህ ግድ ነው፡፡ …ከዚህ በተረፈ ‹እንመራሀለን› የሚሉህ
ወንድሞችህ፣ ልብህን በጩኸት ከማሸበር፣ ዘመንህን ካለፉትም በላይ የከፋ ከማድረግ፣ ለዓመታት ቀጥቀጠው ከመግዛት ያለፈ የፈየዱት
ቁም-ነገር የለምና ለእነርሱ ቀረቤታና ሀዘኔታ ከቶም ሊሰማህ አይችልም (በነገራችን ላይ አንዳንድ ለውጥ ናፋቂዎች ስርዓቱን ከመላው
የትግራይ ተወላጆች ጋር ደርበው መውቀሳቸውና መክሰሳቸው ስህተትና ለሀገር አንድነት ጠንቅ መሆኑን አምነው ካልተቀበሉ የትግሉን
ዕድሜ ከማራዘሙም በላይ ለከፋ ችግር መዳረጉ አይቀሬ ነው፡፡ በዚህ መልኩም ተሰልቶ የሚመጣ ውጤትም የኢህአዴግን ስህተት
በእጥፍ መመንዘር ነው የሚሆነው፡፡ እናም ምርጫው ሁለት ይመስለኛል፤ ይህ አይነቱን ሸውራራ /ጨለምተኛ/ አተያይ አስተካክሎ
ታላቂቷን ኢትዮጵያ በጋራ መገንባት፣ አሊያም የህወሓትን መንገድ በመከተል ለውጡን በዜሮ አባዝቶ ሀገርን እንደአንባሻ ዘጠኝ ቦታ
ለሚከፋፍል አደጋ ማጋለጥ)
የመነቃቃት መንፈስ…
ጥያቄው ይህ ነው፡- ህማማቱ ስንት ቀን ይፈጃል? የማራኪና ተማራኪ አስተዳደር ዕድሜው ምን ያህል ይረዝማል? ስለምንድር ነው
ባለስልጣናት አስፈራሪ፣ ቀለብ ሰፋሪ ህዝብ ደግሞ ተስፈራሪ የሆኑት? ማን ነውስ መብታቸውን የሚጠይቁ የሃይማኖት መሪዎችን-
አክራሪና አሸባሪ፣ ተቃዋሚዎችን-በሀገር ላይ የሚያሴሩ፣ ጋዜጠኞችን-የጠላት ሀገር ተላላኪ ያደረገው? በየትኛው ህግስ ነው ስርዓትን
መደገፍ-ሀገር ወዳድ፣ መቃወም-ይሁዲነት የሆነው? …ግና እመነኝ ውንጀላው በጉልበታም ገዥዎች ዘንድ የተለመደ የፖለቲካ ጨዋታ
ነው፡፡ በተቀረ ነፃነትን ያጣጣሙ ነባር ሀገራትን ትተህ፣ የቅርቦቹን እነቱኒዚያን ብትወስድ እንኳ፣ አደባባዩ ሽንፈት ያወጀባቸው
ገዥዎቻቸው ተመሳሳዩን ይፈፅሙ እንደነበር ድርሳናቶቻቸው ይነግሩሀል፡፡ ምንም እንኳ ዛሬ ታሪክ ቢሆኑም፡፡
ያንተም ጨቋኝ ገዥዎች ታሪክ የሚሆኑት፣ ይህ ሁሉ አሳረ-ፍዳ ከእነጦስ ጥንቡሳሱ ሊወገድ የሚችለው ዋጋን በሰማይ በሚከፍለው
‹‹ንሰሃ›› አይደለም፣ ጎዳናዎችን በሚያጥለቀልቅ ህዝባዊ ቁጣ እንጂ፡፡ እናም የአደባባዩን ርቀት ከጭቆናው ጋር እያለካኩ፣ የፍርሃት
ሰንሰለትን አየበጠሱ፣ በሁከተኛው ስርዓት ላይ የሚጮኹ የነፃነት ድምፆችን ማስነሳቱ አማራጭ አልባ መፍትሄ ነው፤ እነዛ ጎበዛዝቶች፣
በሚከፍሉት ዋጋ ታጋይ እንጂ ትግል እንደማይሞት እያስመሰከሩ፣ መንገዶቹን የሚያንቀጠቅጡ ፋኖዎች ከቁም እንቅልፍ የሚባንኑበትን
ዕለት ማሳጠር የግድ ይላል፡፡
በዚህም አለ በዚያ ይህ ኩነት ይለወጥ ዘንድ ስደት መፍትሄ አይሆንም፤ ማሳደዱን፣ ማስፈራራቱን፣ ማደህየቱን፣ ማሰር፣ መግደሉን…
ከቶም ቢሆን ሀገር ጥሎ በመሄድ ማሸነፍ አይቻልም፤ ምክንያቱም የስርዓቱም ፍላጎት ይኸው ነውና፤ የተቃወመውን፣ በስልጣን
አደገኛነት የጠረጠረውን ከሀገር በማባረር፣ ከአደባባዩ ይበልጥ ማራቅ፣ ከአይን መሰወር፣ በዚህም ለውጥ ያረገዘውን የቁጣ ቀን ማዘግየት፡፡ ለዚህም ነው ‹እኔ ምን አገባኝ›ም ሆነ ስደት መፍትሄ አይሆንም የምለው፡፡ አዎን! ሀገሪቱን የጥቂቶች ብቻ ለማድረግ
የተያዘውን ግብግብ ማጨናገፍ የምትችለው መሬት በሚያርድ ሠላማዊ ቁጣ ብቻ ነው፤ የሰብዓዊ መብት አፈናም ሆነ ሥራ እጥነትና
ድህነት የሚያሰድዳቸው ወንድም እህቶቻችን የባሕር ሲሳይ የሚሆኑበትን አሳዛኝ ዕጣ መለወጥ የምትችለው በአደባባይ ቁጣ ነው፤
የህሊና እስረኞችን ነፃነት ማወጅ የምትችለው እጅ ለእጅ ተያይዘህ የጎዳና ቁጣን በማሰማት ነው፤ ረሀብና ድህነትንም ማጥፋት
የምትችለው በቅድሚያ በሰንካላ ፖሊሲና ደካማ አስተዳደር በሚመራው ስርዓት ላይ መቆጣትና ማምረር ስትችል ነው፡፡ ይህ ሲሆን
ብቻ ነው ኢትዮጵያ የአንተም ሀገር የምትሆነው፡፡
 የጥሪው ድምፅ
‹‹ሰላም ይሉናል፣
ጥርሳቸውን እያፋጩ በጥል
ቤት እያፈረሱ በበቀል
ኑሮን እያደረጉ ገደል
ሰላም ይሉናል፣
እኛ እንግዛ፣ እናንተ ተገዙ
እኛ እንዘዝ፣ እናንተ ታዘዙ
እኛ እናስብ፣ እናንተ ደንዝዙ
ንገሯቸው እባካችሁ
ሰላም ነፃነት ነው ብላችሁ
ዝም አትበሉ
እሪ በሉ
ጠመንጃቸውን እስቲጥሉ፡፡›› (ፕ/ር መስፍን ወ/ማሪያም ‹‹ዛሬም እንጉርጉሮ›› የግጥም መድብል)
እነሆም የሀገሬ ጀግኖች ከአንቀላፉበት አዚም ይነቁ ዘንድ ጩኸቱ በርክቷል፤ የደውል ድምፁም አስተጋብቷል፤ አምነት የሚጣልበት
የአርነቱን ‹ሙሴ›ም፡-
‹‹ጥሩት አያ’ገሌን ያሳየን መንገዱን
መሪ ነው ያጣነው፣ ስናቋርጥ ዱሩን›› (አንዱአለም አባተ ‹‹የረዘመ ትንፋሽ›› የግጥም መድብል) የሚሉ ድምፆች እያፈላለጉት ነው፡፡
እውነት እውነት እልሀለሁም፡- ይህ ሲሆን ነው በነብያቶች አንደበት የተነገረው በኢትዮጵያ ‹‹ታህሪር›› ታሪክ የሚሰራበት፣ ጭቆና-ድባቅ
የሚመታበት፣ ያጎነበሰ አንገት-የሚቃናበት፣ የተሰበረ ልብ-የሚጠገንበት፣ የደከመ መንፈስ-የሚበረታበት፣ ነፃነት የሚዋጅበት፣
በምኩራቦቹ ፍትህ-የሚሰበክበት፣ ህግ-የሚከበርበት፣ አድሎአዊነት-የሚወገዝበት… ይሆናል፤ ደጀ ሰላሞቹም የሰብዓዊ መብት
የሚከበርባቸው፣ የመኖር ዋስትና የሚረጋገጥባቸው…፤ አውደ ምህረቶቹም ያለቀሱ የሚስቁበት፣ የአዘኑ የሚፅናኑበት… ይሆናል፡፡ ይህ
ነው ነብያቶቹ የተናገሩት የተስፋው ቀን፤ የተስፋው ምድር፡፡ … እነሆም በገዥዎች ላይ ሰቆቃንና ዋይታን ከሚያዘንበው የመጨረሻዎቹ
ቀናት በፊት እንዲህ ማለትን ወደድኩ…
 አንድ ምክር-ለጓዶች
ደጋግማችሁ የአደባባይ ተቃውሞን፣ ሕዝባዊ ንቅናቄን ለማውገዝ እንደ ምክንያት የምትጠቀሙበት ‹‹ሀገሪቱን በልማት ጎዳና አከነፍናት፣
እድገታችን ለተከታታይ ዓመታት ከሁለት ዲጂት በላይ ከሆነ ሰነበተ›› የሚለው ሀቲት፣ተራ ፕሮፓጋንዳ እንደሆነ የታወቀ ቢሆንም እስቲ
‹‹ይሁን›› ብለን ብንቀበለው እንኳ እንደምኞታችሁ የተቃውሞው ድምፆች ይዘጉ ዘንድ የግድ እንዲህ የሚሉትን ወሳኝ ጥያቄዎች መመለስ
ይኖርባችኋል፡- የፖለቲካ ነፃነት አለመኖሩስ? በስርዓቱና በአምሳሉ የተቀረፁ ተቋማት ተአማኒነት ማጣታቸውስ? ጎሳን እየነጠሉ ለፖለቲካ
ጥቅም ማዋሉስ? አዋጅና ፖሊሲ ከመፅደቃቸው በፊት ሀቀኛ ተቀናቃኞች፣ ገለልተኛ ምሁራን እና የሚመለከታቸው አካላት ሁሉ በድፍረት
እንዲተቹበት አለመደረጉስ? (‹ሰው በእንጀራ ብቻ ይኖራል!› የሚል እምነት አራማጅ የሆኑትን የኢቲቪ ሸንጋይ ‹‹ምሁራኖች››ን
እርሷቸውና ማለቴ ነው)፣ ሃሳብን በነፃነት ለመግለፅ የሚያበረታ መደላድል አለመኖሩስ? ማንም ሰው ባመነበት ሃሳብ መደራጀት
አለመቻሉስ? የህግ የበላይነት ከወረቀት አለመዝለሉስ? መከላከያ ሠራዊት፣ ፌዴራል ፖሊስና የደህንነት ተቋሙ ተጠሪነታቸው ከህገ-
መንግስቱ ይልቅ ለፓርቲ መሆኑስ? …እናም ‹ህዝብን ከፍ ከፍ አድርጎ ያከበረ መንግስት መንበሩ የፀና ይሆናል!›› እንዲል ጠቢቡ፣
የረዣዥም ተራሮቻችንን አናት ሳይቀር ለማንቀጥቀጥ በማስገምገም ላይ ያለው ይህ ብርቱ የቁጣ ድምፅ የሚረግበው፤ የፈረሱ ቅፅሮችን
በጋራ ለማነፅ በመሀከላችን መተማመን የሚሰፍነው፤ ‹ባቢሎናውያን›ነት ሰክኖ፣ እርስ በእርስ መደማመጥ የሚቻለው እነዚህ ከላይ
የተጠቀሱት የለውጥ ፈላጊው ወሳኝ ጥያቄዎች በአስቸኳይ ሁሉንም ወገን በሚያሳምን መልኩ መፍትሄ የተሰጣቸው እንደሆነ ብቻ ነው፡፡
ከዚህ ሌላ መፍትሄ የለም -ታሪክን በከፋ መልኩ ከመድገም በስተቀር፡፡
መልካም ዕድል!
ኢትዮሚድያ - Ethiomedia.com – October 27

Friday, October 25, 2013

የአዲስ አበባ ሃገረ ስብከት ስራ አስኪያጅ ተሰደዱ

ሲኖዶሱ ያሳለፈውን ውሳኔ ፓትርያርኩ ቀለበሱት 
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ አመታዊ ስብሰባውን እያከናወነ በሚገኝበት ሰዓት በተለያዩ አነጋጋሪ ክስተቶች መታጀቡን የፍኖተ ነጻነት ምንጮች ገልጸዋል፡፡
የሲኖዶሱ ስብሰባ ከመጀመሩ አስቀድሞ የፌደራል መንግስት ጉዳዩች ሚኒስትር ተወካዩች በተገኙበት የጠቅላይ ቤተ ክህነት ሰዎች፣የገዳማትና የአድባራት አስተዳዳሪዎችና ጳጳሳት በተገኙበት በተካሄደ ውይይት ጳጳሳቱ የመንግስት ተወካዩች ላቀረቡት ሐሳብ ያላቸውን ልዩነት በመግለጽ መንግስት በሃይማኖት ጉዳይ እጁን እንዲሰበስብና ለህገ መንግስቱ ተገዢ እንዲሆን መጠየቃቸው ይታወሳል፡፡በዚህ ስብሰባ ወቅት የሚመሩትን የአዲስ አበባ ሃገረ ስብከት በመወከል ተሳታፊ የነበሩት ሃላፊው ያለ ቤተ ክህነቱና ሃገረ ስብከቱ እውቅና ውጪ ወደ አሜሪካ ማቅናታቸው ተረጋግጧል፡፡
የአዲስ አበባው ሃገረ ስብከት ስራ አስኪያጅ መጋቤ አዲስ ይልማ ቸርነት ለስደት ሲዳረጉ ምክትላቸው የነበሩት አቶ ዩናስ ከሃላፊነታቸው እንዲነሱ ተደርገዋል፡፡መጋቤ አዲስ አገራቸውን በመልቀቅ ለስደት የተዳረጉበትን ምክንያት ከወቅቱ ፓትርያርክና አመራራቸው ጋር ስምምነት በማጣታቸው የተነሳ መሆኑን ምንጮቻችን ግምታቸውን አኑረዋል፡፡
ቅዱስ ሲኖዶሱ በትናንትናው የስብሰባ ውሎው ከሃላፊነታቸው እንዲነሱ በአብላጫ ድምጽ ወስኖባቸው የነበሩት የአዲስ አበባው ሊቀ ጳጳስ አቡነ እስጢፋኖስ በዛሬው ዕለት ፓትርያርኩ አቡነ ማቲያስ ‹‹አዲስ አበባ የእኔ ልዩ ሐገረ ስብከት በመሆኑና ማንም ሊያዝበት ስለማይችል ሊቀ ጳጳሱ በቦታቸው እንዲቀጥሉ በመወሰን የትናንቱን ውሳኔ ሽሪያለሁ››ማለታቸውን ምንጮቻችን ተናግረዋል፡፡
ሲኖዶሱ በማድረግ ላይ የሚገኘውን አመታዊ ስብሰባ ነገ የሚያጠናቅቅ ቢሆንም ሂደቱን በመከታተል ጋዜጠኞች እንዳይዘግቡ ሲኖዶሱ ለጋዜጠኞች ወደ ስብሰባው የመግቢያ ፈቃድ ከልክሏል፡፡

ምንጭ UDJ

Thursday, October 24, 2013

ሕዝባዊ እምቢተኝነት በውጭ አገር፤ እንዴት?

ግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ በሁለገብ ትግል ወያኔ ማስወገድ ይገባል ብሎ የሚያምና ለዚህም የሚታገል ድርጅት ነው። “ሁለገብ ትግል” ሲባል ሰላማዊም ሰላማዊ ያልሆኑም የትግል ስልቶችን መጠቀም ማለት ነው። “ሁለገብ ትግል” ሲባል በአገር ውስጥም ከአገር ውጭም የሚደረጉ ትግሎች ማለት ነው።
ከዚህ አንፃር በውጭ አገራት የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን ሚና ምን ሊሆን ይገባል?
በግንቦት 7 እምነት በውጭ አገራት የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን በድጋፍ ሰጭነት ሳይወሰኑ የትግሉ ቀጥተኛ ተሳታፊዎች መሆን ይኖርባቸዋል። በውጭ አገር የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን በወያኔ ጥቅሞችና ተቋማት ላይ በማመጽ ኢትዮጵያ ውስጥ ለሚገኙ ኢትዮጵያዊያን አርዓያ መሆን ይኖርባቸዋል።
በዚህ ረገድ የተጀመሩ አበረታች ጥረቶች አሉ፤ ለምሳሌ:
  1. ወያኔ ሙስሊሞችን ከክርስቲያኖች ለማጣላት ያልፈነቀለው ድንጋይ የለም። በውጭ አገራት የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን “እንቢ አንጣላልህም” ያሉት መሆኑ የሚያኮራ ነው። ወያኔ ከጠበቀው በተቃራኒ የሁለቱም ሃይማኖቶች መሪዎች በጋራ ጉዳዮች ላይ ሲመክሩ መታየቱ ተስፋ ሰጪ ጅማሮ ነው። አብሮነታችንን ማጎልበትና ይህንን በአደባባይ፣ በአዳራሾች፣ በቴሌቪዥን መስኮቶች ለኢትዮጵያ ሕዝብ ማሳየት እጅግ አስፈላጊ ነገር ነው። ውጭ የተጀመረው አገር ቤት መዳረሱ የማይቀር ነው። ይህ ሥራ ተጠናክሮ መቀጠል ይኖርብናል።
  2. ወያኔ በአባይ ግድብ ስም በውጭ አገራት ከሚገኙ ኢትዮጵያዊያን በርከት ያለ ገንዘብ እንደሚያገኝ ተስፋ አድርጎ የነበረ ቢሆንም ኢትዮጵያዊያን “ከአባይ በፊት የሰብዓዊ መብት ጥሰት ይገደብ” “ከአባይ በፊት ሙስና ይገደብ” እያሉ ወዋጮዎቹን እንቢ ብለዋል። በዚህ ጉዳይ ላይ እስካሁን የታየው ጽናት በጣም አበረታች ነው። የወያኔ ሹማምንት በአባይ ጉዳይ እንኳንስ ገንዘብ ስብሰባም ሊሰበሰቡ አልቻሉም። ይህም ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል።
  3. ኢትዮጵያዊያን በስፖርትና በኪነጥበባት መስኮች የሚያደርጓቸው መሰባሰቦች ለትግሉ ትልቅ እገዛ ይሰጣሉ። የኢትዮጵያ ስፓርት ፌዴሬሽን በሰሜን አሜሪካ (ESFNA) ከወያኔና ከወያኔ ሸሪክ ቱጃር ጋር ያደረገው ትንንቅ የሚያኮራ ነው። በርካታ ኢትዮጵያዊያን አገር፣ ነፃነት፣ ክብር ይበልጥብኛል ብለው የቀረቡላቸውን አጓጊ ማባበያዎችን “እንቢ” ብለዋል። ይህ ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል።
  4. ባለፈው ዓመት ጋዜጠኛ አበበ ገላው በመለስ ዜናዊ ላይ፤ ዘንድሮ ደግሞ ጋዜጠኛ ሳዲቅ አህመድና አቶ መስፍን የዘረኛው ወያኔ ግንባር ቀደም አስተባባሪ በሆነው ስብሀት ነጋ ላይ ያሰሙት ተቃውሞ በጣም የሚደገፍና በውጭ አገራት የምንገኝ ኢትዮጵያዊያን ሁሉ ባህል ሊሆን ይገባዋል።
  5. በስዊድን የሚገኙ የሕግ ባለሙያዎች የጀመሩት እና በኢትዮጵያዊያን ከፍተኛ ተሳትፎ እየተካሄደ ያለው የወያኔ ወንጀለኞችን ወደ ፍርድ የማቅረብ ሂደት ተጠናክሮ መቀጠል አለበት።
እነዚህ መልካም ሥራዎች ምሳሌቶች ሲሆኑ በውጭ አገራት የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን ከዚህ በላይ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል። አንዳንዱን ለአብነት ያህል ከዚህ በታች ተዘርዝረዋል።
  1. በአገራችን ውስጥ መሠረታዊ የሆነ ለውጥ እንዲመጣ ከፈለግን ወያኔን ማስደንገጥ፣ ማሸበር፣ ካስፈለገም ማስወገድ የሚችል የአመጽ ኃይል መኖሩ ወሳኝ ነው። እንዲህ ዓይነት የወገን ኃይል ከጀርባው መኖሩ ሲሰማው ነው ሕዝብ ለእንቢተኝነት የሚነሳሳው። በውጭ አገራት የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን ይህንን ኃይል ቢቻል መቀላቀል፤ ካልተቻለም በአባላት ምልመላ፣ በፋይናንስ፣ በሎጂስቲክስና ዲፕሎማሲ መደገፍ ይጠበቅባቸዋል። ይህ ከሁሉ የላቀ የእምቢተኝነት መገለጫ ነው።
  2. ትግሉ እየመረረ መሆኑ በመረዳት በርቀት ሆነን ከመብሰክሰክ በትግል ላይ ያሉትን ድርጅቶች መቀላቀል ሌላው አሁኑኑ ልናደርገው የሚገባ ነገር ነው። ድርጅቶች “አይረቡም” ብለን ስላጣጣልናቸው አይጠናከሩም። ድርጅቶችን ማጠናከርና ማዘመን ያለብን እኛው ነው። መሪዎችን ማውጣት ያለብን እኛው ነው። እስካሁን ድርጅቶችን ያልተቀላቀልን ካለን መቀላቀልና ትግሉን ማጧጧፍ ይኖርብናል።
  3. በየተገኘው አጋጣሚ ሁሉ ወያኔን “እንቢ” እንበል። “እንቢ” የማለትን አጋጣሚ ማሳለፍ የለብን። “እንቢ” ማለት የምንችልባቸው አጋጣሚዎች ብዙዎች ናቸው። ለምሳሌ: -
ሀ) ወያኔ የመኖሪያ ቤቶች ግንባታን አዲስ የገንዘብ ማለቢያ ለማድረግ አቅዶ ተነስቷል። ወደ ሚሊዮን የሚጠጉ ቤቶችን በ2 ዓመት ጨርሼ አስረክባለሁ በሚል ማባበያ በውጭ አገራት ከሚገኙ ኢትዮጵያዊያን ገንዘብ ለመሰብሰብ ዝግጅቱን አጠናቋል። ይኸንን ነገር አጠንክረን “እንቢ” ማለት ይኖርብናል። “ለኛ ቤት ከመሰጠቱ በፊት፤ የተፈናቀሉ ወገኖቻችን መወደቂያ ያግኙ” ማለት ካልቻልን በራሳችን ማፈር አለብን። የአውሮፓና የአሜሪካ መንግሥታትን አምባገነኖችን በገንዘብ አትደግፉ እያልን እኛ ራሳችን ወያኔን በገንዘብ የምንደግፈው ከሆነማ ከነሱ ብሰን መገኘታችንን እንወቀው።
ለ) ወያኔ በስደተኛ ስም በመካከላችን የሰገሰጋቸውን ካድሬዎችን የማጋለጥ ዘመቻ ማፋፋም አለብን። የወያኔ ደጋፊዎችን በኤርትራ ስደተኞች ስም እንደሚገቡ መረጃዎች አሉ። በደል ደርሶብናል ብለው መንግሥታትን አሳምነው የመኖሪያ ፈቃድ ካገኙ በኋላ አጠቃን ካሉት አገዛዝ ጋር የሚሠሩ መሆናቸው የሚያረጋግጡ ማስረጃዎችን አጠናቅረን ለየሀገሩ መንግሥታ ማቅረብ እንደ አቢይ ሥራ መያዝ ይኖርብናል።
ሐ) የወያኔ ባለሥልጣናት የሚገዟቸውን ቤቶች፤ የሚያስተዷድሯቸውን ቢዝነሶች እያደንን ማጋለጥ ይኖርብናል።
መ) የወያኔዎች ሹማምንት በአሜሪካና አውሮፓ በነፃነት ሊዘዋወሩ አይገባም። በሄዱት ሁሉ ተቃውሞና ውርደት ሊከተላቸው ይገባል።
ሠ) የወያኔ ቢዝነሶች ላይ ማዕቀብ ማድረግን (ቦይ ኮት) መልመድ አለብን። ጥረቶቻችንን በፈጠራ ከደገፍን ወደ አገር ቤት የምንልከው ገንዘብ የወያኔ የውጭ ምንዛሬ ረሀብ ማስታገሻ የማይሆንበት መንገድ መሻት አለብን።
ረ) ለወያኔ ባለሥልጣኖች ዲግሪ የሚያድሉ ዩኒቨርስቲዎችና ኮሌጆችን ማዋረድ መጀመር አለብን። ስምንተኛ ክፍል እንኳን በወጉ ላልጨረሱ ሰዎች የማስትሬት ዲግሪ እንደሰጡ ማሳወቅ የኛ ኃላፊነት መሆን አለበት።
በግንቦት 7 እምነት ትግሉ በሁሉም ሥፍራ ነው። ኢትዮጵያዊያን በያለሉበት ቦታ በተደራጀና በተቀናጀ መልክ ወያኔን ፊት ለፊት ከተጋፈጥን የድላችን ቀን እናቀርባለን።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!

Monday, October 21, 2013

የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት ይዞታ

ዓለም ዓቀፉ የሰብዓዊ መብት ተሚዋጋች ድርጅት ሂዩማን ራይትስ ዎች ባለፈው ዓርብ በኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት ይዞታ ላይ ያተኮረ በተለይም አዲስ ኣበባ በሚገኘው እና ማዕከላዊ ተብሎ በሚታወቀው የፌደራሉ የምርመራ ማዕከል በእስረኞች ላይ ይፈጸማሉ ባላቸው ሰብዓዊ ሰቆቃዎች ላይ ያነጣጠረ አዲስ ሪፓርት ይፋ ኣድርገዋል።
Zu: Boss von mexikanischem Golf-Kartell festgenommen - Neuer Schlag gegen Drogenmafia
A relative of an inmate observes policemen behind the security fence after a riot inside Apodaca prison, on February 20, 2012, near Monterrey, state of Nuevo Leon, Mexico. At least 44 inmates have been killed during a riot Sunday and about 30 alleged members of the drug cartel Los Zetas were rushed out from the prison. AFP PHOTO/Julio Cesar Aguilar (Photo credit should read Julio Cesar Aguilar/AFP/Getty Images)
ሰብዓዊ መብት ሲባል በነገስታት መልካም ፈቃድ የሚቸሩ ወይንም መንግስታት ከሚመሩባቸው ህግጋተ መንግስታት የሚመነጩ ብቻ ሳይሆኑ በ ተ መ ድ የሰብዓዊ መብቶች ድንጋጌዎች መሰረት ሰዎች ሰው በመሆናቸው ብቻ በተፈጥሮ የተቀዳጁኣቸው መሰረታዊ የሰው ልጅ መብቶች ናቸው። በእነዚህ ህጎች መሰረት ደግሞ እንደ መኖ ኣልባሳት እና መጠለያ የመሳሰሉ የሰው ልጅ መሰረታዊ ፍላጎቶችን ጨምሮ ዜጎች እንደ ህክምና እና ትምህርት የመሳሰሉ ማህበራዊ ፍላጎቶችን ሁሉ የማግኘት መብት ኣላቸው።
እናም ጥቂት ለማይባሉ ዓመታት እንዲያውም ዓስርተ ዓመታት ማለት ይቻላል በረኃብ አለንጋ ከሚገረፈው የኢትዮጵያ ህዝብ አንጻር ለምን የሚል ጥያቄ ቢቀርብላቸው እንደ ምክኒያት አዲሶቹ መንግስታት በቀድሞዎቹ ላይ እያላከኩም ቢሆን መልሳቸው ግን ምን ሊሆን እንደሚችል መገመት ይቻላል። ድህነት። በእርግጥ የፖሊሲ ችግሮች ሳይዘነጉ ከድህነት ወለል በታች በምትገኘው ኢትዮጵያ ኣምኖ ለመቀበል ማስቸገሩ ባይቀርም ኣይደለም ብሎ ለመከራከር ግን ሊከብድ ይችላል።
ሌሎች በርካታ የግል እና የቡድን መብቶች በገኃድ ሲጨፈለቁ እና በዚሁ ምክኒያት ሰዎች ሲታሰሩ ሲሰቃዩ እና ሲገደሉ ግን የሂዩማን ራይትስ ዎች የበላይ ኃላፊዎች እንደሚሉት በየኣጋጣሚዊ ከየኣቅጣጫው በተለያየ መልኩ ተቃውሞ እና ውግዘት ተለይቶት ኣያውቅም። ለዚህ ግን ባለስልጣናቱ ኣንድም እንደተለመደው ከጥያቄ መራቅ እና ኣሊያም ከእውነት የራቀ የፈጠራ ወሬ እያሉ ከመካድ ያለፈ ምላሽ የላቸውም የሚለው ሂዩማን ራይትስ ዎች ባሳለፍነው ሳምንት ማገባደጃ ላይም የኢትዮጵያን የሰብዓዊ መብት ይዞታ የሚያብጠለጥል አዲስ ሪፖርት ኣውጥተዋል።
ARCHIV - Ein Häftling in Guantanamo in Fußschellen. (am 27.04.2010von der US-Armee herausgegebenes Archivfoto). Seit zehn Jahren halten die USA Terrorverdächtige auf ihrem Marinestützpunkt Guantánamo Bay in Kuba fest. Nach den Anschlägen vom 11. September 2001 hatte US-Präsident George W. Bush dort die Errichtung eines Internierungslagers angeordnet. Sein Nachfolger Barack Obama beschloss zwei Tage nach seinem Amtsantritt im Januar 2009, das Camp binnen Jahresfrist zu schließen. Es war zum Symbol für Folter und Willkür geworden. Aus Obamas Versprechen wurde nichts. EPA/Michelle Shephard / POOL POOL PHOTO. EDS: IMAGE REVIEWED BY U.S. DEPARTMENT OF DEFENSE OFFICIAL PRIOR TO TRANSMISSION. (zu dpa-Themenpaket Guantanamo) +++(c) dpa - Bildfunk+++
በዚሁ ባለፈው ዓርብ ይፋ በሆነው እና 70 ያህል ገጾች ባሉት የሂዩማን ራይትስ ዎች ዘገባ መሰረት በኢትዮጵያ እስር ቤቶች በተለይም አዲስ ኣበባ በሚገኘው እና ማዕከላዊ ተብሎ በሚታወቀው የፌደራሉ የምርመራ ማዕከል በሚገኙ እስረኞች ላይ ይፈጸማሉ የተባሉ ሰቆቃዎችን ለማጋለጥ ተሞክረዋል። ከሁሉም በላይ በሪፖርቱ መሰረት የፖለቲካ እስረኞች ግርፋት ወይንም ቶርችን ጨምሮ ፈታኝ በሆነ ኣያያዝ እየተሰቃዩ መረጃ እንዲአጡ ይደረጋሉ። የሐሰት ሰነድም እንዲፈርሙ ይገደዳሉ ተብለዋል። ይኸው መረጃ ኣንዳንዴ እስረኞቹ ተከሰው ችሎት በሚቀርቡበት ሳዓት እንደ ማስረጃ እንዲቀርብባቸው የሚደረግበት ኣጋጣሚም እንዳለ ተወስተዋል።
35 የቀድሞ እስረኞችን እና ቤተሰቦቻቸውን ዋቢ በማድረግ ሪፖርቱ እንደገለጸው በዚሁ በማዕከላዊ የምርመራ ማዕከል እስረኞች በጥፊ በእርግጫ በጠመንጃ ሰደፍ በዱላ እና በተለያዩ ነገሮች መደብደባቸውን ለሆዩማን ራይትስ ዎች ኣስረድተዋል። ኣንድ ከኦሮሚያ የተያዘ የኦሮሞ ተማሪም ለወራት እጆቹን በካቴና እና እግሮቹን በእግር ብረት ታስሮ ለምግብም ሆነ ለመጸዳዳት በእስረኞች እርዳታ ብቻ መክረሙን በምሬት ያስታውሳል ሲል ሂዩማን ራይትስ ዎች ዘግበዋል።
በሂዩማን ራይትስ ዎች የኣፍሪካ ጉዳዮች ም/ዳይሬክተር የሆኑት ሚ/ስ ሊስሌ ሌፍኮቭ እንደሚሉት ደግሞ የማዕከላዊው እስር ቤት በእሳቸው ኣባባል ማጎሪያ ቤት የተለመዱ ሶስት ክፍለ ማጎሪያዎች ኣሉት። ኣንደኛው ሰዎች ያለ መብራት ተነጥለው ለብቻ የሚታሰሩበት እና ጭለማ ቤት የሚባለው ነው። ሁለተኛው ለግርፋት የተመቻቸው እና በእስረኞቹ ኣጠራር ጣውላ ቤት የሚባለው ሲሆን ሶስተኛው ደግሞ በኣንጻራዊነትም ቢሆን የተሻለ እና እስረኞች እየተንቀሳቀሱ በጋራ የሚታሰሩበት እና ከዚሁ የተነሳ ሸራተን ተብሎ የሚታወቀው ነው።
ሌላው ኣስቸጋሪ ጉዳይ በሪፖርቱ እንደተጠቀሰው እስረኞች ከዘመዶቻቸውም ሆነ ከጠበቆቻቸው እንዳይገናኙ መደረጉ ነው። ምክኒያቶቹ ደግሞ ሚ/ስ ሌፍኮቭ እንደሚሉት እስረኞችን ኣስፈራርቶ ኣሰቃይቶ እና ኣደናግሮ መረጃ ለማወጣጣት እና ቢያንስ ጉልህ የሆኑ የግርፋት ኣሻራዎች እንዳይታዩ ለማድረግም ጭምር ነው።
በኢትዮጵያ ያለው የሰብዓዊ መብት ይዞታ ይበልጥ እየተበላሸ የመጣው የተጭበረበረውን የ2005ቱን ምርጫ ተከትሎ ሲሆን ከ2010 ዓ ም ወዲህ በተለይ ህወኃት መራሹ የኢትዮጵያ መንግስት የሚያካህደው የመብት ጥሰት ህገ ወጥ ብቻም ሳይሆን ሰብዓዊነትም የጎደለው መሆኑን የሂዩማን ራይትስ ዎች ዘገባ ኣመልክተዋል።
የጸረ ሽብር ህግ የተባለው የኢትዮጵያ ህግም ይላል ሪፖርቱ የኢትዮጵያ ባለስልጣናት ተቃዋሚዎችን ለማፈን ሰላማዊ እንቅስቃሴዎችን ለማሽመድመድ የኃይማኖትም ሆነ የብሔር ተቐማት ኃላፊዎችን ለማሰር እና በኣጠቃላይ ሰብዓዊ መብትን ለመጣስ የሚጠቀሙበት ተጨማሪ መሳሪያ ሆነዋል።
ከኢቲኂጵያ መንግስት በኩል የጠ/ሚ/ሩ ቃል ኣቀባይ አቶ ጌታቸው ረዳ ግን የተባለው ሁሉ ከዕውነት የራቀ እና የተለመደ የሂዩማን ራይትስ ዎች ተራ ድራማ ነው ሲሉ ኣጣጥለውታል።
መንግስታዊው የኢትዮጵያ ሰብኣዊ መብት ኮሚሺን ሊቀመንበር ኣንባሳደር ጥሩነህ ዜናም ከአቶ ጌታቸው ረዳ ጋር በተቀራረበ መልኩ የሂዩማን ራይትስ ዎች ዘገባን ደካማ ሪፖርት ብለውታል።
የቀድሞው የሰብዓዊ መብት ጉባዔ ሰመጉ ዳይሬክተር አቶ እንዳልካቸው ሞላ ግን በዚህ ኣይስማሙም። እንደ አቶ እንዳልካቸው እምነት የሂዩማን ራይትስ ዎች ዘገባ ትክክለኛ እና ተጨባጭ ሪፖርት ነው።
በኢትዮጵያ እስር ቤቶች የቶርች ሰለባ ከሆኑት መካከል ደግሞ አቶ ሁሴን ኣህመድ በኢትዮጵያ እስረኖች ላይ ቶርች ስለመካሄዱ ኣንድ እና ሁለት የለውም ይላሉ። በኣሁኑ ጊዜ በኖርዌይ ኣገር የሚኖሩት አቶ ሁሴን ከደረሰባቸው ድብደባ የተነሳ አካላዊ እና አእምሮኣዊ ጉዳት እንደ ደረሰባቸው ይናገራሉ። ከዚሁ የተነሳ ያለ ድጋፍ መንቀሳቀስ እንደማይችሉም ኣስረድተዋል። አቶ ሁሴን ኣህመድ ይህንኑ ለዓለም ህብረተሰብ ለማሳወቅ ከዓለም ዓቀፉ የጸረ ቶርች ኮሚቴ ጋርም እየተንቀሳቀሱ እንደሚገኙ ይታወቃል።
ጃፈር ዓሊ
ሂሩት መለሰ
source DW.DE Amharic 

ተገዥነታችን ለሕዝብና ለሕግ እንጅ ለአምባገነኖች ማስፈራሪያ አይደለም!!!

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ(አንድነት) የተሰጠ መግለጫ
        ፓርቲያችን አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ በሰላማዊና ሕጋዊ መንገድ ተመዝግቦ በሀገራችን ላይ ዴሞክራሲያዊ ስርዓት እንዲሰፍንና ፍትሃዊነት እንዲኖር በቁርጠኝነት እየታገለ ይገኛል፡፡ በትግሉ ውስጥም ፓርቲያችን የተጋረጡበትን ፈተናዎች እየተወጣና የሚከፈለውን ዋጋ እየከፈለ ሰላማዊ ትግሉን አጠናክሮ በመቀጠል ለህዝቡ ያለውን ታማኝነት እያረጋገጠም ነው፡፡
        ፓርቲያችን በመላ ኢትዮጵያ ያለውን አደረጃጀት በመጠቀምና ሕዝቡን በማሳተፍ ለሶስት ወራት የሚቆይ ህዝባዊ ንቅናቄ በማካሄድ የመጀመሪያ ዙር የሆነውን ሰላማዊ ትግል ለማጠናቀቅ ችሏል፡፡ የሚልዮኖች ድምጽ ለነፃነት በሚል መሪ ቃል የተጀመረው ይህ ህዝባዊ ንቅናቄ አራት መሰረታዊ ጥያቄዎችንና ወቅታዊ ጉዳዮችን ያነገበ ሲሆን እንደ ሁልጊዜውም ፓርቲው ሰላማዊነቱን በጠበቀ መልኩ በቁርጠኝነት ንቅናቄውን በታቀደለት መሰረት አካሂዷል፡፡ ወደፊትም ይህንን አጠናክረን የምንቀጥል መሆኑን ለማረጋገጥ እንወዳለን፡፡
      ኢህአዴግና መሪዎቹ መንግስት እንደመሆናቸው መጠን በሰላማዊ መንገድ ለምንንቀሳቀስ ፓርቲዎች ድጋፍና ትብብር ማድረግ ሃላፊነታቸው ቢሆንም ከዚህ በተቃራኒ በሰላማዊ መንገድ እየተንቀሳቀስን ያለን ፓርቲዎችን ለማጥፋት ቀን ከሌሊት እየሰሩ ይገኛሉ፡፡ ልክ ከዚህ በፊት ሲያደርጉት እንደነበረው ባልዋልንበት ዋሉ፣ ባልተገኘንበት ተገኙ… በማለት ህዝባዊ መሰረታችን ጥርጣሬ ላይ እንዲወድቅ ለማድረግ ያገኙትን አጋጣሚ ሁሉ ይጠቀማሉ፡፡ ለዚህ አባባላችን ጥሩ ማስረጃ የሚሆነን ባለፈው ሳምንት ጋዜጣዊ መግለጫ የሰጡት አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ በመሪ ደረጃ በማይጠበቅ መልኩ ህጋዊና ሰላማዊ እንቅስቃሴችንን እሳቸው ከፈለጉት አካል ጋር በማገናኘት ስም ለማጥፋት መሞከራቸው ነው፡፡
    አቶ ኃይለማርያምም ሆኑ መንግስት የሆነው ፓርቲያቸው ለሚነሱ ሀገራዊ ጥያቄዎች አፋጣኝ ምላሽ ከመስጠትና በተነሱ ጉዳዮች ዙሪያ ለመነጋገር በርን ከመክፈት ይልቅ ዙሪያ ጥምጥም በመሄድ ለጥያቄ አቅራቢዎች የተለየ መልክ ለመፍጠር የሚያደርጉት ጥረት የምናውቀውና የነበረ አሮጌ መንገድ ነው፡፡
     ፓርቲያችን ህዝባዊ ንቅናቄ ያደረገው ህጋዊ አግባቡን ጠብቆና የራሱን አጀንዳ ቀርፆ ነው፡፡ ጠ/ሚንስትሩ የራሳቸው አጀንዳ የላቸውም፤ የሻዕቢያ መልክት አድራሾች ናቸው ወዘተ ያሉበት ድፍረት የራሳችን አጀንዳ እንዳለን ጠፍቷቸው ሳይሆን ሆን ብለውና አቅደው ስም ለማጥፋት፣ ህዝቡ ውስጥ ጥርጣሬ ለመጫር በመፈለጋቸው ብቻ ነው፡፡ እኛ ተላላኪነታችን ለኢትዮጵያ ህዝብና ይጠቅማል ብለን ለቀረፅነው የፖለቲካ ፕሮግራም ብቻ ነው፡፡ እንደዚህ አይነቱን ስም ማጉደፍም ፓርቲያችን በቸልታ አይመለከተውም፡፡ ስለዚህ አቶ ኃይለማርያም ከባለፈው ስህተታቸው በመማር ከአጉልና ማስረጃ አልባ ፍረጃ እንዲላቀቁ አጥብቀን እንመክራለን፡፡
      የሙስሊም ወገኖችን ጥያቄ በተመለከተ ፓርቲችን ያለው አቋም ግልፅ ሲሆን አሁንም ጥያቄያችው በሰላማዊና ህጋዊ መንገድ መመለስ፤ ዜጎች የመብት ጥያቄ ሲያነሱ መፈረጁ ይቁም፤ ካላግባብ የሃማኖት ነፃነት ጥያቄ ስላነሱ ወደ እስር ቤት የተወረወሩ ዜጎች ባስቸኳይ ይፈቱ የሚል ነው፡፡ በተጨማሪም ስርዓቱ ካላግባብ ያሰራቸው ጋዜጠኞችና የፖለቲካ እስረኞች ባስቸኳይ ይፈቱ ብለን እንጠይቃለን፡፡ ወደፊትም ይህንን ጥቄያችንን አጠናክረን እንቀጥላለን፡፡ እኛ እያልን ያለነው ከኢ-ፍትሃዊነት ጋር አንደራደርም፤ አንቀበለውም ነው፡፡ ስለዚህ ፓቲያችንን ከሙስሊም ወገኖች ጥያቄ ጋር በማያያዝ ትርፍ ፍለጋ መሯሯጥ ስህተት ብቻ ሳይሆን ወንጀልም ነው፡፡
      አቶ ኃይለማርያም በህገ መንግስቱ በግልጽ የተቀመጡ ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ፣ የመሰብሰብና አቤቱታ የማቅረብ መብትን በአደባባይ የጨፈለቀው ንግግራቸው ሰላማዊ ሰልፍን በተመለከተ ነው፡፡ በቂ ጥበቃ የለንም በሚል ተልካሻ ሰበብ የዜጎችን መብት መንጠቅ አይቻልም፡፡ በቂ ጥበቃ ማድረግ ያልቻለ መንግስት ስልጣኑን ለህዝብ በማስረከብ ይቅርታ ጠይቆ መሄድ እንጅ ከአሁን በኋላ መብታችሁን አታገኟትም በማለት መዛት ትዝብት ውስጥ የሚጥል ድርጊት ነው፡፡
        ስለዚህ ፓርቲያችን አንድነት አሁንም ተገዥነቱን ለህዝቡና ለህግ አድርጎ በአምባገነኖች ዛቻ ሳይበረግግ፤ ዘር፣ ፆታ፣ ሀይማኖት፣ ቀለም ሳይለይ ዜጎች የሚያነሱት ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጥያቄዎች እንዲመለሱ፤ የመንግስት በሐይማኖት ጣልቃ ገብነትም እንዲቆም ትግሉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ ያረጋግጣል፡፡
      ከዚህ በተጨማሪም ፓርቲያችን የአፍሪካ መሪዎች ብዙ መፍትሄ ፈላጊ ችግሮች ባሉባት አፍሪካ ተሰብስበው እንግደል፣ እንሰር፣ እንጨፍጭፍ፣ ዘር እናጥፋ፣ ዜጎቻችንን እናሰቃይ ግን መታሰርም መከሰስም የለብንም በሚል የያዙት አቋም አሳፋሪና ተቀባይነት የሌለው ነው፡፡ ሕግ እየጣሱ በህግ አለመጠየቅ አይቻልም፡፡ ዘር እያጠፉ ያለመታሰር መብት አይኖርም፡፡ ማንም ሰው ከህግ በላይ የመሆን መብት የለውም፡፡
    የአፍሪካ መሪዎች ተሰብስበው ማለት ያለባቸው አይሲሲ ሊከስሰን አይገባም ሳይሆን የዜጎቻቸውን እንባ ማበስ ነው፡፡ ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች እንዲረጋገጡ መጣር ነው፡፡ መሳሪያና ጉልበት የችግሮች መፍቻ መሆናቸው እንዲያበቃ የሰለጠነ መንገድ መከተል ነው፡፡ የሚያስከስሳቸውና የሚያሳስራቸው ስራቸው እንጅ ሌላ አይደለም፡፡ ስለዚህ ፓርቲያችን አሁንም ሆነ ወደፊት በዜጎቻቸው ላይ ግፍና ሰቆቃ የሚፈፅሙ ሁሉ ሳይውል ሳያድር ወደ ፍርድ መቅረብ አለባቸው ብሎ ያምናል፡፡ አንዳንድ የአፍሪካ መሪዎች አይሲሲን በተመለከተ የሚያራምዱት የአትክሰሱን አቋም ፓርቲያችን አይቀበለውም፡፡
ዘላለማዊ ክብር ለኢትዮጵያ!!!
አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት)
                                              ነሐሴ 11 ቀን 2005 ዓ.ም
                                             አዲስ አበባ      
 ምንጭ ዘ-ሐበሻ

ስብሃት ነጋ ከአዜብ ጋር ፍጭት እንደነበር አመኑ * ጋዜጠኛ ደረጀ ደስታ እስካሁን ተጠይቀው የማያውቁትን ጠየቃቸው

(ዘ-ሐበሻ) የዘኢትዮጵያ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ ደረጀ ደስታ በዋሽንግተን ዲሲ የሕወሓት መስራች የሆኑትን አቦይ ስብሃት ነጋን እስካሁን ተጠይቀው የማያውቋቸውን ጥያቄዎች በመጠየቅ ሲያፋጥጣቸው ዋለ። ጋዜጠኛ ደረጀ ደስታ ከሕወሓት ጋር ባደረገው ቃለምልልስ ከወ/ሮ አዜብ መስፍን ጋር አለባቸው ስለሚባለው ፍጭት አንስቶባቸዋል። በተጨማሪም በመሬት ጉዳዮች እና በሌሎች ጉዳዮችም ጠንካራ ጥያቄዎችን በመጠየቅ ተፈታትኗቸዋል። ስብሃት በዚህ ቃለ ምልልሳቸው ሕወሓት ከመለስ በኋላ ጠንክሯል፤ አቶ መለስ ከሞቱ በኋላ ስለተሾሙት የትግራይ ጀነራሎች የማውቀው የለም ብለዋል። ይህ ቃለምልልስ ሊያመልጥዎ አይገባም፤ እንደሚከተለው አስተናግደነዋል።
“የኢሕአዴግ አባል የሚባል የለም፤ የሕወሓት አባል ነኝ”።
ከአቶ መለስ ጋር የሃሳብ ልዩነት ነበራቸው? 

Saturday, October 19, 2013

መዐሕድ “የአማራ ተወላጅ ተማሪዎች መፈናቀል” እንዲቆም ጠየቀ

Written by  ናፍቆት ዮሴፍ
በ15 ቀን ውስጥ ከወልቃይት  ጠገዴ ሁለት ሺ ተማሪዎች ተፈናቅለዋል”
            የመላው አማራ ህዝብ (መዐህድ) በአማራ ተወላጅ ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ያለው መፈናቀል በአስቸኳይ እንዲቆም ጠየቀ፡፡ መአህድ ባወጣው መግለጫ እንዳስታወቀው፤ የአማራ ተወላጆችን መፈናቀል በተመለከተ ከ2004 ዓ.ም ጀምሮ ለሚመለከታቸው የመንግስት አካላት ማሳወቁንና መፈናቀሉ እንዲቆም መጠየቁን ጠቁሞ፤ ጉዳዩ እስካሁን እልባት አለማግኘቱን ገልጿል፡፡
መፈናቀሉ ሊቆም ቀርቶ ተጠናክሮ መቀጠሉንና በቅርቡም ከጉራፈርዳ፣ ከቤኒሻንጉል እና ከወልቃይት ጠገዴ የአማራ ተወላጅ ተማሪዎች መፈናቀላቸውን የጠቆመው መዐህድ፤ ድርጊቱ በአገሪቱ ስርዓት አልበኝነት መንሰራፋቱን ያሳያል ብሏል፡፡
ከተማሪዎች በተጨማሪ የአማራ ተወላጅ አርሶ አደሮችንም ለይቶ ማፈናቀሉ ለመሪር ሀዘን እንደዳረገው መአህድ ገልፆ፤ አንድን ብሄር ማዕከል ያደረገ ማፈናቀል እንዲቆም ጠይቋል፡፡
ባለፉት 15 ቀናት ብቻ “አካባቢያችሁ አይደለም” በሚል ከወልቃይት ጠገዴ ሁለት ሺህ ተማሪዎች መፈናቀላቸውን የገለፁት የመአህድ ፕሬዚዳንት አቶ ሸዋንግዛው ገብረስላሴ፤ ከጉራፈርዳም ተማሪዎች ተፈናቅለው ከትምህርት መስተጓጐላቸውንና ለጊዜው ቁጥራቸው በውል አለመታወቁን ፕሬዚዳንቱ ጨምረው ገልፀዋል፡፡ “ከጉራፈረዳ ምን ያህል ተማሪዎች እንደተፈናቀሉና በምን ሁኔታ ላይ እንዳሉ የሚያጣራ ቡድን ልከናል” ያሉት አቶ ሸዋንግዛው፤ አጣሪ ቡድኑ ሁኔታውን አጣርቶ ሲመለስ መዐህድ በድጋሚ የአቋም መግለጫ እንደሚያወጣም ተናግረዋል፡፡
“ተማሪዎች የወደፊት አገር ተረካቢ ሲሆኑ አርሶ አደሮችም የአገር ህልውና ምሰሶ ስለሆኑ በአገራቸው የትኛውም ቦታ የመማርና የመስራት መብታቸው ተከብሮ፤ ተማሪዎችም ወደ ትምህርት፣ አርሶ አደሮችም ወደ ስራ ገበታቸው እንዲመለሱ እንጠይቃለን” ብለዋል፤ ፕሬዚዳንቱ፡፡
የአማራ ተወላጆችን ከተለያዩ አካባቢዎች ከማፈናቀል በተጨማሪ የአማራውን ክልል ለማጥበብ ወደ አጐራባች ክልሎች የሚደረገው የመሬት ሽንሸና ዘመቻ በአስቸኳይ እንዲቆም መዐህድ በመግለጫው የጠየቀ ሲሆን በአማራ ህልውና ላይ በተደጋጋሚ እየደረሰ ያለው ስልታዊ እንቅስቃሴ እና ትንኮሳ ሊገታ ይገባል ሲል አሳስቧል፡፡ ሌሎች ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎችና ሲቪል ማህበራትም ይህንን ኢ-ሰብአዊ ድርጊትና መብት ረገጣ እንዲያወግዙ ጠይቋል፡፡
ምንጭ አዲስ አድማስ

Tuesday, October 15, 2013

Dictatorship prisoners

The film about journalists Martin Schibbye and Johan Persson, who was imprisoned in Ethiopia and was sentenced to eleven years in prison here.The Swedish journalists Martin Schibbye and Johan Persson was shot and arrested when attempting to illegally enter the Ogaden region of Ethiopia to report on conditions there. For four days, they were kept in the desert where they were forced to participate in a film that would be used as evidence against them. The interrogations were harsh and they suffered, among other things, a mock execution. They eventually sentenced by an Ethiopian court to eleven years in prison but was released after just over a year ago they asked the government for clemency.
Abdullahi Hussein was the regional president's adviser and head of the Ogaden TV channel Cakaara News. He had responded to the abuses and atrocities against civilians and for a few years he copied the president's secret video files. Files included the internal meetings where individual officers and soldiers in the regional militia testify arbitrary arrests, torture, murder, extortion and rape.Abdullahi Hussein planned to escape from Ogaden and share its evidence to the international media and human rights organizations.
Abdullahi was with the president when John and Martin were arrested and he was able to follow the course of events in the desert from the "other side". When he got the film material from the desert in his hand, he decided that it was time to leave the Ogaden.
In the documentary film Dictatorship prisoners, directed by Andreas Rocksén , gives John, Martin and Abdullahi a frightening picture of the Ogaden, a region that has become increasingly attractive for international oil and mineral companies, among them the Swedish Lundin Group.
Transmission:BBC1Monday, October 14, 2013 at 21:00
http://www.svt.se/dokumentarfilm/diktaurens-fangar.

በደብረ ማርቆስ ዩነቨርስቲ ተማሪዎችና በመንግስት መካከል ረብሻ ተነስቷል

(ዘ-ሐበሻ)  ጥቅምት 4 ቀን 2006 ዓ.ም. በደብረማርቆስ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎችና በመንግስት መካከል ውጥረት ነግሷል፡፡ የችግሩ ዋነኛ መንስኤም በግቢው በሚቀርብ ምግብ ዙሪያ እና መንግስት የዩኒቨርስቲ ተማሪዎችን ኃይማኖታዊ ስርዓትን
የተላበሰ አለባበስ መልበስ የተከለከለ ነው በሚል በተለይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ኃይማኖት ተካታዮችና የእስልምና ኃይማኖት ተከታዮች ድርጊቱን በመቃወማቸው ረብሻ ተቀስቅሷል፡፡ በዚህም በተፈጠረ አለመግባባት የፌደራል ፖሊስ ተማሪዎችን እየደበደበ ከግቢ ያስወጣ ሲሆን፤በዚህም የቆሰሉ ተማሪዎች እንዳሉ እና በአሁን ሰዓትም የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው መሆኑም ተጠቁሟል፡፡
በተለይ ትናንት ሰኞ ማታ ጥቅምት 4 ቀን 2006 ዓ.ም. በርካታ ተማሪዎች በፈደራል ፖሊስ እየታደኑ እየታሰሩ እንደሚገኙ የተጠቆመ ሲሆን በከተማው ያሉ ወላጆችም በጉዳዩ እጅግ በመቆጣታቸው በዚህ ምሽትም በርካታ ወላጆችም በተማሪዎቹ ላይ እየተወሰደ ባለው እርምጃ በመቃወም ከቤታቸው ውጭ ከፌደራል ፖሊስና ከአማራ ክልል ፖሊስና አስተዳደር ጋር መፋጠጣቸውም ተነግሯል፡፡ በተፈጠረው ችግርም እስካሁን ምን ያህል ተማሪ እንደተጎዳ በቁጥርና መጠን ለማወቅ አልተቻለም፡፡ በጉዳዩ ዙሪያ የዩኒቨርስቲው አስተዳደርንና የአማራ ክልል አስተዳደርና ፖሊስን  ለማናገር ብንሞክርም ስልካቸው ዝግ ነው፡፡ የነበረው አለመግባባትም ይህ እስከተዘገበበት ድረስ በግቢው በደንብ አለመረጋጋት እንዳለም ምንጮች አስታውቀዋል፡፡

Saturday, October 12, 2013

አደባበዬቻችን እና መንገዶቻችን መሉሱልን? ይድነቃቸው ከበደ (የሰማያዊ ፓርቲ የህግ ጉዳይ ሃላፊ)

‹‹ ዲሞክራሲ የሚመሠረተው መንግስት ሕዝቡን ሊያገለግል የቆመ ነው በሚል መሠረት ሃሳብ ላይ ነው፡፡ ይህም ማለት
ሕዝብ መንግሥትን ለማገልገል የተፈጠረ አይደለም፡፡ በሌላ አነጋገር ህዝብ የአንድ ዲሞክራሳዊ አገር ዜጋ እንጂ ተገዥ
አይደለም፡፡ መንግስት የህዝብን መብት በሚያስጠብቅበት ወቅት ህዝብ ደግሞ በልዋጩ ለመንግስት ታማኝነቱን
ይገልፃል፤በጨቋኝ ሥርዓት ግን መንግስት ራሱን ከህዝብ በማግለል ታማኝነትን ከህዝብ ይሻል ፤መንግስት ውሳኔ
የሚወስነው ተገቢውን የህዝብ ድጋፍና ተሳትፎ ሳያገኝ ከሆነ የህዝብ ታማኝነት መመኘት ከንቱ ቅዠት ይሆናል፡፡ ›› (what
is democracy) ከሚለው መፃፍ የተወሰደ ነው፡፡
ጥላቻ ሁለተኛ ከባዱ የሰው ልጅ ስሜት ነው፤ፍቅር የመጀመሪያ ነው፡፡ ጥላቻ በፍራቻ በእውቀት ማነስና በተጠራጣሪነት
የሚመጣ ነው፡፡ ጥላቻ ይቅር ባይነትና መግባባትን ያሣጣል፡፡ ጥላቻ በቡድን፤ጥላቻ በግለሰብ እና ጥላቻ በማህበረሰብ
ውስጥ ሊከሰት ይችላል ውጤቱ ግን ከባድ ቀውስን ያስከትላል፤ለዚህም ይመስላል በሰማያዊ እና በአንድነት ፓርቲ
አማካኝነት በተካሄዱ የተቃውሞ ሠልፈኞቹ ላይ ሁሌም ፍቅር የሚሰበከው ፡፡በመሆኑም በተቃውሞ ሠልፎች ላይ
ፍቅርን፣ሠላምን፣አንድነትን እና ተስፋን ለሰበኩ ለሠላማዊ ታጋዬች ያለኝ አክብሮቴ የባዛ ነው፡፡
በአገራችን ለታየው ብልሹ የመንግስት አስተዳደር በተቃዋሚ ፓርቲዎች እየታየ ያለው እንቅስቃሴ አንድ ሰው ከእንቅልፉ
ተነስቶ ሁለት እጁን ከፍ አድርጎ ከመንጠራራት ጋር የሚዛመድ ነው፤ ይህን መንጠራራት ያልወደደዉ ሽብሩ መንግስታችን
እንቅስቃሴዎችን ለመግታትና ለማፈን የሚያደርገው ጥረት የፖለቲካው እንቅስቃሴ ውጥረት የበዛበት እንዲሆን አድርጎታል፡፡
በመሆኑም በማንቀላፋት ላይ ይገኝ የነበረው የተቃዋሚ ፓርቲዎች እንቅስቃሴ በእድሜ ለጋ የሆነው ሰማያዊ ፓርቲ አደባባይ
በመውጣት ህዝብን በማስተባበር ተቃውሞ ማሰማት መጀመሩን ተከትሎ በሌሎች ፓርቲዎች እየታየ ያለው መነቃቃትና
ተገቢ የሆነው ሥራ ለጨቋኙ መንግስታችን ፈታና ለህዝብ ደግሞ ተስፋ መሆኑ የማይካድ ሃቅ ነው፡፡ በዚህም መሠረት
የተቃዋሚ ፓርቲዎች ከመንጠራራት ባለፈ እራሳቸውን በጠንካራ መዋቅር በማደራጀት እና አባል በማብዛት፤ እንዲሁም
አማራጭ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊ እና ማህበራዊ ሠነዶችን በማዘጋጀት የህዝብ ሙሉ እምነትን እና ተሳትፎ ማዳበር
ይጠበቅባቸዋል፡፡ በተጨማሪ የተለያዩ ሠላማዊ የተቃውሞ እንቅስቃሴዎችን በማስተባበር መንግስትን ማስጨነቅ እና
ለህዝብ ጥያቄ ምላሽ እንዲሰጥ በማድረግ የሥርዓት ለውጥ እንዲመጣ ማድረግ ከተቃዋሚ ፓርቲዎቻችን የሚጠበቅ ተግብር
ነው፡፡
ስለ ተቃዋሚ ፓርቲዎቻችን እንስቃሴ ጅማሮ በበጎ ጎን የሚታይ እና የሚበረታታ መሆኑ ቅድሚያ የሚሰጠው ሲሆን፤
በተቃዋሚ ፓርቲዎች እየተደረጉ ያሉና ወደፊት የሚደረጉ የተቃዋሚ እንቅስቃሴዎችን ለመግታትና ለማፈን የሚወጡ
መመሪያዎችና ደንቦች እንዲሁም አዋጆች የህዝብን ድምፅ ለማፈን የተለመደው የገዥው ስርዓት የፈሪ ብትር መሆናቸው
የሚታወቅ ነው፡፡ በመሆኑም የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሰላማዊ ሠልፍና የአደባባይ ስብሰባ መሳወቂያ ክፍል አዲስ
መመሪያ ማውጣቱን በተለያየ የዜና ማሰራጨዎች ተሰምቷል፡፡መመሪያውን መስተዳደሩ በስራ ላያ እንደዋለውና ሰማያዊ እና
አንድነት ፓርቲ በዚህ መመሪያ መሠረት መስተናገዳቸውን አቶ ማርቆስ ብዙነህ የሰላማዊ ሠልፍና የአደባባይ ስብሰባ
መሳወቂያ ክፍል ለአዲስ ዘመን ጋዜጣና ለኢሳት በሰጡት አጭር መብራሪያ ገልጸዋል፡፡
ይሁን እንጂ በዓለም አቀፍ የተባበሩት መግስታት ድርጅት የሰብአዊ መብቶች ጉባሄ ባፀደቀው መግለጫ ኢትዮጵያም
በፈረመችው ስለ መሰብሰብ እና መደራጀት መብቶች የሚከተሉትን ብሏል ‹‹ የዜጎች የመሰብሰብ እና የመደራጀት መብቶች
ተግባራዊ ሂደት ገደብ በማይጣልበት ሁኔታ መከበር ሲኖርበት ነገር ግን ገደብ ቢደረግ እንኳን ገደቡ የዓለም ዓቀፍ ህግና
ሰብአዊ መብቶችን መሰረት ያደረገ እና የእነዚህን መብቶች ሁለንተናዊ ጥበቃ እዉን የሚያደርግ መሆን አለበት፤በተለይም
ዜጎች የፖለቲካ እና የአይማኖት ለማስከበር የሚያደርጓቸው ተቃውሞዎች መደገፍ አለባቸው፡፡ ››የሚል ሲሆን ፡፡
የኢፌዴሪ ህገ መንስት አንቀፅ 30 ንዑስ አንቀፅ 1 ማንኛውም ሰው ከሌሎች ጋር በመሆን መሣሪያ ሳይዞ በሰላም የመሰብሰብ
፣ሰላማዊ ሠልፍ የማድረግ ነፃነት እና አቤቱታ የማቅረብ መብት አለው፡፡ ከቤት ውጭ የሚደረጉ ስብሰባዎችና ሰላማዊ ሠልፎች በሚንቀሳቀሱባቸው ቦታዎች በሕዝብ እንቅስቃሴ ላይ ችግር እንዳይፈጥሩ ለማድረግ ወይም በመካሔድ ላይ ያለ
ስብሰባ ወይም ሰላማዊ ሰልፍ ሰላምን፣ዴሞክራሳዊ መብቶችንና የሕዝብን የሞራል ሁኔታ እንዳይጥሱ ለማስጠበቅ አግባብ
ያላቸው ስርዓቶች ሊደነገጉ ይችላሉ፡፡ በማለት ለህገ መንግስቱ አፈፃፀም ይረዳ ዘንድ ደንብና መመሪያ ሊወጣ እንደሚችል
የሚያመለክት ነው፡፡
ይሁን እንጂ ህገ መንግስቱ ከመፅደቁ በፊት በኢትዩጵያ ሽግግር መንገስት የተወካዮች ምክር ቤት ተጠባባቂነት የወጣ አዋጅ
ቁጥር 3/1983 ያለ ሲሆን ፤በወስጡ ተደንግገው የሚገኙ የህግ ማቀፎች ህገ መንግስቱን በግልፅ የሚቃረን ያለመሆኑ እንደ
በጎ ጎን ይታያል፡፡ ሆኖም ግን ዓለም አቀፍ የሰብአዊ እና የዲሞክራሲ መብቶችን እንዲሁም የኢፌዴሪ ህገ መንስት
ያስቀመጣቸው የዲሞክራሲ መብቶችን ከግምት ያስገባ አዋጅ አለመሆኑ ማሻሻያ እንደሚያስፈልገው የሚያመላክት ነው፡፡
ከላይ የተገለፁት የህግ ቅደም ተከተሎች ማለትም ዓለም አቀፍ ስምምነት ፣ የኢፌዴሪ ህገ መንስት እና አዋጅ ቁጥር 3/1983
በመሰብሰብ እና ሰላማዊ ሠልፍ በማድረግ መብት ላይ ተዘርዝረው የሚገኙ የህግ ድንጋጌዎች እጅግ በጣም ተቀባይነት
ያላቸው ናቸው፡፡ ነገር ግን ለዚህ አፈፃፀም ይረዳ ዘንድ ወጣ ስለተባው እና የአ/አ መስተዳደርም እየሰራውበት እገኛለው
ስለሚለው መመሪያ ህጋዊነቱ አጠራጣሪ ነው፤ በመሆኑም እነዚህን ማሳያዎች መመልከት በቂ ነው፡፡
1ኛ.የመመሪያው ድብቅነትና ህጋዊነት ፡- ‹‹ ሕግን አለማወቅ ከተጠያቂነት አያድንም ›› ተብሎ በደማቁ ተፅፎ የሚገኝው የህግ
ድንጋጌ አመላካችነቱ ማንም ሰው ህግን በማወቅም ይሁን ባለማወቅ ላጠፋው ጥፋት ተጠያቂ እንደሚሆን ነው፡፡ ስለዚህም
ተጠያቂነት የሚመነጨው ከህግ ነው ፤አንድ ህግ ደግሞ ህግ ነው ሊያስብለው የሚያስችለው የህግ አወጣጥ ስነ-ስርአቱን
ተከትሎ ሲሄድ ነው፡፡ በመሆኑም የአገራችን የህግ አወጣጥ ስነ-ስርአት ስንመለከት በቅድሚያ የሚፈለገው ህግ በህዝብ
ተወካዬች ምክር ቤት ወይንም በሚኒስትሮች ምክር ቤት ቀርቦ ሲፀድቅ እና በነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ሲወጣ ነው፡፡ ታትሞ
የወጣውን ህግ ማወቅ የሁሉም ሰው ግዴታ ነው ፤ ለዚህም ነው ‹‹ ሕግን አለማወቅ ከተጠያቂነት አያድንም ›› የተባለው፡፡
ስለዚህም የአ/አ ከተማ አስተዳደር ስለ ሰላማዊ ሠልፍና ሕዝባዊ የፖለቲካ ስብሰባ የወጣ መመሪያ አለኝ የሚለው ለህዝብ
ግልፅ አይደለም፡፡በመሆኑም አንድነት እና ሰማያዊ ፓርቲ የተስተናገዱት በመመሪያው መሠረት ነው ይባል እንጂ ፓርቲዎች
መመሪያውን ከየትኘውም ቦታ መግዛትም ሆነ መግኘት አልተቻላቸውም፡፡በተጨማሪ የሰላማዊ ሠልፍና የአደባባይ ስብሰባ
መሳወቂያ ክፍል አለኝ የሚለው መመሪያ ለፓርቲዎቹ ለማሳየትም ሆነ ለመግለፅ ፍቃደኛ አይደለም፡፡ ነገር ግን በቃል ብቻ
የማይታይ እና የማይነበብ መመሪያ አለኝ ከማለት ያለፈ መመሪያው የት እንዳለ የማይታወቅ ነው፡፡ ስለዚህም የመመሪያው
ድብቅነትን መነሻ በማድረግ በአገራችን የህግ አወጣት ስነ-ስርአት መሠረት መመሪያው ህግ ነው ብሎ ለመቀበል ይቸግራል፡፡
2ኛ. መመሪያዊ ከይት እንደመጣ አይታወቅም፡- የህግ ቅደም ተከተሎችን ስነመለከት አዋጅ፣ደንብ እና መመሪያ
ናቸው፡፡በመሆኑም በአወጅ ባልተሰጠ ስልጣን ደንብ ሊወጣ አይችልም እንደዚሁም በደንብ ላይ ባልተሰጠ ስልጣን መመሪያ
ሊወጣ አይችልም፡፡ በዚህም መሠረት በአዋጅ ቁጥር 3/1983 ታትሞ በወጣ ስለ ሰላማዊ ሰልፍና ሕዝባዊ የፖለቲካ ስብሰባ
ስነ-ስርአት አዋጅ ላይ ለአዋጁ ማስፈፀሚያ የሚረዳ ደንብና መመሪያ ማውጣት እንደሚቻል እና ማን ሊያወጣ እንደሚችል
የሚያመላክት ነገር የለም፡፡ ስለዚህም የአ/አ ከተማ አስተዳደር ስለ ሰላማዊ ሰልፍና ሕዝባዊ የፖለቲካ ስብሰባ ስነ-ስርአት
የወጣ መመሪያ አለኝ የሚለው በየትኛውም መመዘኛ የህግ አግባብነት የሌለው ነው፡፡ምክንያቱ ደግሞ በስራ ላይ ዋለ
የተባለው መመሪያ በህግ በተሰጠ ስልጣን መሠረት የወጣ መመሪያ አይደለም ስለዚህም መመሪያው ህጋዊነቱ አጠራጣሪ
ነው፡፡
3ኛ. መመሪያ ከህገ መንግስቱ በላይ አይደለም፡- ይህ ማለት መመሪያ በህግ ተደንግገው ለሚገኙ መብት እና ግዴታዎች
ማስፈፀሚያ የሚረዳ የአሰራር ስልት አመላካች ነው፡፡ በመሆኑም ከአዋጅ ቁጥር 3/1983 እንዲሁም ከህገ-መንግስቱ በላይ
መመሪያን መሠረት በማድረግ ሰላማዊ ሰልፍና ሕዝባዊ የፖለቲካ ስብሰባ የማድረግ መብት በመመሪያ ለመገደብ የሚስችል
ህጋዊ መሠረት የለም፡፡በህገ መንግስቱ አንቀጽ 9 ንዑስ አንቀጽ1 ማንኛውም ህግ፣ልማዳዊ አሰራር እንዲሁም የመንግስት
ባለስልጣን ወይም አካል ውሳኔ ከህገ መንግስቱ የሚቃረን ከሆነ ተፈፃሚነት አይኖረውም ሲል እንዲ አይነቱን በህግ ሰይሆን
በጉልበት እና በማንአለብኝነት የሚወጡ መመሪያዎችን ለመከላከል ወይም ውድቅ ለማድረግ ነው፡፡
በመሆኑም በህገ መንግስቱ የተቀመጡት ሰብአዊና ዲሞክራሳዊ መብቶች ለዜጎች ዋስትና የሚሆኑት በህግ አስፈፃሚው እና
በህግ ተርጓሚው በወረቀት ከመፃፍ በላፈ ተግባራዊ ሲደረግ ነው፡፡ በይበልጥ ደግሞ ህገ መንግስቱን መሠረት አድርገው ዜጎች ድጋፋቸውን እና ተቃውሟቸውን እንዲሁም ማህበራዊና ፖለቲካዊ ጉዳዬቻቸውን በገዛ አገራቸው ዋስትና አግኝተው
በነፃነት በመረጡት መንገድ ሃሳባቸውን ሲገልፁ ህገ መንግስቱ ተቀባይነቱ በዛው ልክ ይጨምራል፡፡
ይሁን እንጂ በአገራችን ባለው ነባራዊ ሁኔታ ህገ መንግስት እና ህዝብ ፊትና ጀርባ ሆኗዋል ለዚህም እንደማሳያ ብዙ
ምክንያቶችን ማቅረብ ይቻላል፤የሚቀርብ ምክንያቶች የአደባባይ ሚስጥር ከሆኑ ሰንብተዋል፡፡የነገሩ ሁኔታ በዚህ የሚቀጥል
ከሆነ ለህግ እና ለህጋዊ ሥርአት የሚኖረው አመለካከት ከመበላሸቱ በላፈ ያልተረጋጋ ምህበረሰብን ለመፍጠር ዋንኛ
ምክንያት ይሆናል፤ የዚህን ውጤት ደግሞ መገመት ቀላል ነው፡፡
ስለዚህም ከላይ የተገለፁትን መጠነኛ የህግ አመላካቾችን በመዳሰስ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሰላማዊ ሠልፍና
የአደባባይ ስብሰባ መሳወቂያ ክፍል አለኝ የሚለው መመሪያ ምንም አይነት ህጋዊነት መሠረት እንደሌለው የሚያመላክት
ነው፡፡ በመሆኑም ህዝብ በነቂስ ወጥቶ ድምፁን የሚያሰማበት መንገዶችን እና አደባባዬችን በህግ ወጥ መመሪያ እና በፖሊስ
ጉልበት መከልከል ይቻል ይሆናል ግን እስከመቼ …………. ??????፡፡
source ethiopian media forum .

Tuesday, October 8, 2013

የአማራ ክልል የድንበር ከተሞች ለአጎራባች ክልሎች ሊሰጡ ነው፡፡

መስከረም (ሃያ ስምንት)ቀን ፳፻፮ / ኢሳት ዜና :-ኢሳት ከአማራ ክልል ባለስልጣናት ባገኘው መረጃ  የጃን አሞራ፣ የማይጸብሪ አዋሳኝ፣ ራስዳሸንን ጨምሮ የአዲአርቃይን አካባቢዎች ወደ ትግራይ፣ በመተማ በኩል ደግሞ የተወሰነውን ክፍል ለቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ለመስጠት ድርድር በመካሄድ ላይ ነው።
ባለስልጣናቱ ቀደም ብለው የህዝቡን የልብ ትርታ ለማዳመጥ ጥረት ሲያደርጉ እንደነበር የደረሰን መረጃ የሚያመለክት ሲሆን፣ አንዳንድ የወረዳ ባላስልጣናት ጉዳዩን ወደ መድረክ እንድናወጣላቸው ተማጽነዋል።
መንግስት ከአሁን በፊት በአማራ ክልል ስር የነበረውን የመተከል ዞን ለቢኒሻንጉል ጉምዝ ፤ራያና ቆቦ ፤ዳንሻ እና ሁመራ ፤በመተማ በኩል ለሱዳን ፤የመተማ ቀሪው ክፍል ለቤንሻንጉል ፣ በሰሜን ሺዋ በኩል  ለኦሮምያ የልማት እገዛ በሚል መሰጠቱን በማውሳት ፣ አሁንም ተጨማሪ መሬት እየተቆረሰ ክልሎችን ለማስደሰት እየዋለ ነው በማለት ቅሬታቸውን ገልጸዋል።
የአንቀጽ 39 ቱርፈቶች የሰጡን ገፀ በረከቶች ናቸው ሲሉ የአማረሩት የድንበር ከተማ ነዋሪዎች፣  ”ጨለምተኛ አባት መሬት እየሸጠ ልጆቹን ከእርስት ይነቅላል፡፡ ጨለምተኛ መንግስት አገርን በመሸጥ ዜጎችን ያስደፍራል፡፤ ምንነታቸውን ያሳጣል መንግስትም ማንነታችን እየነጠቀን ነው ሲሉ” ገልጸዋል።
ሁኔታው ያበሳጫቸው ነዋሪዎች በአገር ውስጥና በውጭ የሚገኙ ድርጅቶች ጉዳዩን አጽንዎት ሰጥተው ሊያዩት ይገባል ብለዋል።
ከዚሁ ጋር በተያያዘ የትግርኛን ቋንቋ በአማራ ክልል ተማሪዎች እንዲማሩት ለማድረግ ታስቦ በጎንደር በተካሄደው የፓይለት ጥናት ህዝባዊ ተቃውሞ በማስነሳቱ እንዲቆም ተደርጓል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የቋንቋ ጥናት ባለሙያ የሆኑት ፕሮፌሰር ባየ ይማም በቅርቡ በአቀረቡት ጥናት የመንግስት ቋንቋ አጠቃቀም ‘የህዝብን ጉዳይ በህዝብ ቋንቋ’ የሚለውን መርህ የተከተለ ባለመሆኑ ህዝቡ ማግኘት ያለበትን መልእክት በትክክል እያገኘ፤ ለለውጥም እየተነሳሳ አይደለም ብለዋል፡፡ ባጭር ቃል በዚህ አይነት ቋንቋ የሕዝብን አእምሮ መቀየር እንደማይቻል የገለጹት ፕሮፌሰሩ፣ባለስልጣናቱ  የአማረኛ ቋንቋ እንዲጠፋ የበኩላቸውን እየተወጡ ነው ብለዋል፡፡
“ሀገራችን የቋንቋ ፖሊሲና የአጠቃቀም ደንብ ወይም ስርዓት እስካሁን የላትም፡፤ እስካሁን ድረስ ከህገመንግስታዊ የመብት ማረጋገጫ አንቀጾች ያለፈ፣ ቋንቋን እንደ ማንኛውም የሀገር ሀብት በእቅድ የሚያሳድግ፣ የሚቆጣጠር፣ አጠቃቀሙን ስርዓት የሚያሲዝ ፖሊሲና ዝርዝር ደንብ  የለንም፡፡ ባለመኖሩም ሁሉም እንደፈለገ የሚተረጉምበት፣ የሚጽፍበት፣ የሚያሰራጭበት ሁኔታ ውስጥ ገብተናል፡፡ ይህ ሊቆምና ቋንቋዎቻችን በዕቅድ ሊያድጉና ጥቅም ላይ ሊውሉ ይገባል” ሲሉ ፕሮፌሰሩ ተናግረዋል።
ፕሮፊሰር ባየ ይማም ለቋንቋው ድክመት  የመንግስት ባለስላጣናት ተጠያቂ መሆናቸውንም ገልጸዋል።
አማርኛ ቋንቋ የሀገሪቱ የስራ ቋንቋ መሆኑ እየታወቀ ክልሎች በፍፁም ጥላቻ እንዲያድርባቸው እንዲሁም  ክፍል ውስጥ ገብተው የመማርን መብት ለተወላጆች ብቻ ትቻለሁ በማለት የአማርኛ ትምህርት ክፍለ ጊዜዎች ፤ በትግራይ ፤ ኦሮምያ፤እና ደቡብ ልልኦች ክፍት ይሆናሉ።
ተማሪዎች በቋንቋ ትምህርት በሚመዱበበት ወቅትም በአማርኛ ቋንቋ የሚሰጡ ደጋፊ ትምህርቶችን ላለመማር አሰጣ አገባ እንደሚገቡ ታውቁዋል፡፡
በኦሮሚያ፣ በትግራይ፣ በቤንሻንጉል እና ሶማሊ ክልሎች የክልሎቹን ቋንቋ የማይናገሩ ተማሪዎች ተመርቀው ስራ ለማግኘት አይችሉም። በመሆኑም ከአማራ ክልል የሚመጡ ተማሪዎች ከክልላቸው፣ ከአዲስ አበባ እና ከደቡብ ክልል ውጭ በሌሎች ክልሎች ተቀጥረው ለመስራት እየተቸገሩ ነው።
አንዳንድ ልዩ ችሎታ ያላቸው ወይም መንግስታዊ ባልሆኑ ድርጅቶች ውስጥ ተቀጥረው ለመስራት ካልሆነ በስተቀር የአማራ ክልል ተማሪዎች ስራ ለመያዝ እንደሚቸገሩ ጉዳዩን በቅርበት የሚከታተሉ ሰዎች ገልጸዋል።
በሌላ በኩል ግን አማርኛ የሚችል የማንኛውም ክልል ተወላጅ በአማራ ክልል ተወዳድሮ ስራ የመያዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
አስተያየት ሰጪዎች እንደሚሉት በኢትዮጵያ ውስጥ እንደልብ ተዘዋውሮ የመስራት እና የመኖር መብት በእጅጉ ተገድቧል።

Monday, October 7, 2013

ሊበሏት የፈለጓትን አሞራ ይሏታል ጅግራ

ባለፈዉ ዐርብ መስከረም 25 ቀን 2006 ዓ.ም. የወያኔዉ ሎሌ ኃ/ማሪያም ደሳለኝ አዲስ አበባ ዉስጥ ለአገር ዉስጥና ለዉጭ አገር ጋዜጠኞች በሰጠዉ ጋዜጣዊ መግለጫ ተቃዋሚ ፓርቲዎች በየእሁዱ ለሚጠሩት ሰልፍ ጥበቃ ማድረግና በየእሁዱ ተመሳሳይ ጥያቄ ማድመጥ መንግስትን ከሚገባዉ በላይ ያሰለቸዉ ስለሆነ እነዚህ አንድ አይነት ጥያቄ ያነገቡ ሰልፎች የሚቀጥሉ ከሆነ የተቃዉሞ ሰልፍ ማድረግ ይከለከላል በማለት ጌቶቹና ዘረኞቹ የወያኔ መሪዎች የመብትና የነጻነት ጥያቄ የሚያነሳ ማንንም ሰዉ ለማሰር፤ ለመደብደብና ለመግደል ያላቸዉን እቅድ በግልጽ ተናግሯል። የሰላማዊ ሰልፍ ጥያቄ ባቀረቡ ቁጥር መሪዎቻቸዉ የሚታሰሩባቸዉ፤ አባላቶቻቸዉ የሚደበደቡባቸዉና ቢሯቸዉ ተሰብሮ ንብረታቸዉ የሚዘረፍባቸዉ የኢትዮጵያ ተቃዋሚ ድርጅቶች አንድም ቀን ሰለቸን ሳይሉ ደብዳቢዉ፤ አሳሪዉና የተቃዋሚ ድርጅቶችን ቢሮ እየሰበረ ንብረታቸዉን የሚዘርፈዉ ወያኔ ሰላማዊ ሰልፍ “ሰለቸኝ” ማለቱ ወያኔ ኢትዮጵያ ዉስጥ የሚደረግ ምንም አይነት ትግል የሱን የስልጣን “ዘለአለማዊነት” የሚጻረር መስሎ ከታየዉ ምንም ነገር ከማድረግ ወደ ኋላ የማይመለስ ፀረ ህዝብ ኃይል መሆኑን እንደገና አረጋግጧል።
ተቃዋሚ ፓርቲዎች ከዚህ ቀደም ቤት ውስጥ ሆነው ይጠይቁት የነበረውን ጥያቄ አሁን አደባባይ ወጥተዉ መጠየቅ መቻላቸዉ ዲሞክራሲያዊ ስኬት ነው ያለዉ ኃ/ማሪያም ደሳለኝ በሌላ በኩል ደግሞ ሰላማዊ ሰልፍ በችርቻሮ የሚሰጥ የወያኔ ችሮታ ይመስል ሰልፉ በየእሁዱ የሚቀጥል ከሆነ ሰልችቶናልና እንከለክላለን ማለቱ እንደ ግንቦት 7 እምነት ቀድሞዉንም ቢሆን ወያኔ ሰላማዊ ሠልፍ ማድረግ ይቻላል ብሎ ፈቃድ የሰጠዉ ለዲሞክራሲ ካለዉ እይታና እራሱ የጻፈዉን ህገ መንግስት ተከትሎ ሳይሆን እርዳታ ሰጪ ምዕራባዉያን አገሮችን ለማስደሰት ብቻ ነዉ።
አገር ዉስጥ የሚገኙ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ከቅርብ ግዜ ወዲህ የተቀናጀ ትግል ማድረግ በመጀመራቸዉ ክፉኛ የተደናገጠዉ ወያኔ “ሊበሏት የፈለጓትን አሞራ ይሏታል ጅግራ” አንደሚባለዉ እነዚህን ኢትዮጵያ ዉስጥ ፍትህ፤ እኩልነትና፤ ዲሞክራሲ እንዲሰፍን የሚታገሉትን ፍጹም ህዝባዊና ፍጹም ሰላማዊ የሆኑ ድርጅቶች ለማጥፋት ሰበብ ሲፈልግ የተለመደዉን ግንቦት 7 የሚል ዘፈኑን መዝፈን ጀምሯል። የወያኔ አገዛዝ በአፉ አንደሚናገረዉ ለኢትዮጵያ ህዝብ የሚያስብና የሚጨነቅ ከሆነ ማድረግ ያለበት ከኢትዮጵያ ህዝብ ለሚቀርብለት ጥያቄ ተገቢዉን ምላሽ መስጠት ብቻ ነዉ። አለዚያ ህዝብ ጥያቄ ባነሳና ለመብቱና ለነጻነቱ በታገለ ቁጥር የሐይማኖት አክራሪዎች፤ የቀድሞ ስርዐት ናፋቂዎች ወይም የግንቦት ሰባት ተከታዮች ናችሁ እያለ ቢያቅራራ እንዲህ አይነቱ የተለመደ የአምባገነኖች ቀረርቱ ያ የማይቀረዉ ክፉ ቀን ሲመጣ ስንቅ እንደማይሆነዉና ከህዝባዊ ቁጣ እንደማያድነዉ ከወዲሁ ሊገነዘብ ይገባል። ደግሞም ግንቦት 7 አላማዉ፤ ለህዝብ ያለዉ ክብርና ለኢትዮጵያ አንድነት ያለዉ ቀናኢነትና የማያወላዉል አቋም በኢትዮጵያ ህዝብ ዘንድ በአጭር ግዜ ዉስጥ ከፍተኛ ተወዳጅነትን አስገኝቶለታልና የወያኔን የዕለት በዕለት አስተዋዋቂነት በፍጹም አይሻም።
ግንቦት 7 አላማዉና ፍላጎቱ እንደ ስሙ ፍትህ፤ ነጻነትና ዲሞክራሲ ነዉና የህዝባዊ ትግላችን አላማ ወያኔንና ዘረኛ ስርዐቱን መደምሰስ ብቻ ሳይሆን አገራችን ዉስጥ የህግ የበላይነት ሰፍኖ ኢትዮጵያ ዛሬም ነገም ከሽብርተኝነት የነጻች አገር አንድትሆን ነዉና ወያኔ ያሰኘሰዉን ቢናገር ወይም እንዳሰኘዉ ቢፎክር ንቅናቄያችን ከዚህ ህዝባዊ አላማዉ ንቅንቅ እንደማይል ለወገንም ለጠላትም ማረጋገጥ ይፈልጋል። ግንቦት 7 የኢትዮጵያና የህዝቦቿ ዋነኛ ጠላት ወያኔ ነዉ ብሎ ያምናል፤ ስለሆነም የግንቦት ሰባት ህዝባዊ ክንድ ያነጣጠረዉ በዚሁ በዋነኛዉ የህዝብና የአገር ጠላት ላይ ብቻ እንደሆነ ኢትዮጵያዉያንና ለኢትዮጵያ ህዝብ ሰላምና ብልጽግና የሚመኙ ሁሉ እንዲገነዘቡለት ይፈልጋል።
ግንቦት 7 ህዝባዊ አላማ አንግቦ፤ ግብ አስቀምጦና ወዳስቀመጠዉ ህዝባዊ ግብ የሚያደርሰዉን የትግል ስልት በጥንቃቄ ነድፎ የሚንቀሳቀስ ህዝባዊ እንቅስቃሴ ነዉ። ግንቦት 7 ወያኔና ዘረኛ ስርዐቱ ተደምስሰዉ ኢትዮጵያ በዜጎቿ ሙሉ ፍላጎትና ፈቃድ ብቻ የምትመራ አገር የመሆኗ ሀቅ የማይቀርና ምንም አይነት ምድራዊ ኃይል ገድቦ ሊያቆመዉ የማይችል ህዝባዊ ማዕበል ነዉ ብሎ ያምናል። ግንቦት 7 በዚህ አጋጣሚ በየዋህነት ተሳስተዉና ግዜያዊ ጥቅም አታሏቸዉ ከሚንቋቸዉና እንደ ቤት ዉስጥ ዕቃ ከሚጠቀሙባቸዉ ዘረኞች ጋር እጅና ጓንት የሆኑ እንደ ኃ/ማሪያም ደሳለኝ አይነቶቹ የዋሆች የበደሉትን ህዝብ ይቅርታ ጠይቀዉ ህዝባዊ ትግሉን እንዲቀላቀሉ ወገናዊ ጥሪ ያቀርብላቸዋል። ከዚህ በተጨማሪ ግንቦት 7 ባለፉት ሁለት አመታት በተለይም ከወያኔዉ ቁንጮ ሞት በኋላ ከወያኔ ጋር ከፍተኛ ቅራኔ ዉስጥ የገባችሁ የኢህአዴግ አባል ድርጅቶችና በድርጅቶቹ ዉስጥ የምትገኙ የኢትዮጵያ ህዝብ ወገኖች ወያኔን ለማስወድ ከዛሬ የተሻለ ግዜ አይመጣምና ኑና በጋራ ጠላታችን ላይ እንዝመት የሚል ህዝባዊ ጥሪዉን ያስተላልፋል።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!

ታማኝ እና ቴዲ ትላንት ምሽት (ክንፉ አሰፋ)

                                           ክንፉ አሰፋ
 ትላንት ምሽት። እለተ እሁድ፤ ኦክቶበር 6፣ 2013። ታማኝ በየነ እና ቴዲ አፍሮ በስልክ ያወራሉ። ንግግራቸው
ከወትሮው የተለየ አልነበረም። እንደቀድሞው እየተቀላለዱ ይሳሳቃሉ። ታማኝ ከዴንቨር-ኮሎራዶ፣ ቴዲ ደግሞ ከሲድኒ-
አውስትራሊያ በስራ ላይ ነበሩ። በዚህ የሶስትዮሽ የስልክ ጨዋታ ላይ እኔና ጴጥሮስ አሸናፊም ገብተናል።
 ያን ሰሞን በኢትዮጵያ ድረ-ገጾች፣ በተለይ ደግሞ በፌስቡክ እና ሌሎች ማህበራዊ መድረኮች ላይ የውይይት ርእስ
ሆኖ ሰነበተ። የታማኝ እና የቴዲ ጉዳይ። በዚህ ዙርያ የነበረው ውይይት በወዳጆቻቸው ዘንድ በጥቂቱም ቢሆን ግርታ
መፍጠሩ አልቀረም። አንዳንዶች ለሁለቱም የጥበብ ሰዎች ካላቸው ፍቅርና አድናቆት ሲወያዩ ሰነበቱ። ሌሎች ደግሞ
ክስተቱን ወደ ሌላ አቅጣጫ ለመቀየር ሞከሩ። ጉዳዩ በእጅጉ አሳስቧቸው ለነገሩ እልባት ለመስጠት እንቅልፍ ያጡም ነበሩ።
 የትናንት ምሽቱ ውይይት ግርታውን እንደበረዶ አጠራው። በሁለቱ የጥበብ ሰዎች ዙሪያ ለሚነሳው ጥያቄዎ ምላሽ
ሰጠ። እናም ምንም አዲስ ነገር የለም እላችኋለሁ። ሁለቱም እንደድሯቸው ያወራሉ፣ ይቀላለዳሉ፣ ይሳሳቃሉ።
 ቴዲ በእርግጥም ቅን ነው። ታማኝም እንዲሁ። ሳያውቅ ለሚያጠፋው ጥፋት ይቅርታ ለማለት አይከብደውም።
ወረድ ብሎ፣ ዝቅ ብሎ፤ ታናሽ ወንድሙን ይቅርታ የሚጠይቅ ትልቅ ሰው ነው። ነገሩ እዚያም አልደረሰ። ልብ ለልብ
የሚተዋወቁ የዘመኑ ልጆች ነገሮችን አያካብዱም።
 ለምስክርነት ብጠራ እንዲህ እላለሁ። በእልህ ሳይሆን በፍቅር የሚያሸንፉ ምርጥ የኢትዮጵያ ልጆች፤ ሁለት ባለ
ራእዮች። ትውልድ አልፈው አንድን ህብረተሰብ የመለወጥ ትእንግርታዊ ስጦታ ያላቸው የዘመናችን እንቁዎች።...
 ታማኝ በየነ ለኢሳት ድጋፍ ለማሰባሰብ እስራኤል ሃገር ሄዶ ሲናገር “አምላኬ ሰው ስጠኝ በልኬ” የሚለውን የቴዲ
አፍሮ ስራ አንስቶ አንድ-ሁለት ማለቱ ነበር ውይይቱን የጫረው። በዚህ ጉዳይ ከታማኝ ጋር ብዙ አውርተናል። ታማኝ
ለማለት የፈለገው እና ሰዎች ለአባባሉ የሰጡት ትርጓሜ ግርግሩን እንደፈጠረው ለመረዳት ብዙ ጊዜ አልወሰደብኝም። ታማኝ
ቃል በቃል እንዲህ አለኝ። ቴዲን በቁመናው ለመተቸት ለመሆኑ እኔ ማን ነኝ?
 ለዚህ ትውልድ የተተወለት እርሾ እንዲህ አይነቱ የፍቅር እና የይቅርታ መንፈስ አልነበረም። ከዚያኛው ትውልድ
በጥበብና በፍቅር መኖርን አልወረስንም። በሃይል እና በእልህ ለማሸነፍ እንጥራለን። እናም አሸናፊዎች ሳይሆን ተሸናፊዎች
ሆነን ቀረን።
 መልካም ነገር ከታማኝ እና ከቴዲ ተማርኩ። ቅንነትና ራስን ዝቅ ማድረግ። በእርግጥ ሁለቱ በችግር እና በደስታ
ጊዜ ብዙ ነገሮችን ያሳለፉ የልብ ወዳጆች ናቸው። አንዱ ሌላውን ጠንቅቆ ያውቀዋል።
 "ፍቅር ያሸንፋል ከማለት በላይ የሚሆን ገላጭ ቃል የለኝም።" አለ ቴዲ በስልኩ ውይይት። ንግግሩ ልብ
ይሰብራል። አጥንት ሰርስሮም ይገባል።
 "ስህተት እንኳን ቢሆን አዲስ ነገር አይደለም። ሁላችንም እንሳሳታለን። ነገሮችን ማየት ያለብን ከዚያ አልፈን
ነው።" ቴዲ ጨመረበት።
 ታላቁ መጽሃፍ እንዲህ ይለናል። ፈጣሪ ንጉስ ሰለሞን ጠርቶ ምን ልስጥህ ሲል ጠየቀው። ንጉስ ሰለሞንም
"አምላኬ ሆይ ጥበብ እና ማስተዋልን ስጠኝ።" አለው። ጠቢቡ ሰለሞን ሃብትና ንብረትን አልጠየቀም፣ ሃይልና ጉልበትንም
አልተመኘም። እንዲህም ሆነ። እግዚአብሄር ለሰለሞን ማስተዋልና ጥበብን ሰጠው። ንጉስ ሰለሞንንም ሃያል ሆነ። በጥበብ!
 በጥበብና በፍቅር ህብረተሰብን መቀየር እንደሚቻል አስተዋልኩ። ይህ ደግሞ የሁለቱ የጥበብ ሰዎች የጋራ መድረሻ
ነው። እዚያ ላይ ለመድረስ የሚያስፈልገን ፍቅር ነው። ሁሉም ነገር ያልፋል። ፍቅር ያሸንፋል!
 እሁድ እንዲህ አለፈ። ከዚያ በኋላ ልክ እንደ ህጻን ልጅ ተኛሁ። ነገ ሌላ ቀን ነው።...
ምንጭ የኢትዮጵያ ሜዲያ መድረክ

Saturday, October 5, 2013

ከ3ሺህ በላይ የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የኢንጂነሪንግ ተማሪዎች ከግቢ ተባረሩ

       Written by  ናፍቆት ዮሴፍ
       በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የአራተኛ አመትና የሁሉም የምህንድስና ዘርፍ ተማሪዎች ከትላንት በስቲያ ከግቢ መባረራቸውን የአዲስ አድማስ ምንጮች ገለፁ፡፡ ለተማሪዎቹና ለዩኒቨርሲቲው ግጭት ምክንያት የሆነው የብቃት ማረጋገጫ ፈተና እንደሆነም ምንጮቹ ጠቅሰዋል፡፡ 
የሁሉም የምህንድስና ተማሪዎች አራተኛ አመት ላይ ሲደርሱ የብቃት ምዘና ፈተና ይወስዳሉ ያሉት ምንጮቹ፣ የዘንድሮው ተማሪዎች ግን ለእረፍት ወደየቤታቸው ሲሄዱ ሞጁል ይዘው ሄደው አጥንተው መፈተን ሲገባቸው፣ ድንገት ተፈተኑ መባላቸው እንዳስደነገጣቸው ገልፀዋል፡፡ 
“የሁለት ቀን ትምህርት ተሰጥቷችሁ ተፈተኑ መባላችን ትክክል አይደለም” ያለችው አንዲት የዩኒቨርስቲው ተማሪ፤ “ከእኛ በፊት የነበሩት የአራተኛ አመት ተማሪዎች ሳይፈተኑ “Holistic pass” (ምዘናውን እንዳለፉ የሚልጽ) ወረቀት እንደተሰጣቸው እናውቃለን” ብላለች፡፡ 
የብቃት ምዘና ፈተናው የሚጀምረው ካለፈው አመት ተማሪዎች እንደነበር የገለፀችው ተማሪዋ፤ ዘንድሮ ከእኛ መጀመሩ አግባብ አይደለም፣ ቢጀመርም ከልምምድ በኋላ እንዲሆን ጠይቀን ምላሽ አላገኘንም ብላለች፡፡ 
“እኛ አንፈተንም አላልንም ግን የሶስት አመት ትምህርት በሁለት ቀን ቲቶር ለፈተና አያበቃም” ያለው ሌላው ተማሪ፤ የፈተናው ጊዜ ይራዘምልን ብለው በመጠየቃቸው “ብትፈተኑ ተፈተኑ ያለበለዚያ ግቢውን ልቀቁ” ተብለው በፖሊስ ሃይል ከግቢ መባረራቸውን ገልጿል፡፡ በአሁኑ ሰዓት ከሶስት ሺህ በላይ ተማሪዎች ከግቢው እንደተባረሩና በአርባ ምንጭ ከተማ ሲቀበላ በተባለው አካባቢ በሚገኘው ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ግቢ ብዙ ተማሪ እንደሚገኝ የተናገረው የሲቪል ምህንድስና የአራተኛ ዓመት ተማሪ፤ ሌሎቹም በመስጊድና በየአስፓልቱ ላይ እየተንገላቱ እንደሆነ ገልጿል፡፡ 
“ያለ ምግብና ያለ መጠለያ በረሃብ ልናልቅ ነው” ያለው ሌላው ተማሪ፣ መንግስት በአስቸኳይ ለጉዳዩ እልባት ይስጥልን ሲል ተማጥኗል፡፡ ከአራተኛ አመት ተማሪዎች በተጨማሪ የአምስተኛ አመት የኤሌክትሪካል ኢንጂነሪንግ ተማሪዎችም መባረራቸውን የጠቀሰው ተማሪው፤ ሳናጠና እና ሞጁል ሳይዘጋጅ በሁለት ቀን የክፍል ጥናት ብቻ የሶስት አመት ትምህርት ተምረን ውጤት ልናመጣ ስለማንችል ባንፈተን ይሻላል የሚል አቋም መያዛቸውን ተናግሯል፡፡ 
“ዩኒቨርስቲው ሃላፊዎቹ የሚሏችሁን ሰምታችሁ ካልተፈተናችሁ ምንም አይነት አገልግሎት ከግቢው አታገኙም በሚል በፖሊስ ሃይል ተባረናል” ያለው ይሄው ተማሪ፤ ወደ ቤተሰብ ለመመለስም ሆነ እዛው ከተማ ውስጥ አልጋ ይዞን ለመቆየት ምንም ገንዘብ እንደሌላቸው ጠቁሞ በችግር ላይ መሆናቸውን ተናግሯል፡፡ ትላንትና ረፋድ ላይ በከተማው ፖሊስ ጣቢያ የመሰብሰቢያ አዳራሽ “ተሰብሰቡና እንነጋገር” የሚል ሃሳብ ከዩኒቨርሲቲው ሰዎች ቀርቦ ተማሪዎች አዳራሹን ሞልተው፣ ሃላፊዎቹን ለረጅም ሰዓት ቢጠባበቁም ማንም እንዳልመጣና በመጨረሻም ተማሪዎች መበታተናቸውን ምንጮች ገልፀዋል፡፡ 
በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ለምህንድስና ተቋሙ ፕሬዚዳንት ለዶ/ር ካሳሁን እና ለዩኒቨርስቲው የተማሪዎች አገልግሎት ዘርፍ ሃላፊ ለዶ/ር ተሾመ በተንቀሳቃሽ ስልካቸው ላይ በተደጋጋሚ ብንደውልም ስልካቸው ዝግ በመሆኑ ልናገኛው አልቻልንም በዩኒቨርስቲው የተለያዩ የቢሮ ስልኮች ደውለን ጉዳዩን ለማጣራት ያደረግነው ጥረትም ስልኮቹ ባለመነሳታቸው ሳይሳካ ቀርቷል፡፡
ምንጭ አዲስ አድማስ

ከ200 በላይ ስደተኞች አሁንም አልተገኙም

ከ200 በላይ ስደተኞች አሁንም አልተገኙም
መስከረም ፳፬(ሃያ አራት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ላምባዱሳ እየተባለ በሚጠራው የጣሊያን ደሴት አካባቢ በጀልባ መስጠም ከሞቱት መካከል የ11 ሰዎች አስከሬን ቢገኙም፣ ከ200 በላይ ሰዎች አሁንም የገቡበት አልታወቀም።
ፖፕ ፍራንሲስ በስፍራው ተገኝተው አደጋውን ከተመለከቱ በሁዋላ ሀዘናቸውን ገልጸዋል፣ ችግሩን ዝም ብለው የሚያዩትን አገራትም ወቅሰዋል።
ብዙ የጣሊያን ባለስልጣናት የህጻናቱን አስከሬን እያዩ ስሜታቸውን መቆጣጠር ተስኖአቸው ሲያለቅሱ ታይቷል።
እስካሁን ድረስ አስከሬናቸው የተሰበሰበውና የጠፉት ሰዎች ዜግነት በውል ተለይቶ አልታወቀም። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስደተኞች ኮሚሽነር አብዛኞቹ ኤርትራውያንና ሶማሊዎች ናቸው ብሎአል።
እንዲህ አይነት አሰቃቂ አደጋ ሲደርስ ይህ የመጀመሪያው ነውም ተብሎአል።