Saturday, October 5, 2013

ከ200 በላይ ስደተኞች አሁንም አልተገኙም

ከ200 በላይ ስደተኞች አሁንም አልተገኙም
መስከረም ፳፬(ሃያ አራት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ላምባዱሳ እየተባለ በሚጠራው የጣሊያን ደሴት አካባቢ በጀልባ መስጠም ከሞቱት መካከል የ11 ሰዎች አስከሬን ቢገኙም፣ ከ200 በላይ ሰዎች አሁንም የገቡበት አልታወቀም።
ፖፕ ፍራንሲስ በስፍራው ተገኝተው አደጋውን ከተመለከቱ በሁዋላ ሀዘናቸውን ገልጸዋል፣ ችግሩን ዝም ብለው የሚያዩትን አገራትም ወቅሰዋል።
ብዙ የጣሊያን ባለስልጣናት የህጻናቱን አስከሬን እያዩ ስሜታቸውን መቆጣጠር ተስኖአቸው ሲያለቅሱ ታይቷል።
እስካሁን ድረስ አስከሬናቸው የተሰበሰበውና የጠፉት ሰዎች ዜግነት በውል ተለይቶ አልታወቀም። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስደተኞች ኮሚሽነር አብዛኞቹ ኤርትራውያንና ሶማሊዎች ናቸው ብሎአል።
እንዲህ አይነት አሰቃቂ አደጋ ሲደርስ ይህ የመጀመሪያው ነውም ተብሎአል።

No comments:

Post a Comment