Saturday, July 13, 2013

የነገው ጎንደር እና የደሴው ሰላማዊ ሰልፍ ቅስቀሳ ተጠናክሮ ቀጥሏል

በደሴ ከተማ በትናንትናው ዕለት ሐምሌ 5 ቀን 2005ዓ.ም. የአንድነት ፓርቲ ሐምሌ 7 ቀን 2005ዓ.ም. ጠዋት ከአራዳ የፓርቲው የደቡብ ወሎ ዞን ጽህፈት ቤት ለሚጀምረው ሰላማዊ ሰልፍ ፓርቲው ከፍተኛ አመራሮች አቶ ግርማ ሰይፉ፣ አቶ በላይ ፈቃዱ፣ አቶ ዳንኤል ተፈራ፣አቶ ፍቃዱ ሰጠኝ ከአዲስ አበባ፤ አቶ ብስራት አቢ፣ አቶ መኳንንት፣ አቶ አንዋር፣ አቶ ከበደ፣ አቶ ሰይድ እና ሌሎች አንድነት ፓርቲ የደሴ ነዋሪዎች በራሪ ወረቀት ሲበትኑ በአማራ ክልል ልዩ ፖሊስና በአድማ በታኝ እንዲያቆሙ በማድረግ ወደ ፖሊስ ጣቢያ ወስደዋቸው ነበር፡፡

በወቅቱም ከአንድ ካሜራ ባለሙያ ባልደረባዬ ጋር ለቅስቀሳ የወጡት የአንድነት ፓርቲ የደቡብ ወሎ ዞን ኃላፊዎች አቶ ብስራት አቢ፣አቶ መኳንንት፣ አቶ ሰይድ እና አቶ አንዋር በክልሉ ፖሊስ ወደ ተወሰዱበት ደሴ 1ኛ ፖሊስ ጣቢያ ሄደን ስለጉዳዩ ስንጠይቃቸው ፖሊሶቹ እኛ አላሰርናቸውም፣ ነግር ግን ከበላይ አካል ቅስቀሳውን አስቁሙ ብለው ትዕዛዝ ሰጥተውን ነው፤ ለዚህም ልናናግራቸው እንጂ ልናስረዳቸው አይደለም ሲሉ ምላሽ ሰጥተውናል፡፡ እኛም ያዘዛችሁ የበላይ አካል ማን ነው? የፀጥታው ዘርፍ ኃላፊ አቶ ሙሉጌታ በላይን ስንጠይቃቸው እኮ እኛ አልከለከልንም፣ ከልክሉም አላልንም፣ የሚከለክልም የለም ብለውናል፣ እናንተስ በምን የህግ አግባብ ነው ቅስቀሳውን የምትከለክሉት ስል ጥያቄ አቅርቤላቸው ነበር፡፡

ፖሊሶቹ በበኩላቸው ያዘዘንን አካል ማንነት መግለፅ አንፈልግም፣ ይሄ እኮ ምስጢር ነው፣ ከፈለጋችሁ የከተማው ፖሊስ መምሪያ ጠይቁ ሲሉ ምላሽ ከሰጡ በኋላ የያዟቸውን የአንድነት ፓርቲ አመራሮች ለቀዋቸዋል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ የፓርቲው አመራሮችና አባላት ለነገ ሐምሌ 7ቱ ህዝባዊ ሰላማዊ ሰልፍ ዛሬ ቅዳሜም በራሪ ወረቀቶችን በመበተንና ፖስተር በመለጠፍ የቅስቀሳ ስራ እያደረጉ እንደሚገኙ ለማይት ችለናል፡፡

በተመሳሳይ ዜና በሰሜን ጎንደር ዞን ጎንደር ከተማ ነገ እሁድ ሐምሌ 7 ቀን 2005ዓ.ም. ለሚደረገው ተመሳሳይ ሰላማዊ ሰልፍ ከአዲስ አበባ የሄዱት የአንድነት ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች አቶ አስራት ጣሴ፣ አቶ ዘካርያስ የማነብርሃን፣አቶ አበበ አካሉ፣አቶ ሀብታሙ አያሌው፤ እንዲሁም የሰሜ ጎንደር ዞን የአንድነት ፓርቲ አመራሮች አቶ አለላቸው አታለል፣ አቶ ጀማል አብደላ፣ አቶ አማረ ስጦታውና የቀጠናው ኃላፊ አቶ አእምሮ አወቀን ጨምሮ አባላቱና ደጋፊዎች የቅስቀሳ ስራ እንዳያደርጉ በፖሊስ ተከበው እየተከለከሉ የነበረ ቢሆንም በመጨረሻ ዛሬ ተፈቅዶላቸው የፓርቲው ሰዎች ቅስቀሳውን አጠናክረው መቀጠላቸው ታውቋል፡፡ እዛው ጎንደር በትናንትናው ዕለት ከአዲስ አበባ ለመረጃ ስራ የተላኩት የፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ ባልደረባ አቶ ወንደሰወሰን ክንፈ እንቅስቃሴውን ሲቀርፁበት የነበረውን ካሜራ ከተማው ፖሊሶች ነጥቀው ክስ መመስረቱ ይታወቃል፡፡

በሁለቱም በጎንደርና በደሴ ከተማ ነገ እሁስ ሐምሌ 7 ቀን 2005ዓ.ም. ከጠዋቱ 3 ሰዓት የሚደረገውን ህዝባዊ ሰላማዊ ሰልፍ ለመዘገብ ፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ እና የኢትዮጵያ ቴሌቪዥንን ጨምሮ የተለያዩ የሀገር ውስጥና ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙኃን መግባታቸውን ለማየት ችለናል፡፡ የሁለቱም የደሴና የጎንደር ከተማ ነዋሪዎች ሰላማዊ ሰልፉን ለመውጣት እንደተዘጋጁ እየገለፁ ሲሆን መንግስት ሰልፉን ልከልክል ቢል እንኳ ወደ ሰላማዊ ሰልፉ ከመውጣት ወደ ኋላ እንደማይሉ ያነጋገርኳቸው አንዳድ የከተማው ነዋሪዎች አረጋግጠውልኛል፡፡የነገው ጎንደር እና የደሴው ሰላማዊ ሰልፍ ቅስቀሳ ተጠናክሮ ቀጥሏል

በደሴ ከተማ በትናንትናው ዕለት ሐምሌ 5 ቀን 2005ዓ.ም. የአንድነት ፓርቲ ሐምሌ 7 ቀን 2005ዓ.ም. ጠዋት ከአራዳ የፓርቲው የደቡብ ወሎ ዞን ጽህፈት ቤት ለሚጀምረው ሰላማዊ ሰልፍ ፓርቲው ከፍተኛ አመራሮች አቶ ግርማ ሰይፉ፣ አቶ በላይ ፈቃዱ፣ አቶ ዳንኤል ተፈራ፣አቶ ፍቃዱ ሰጠኝ ከአዲስ አበባ፤ አቶ ብስራት አቢ፣ አቶ መኳንንት፣ አቶ አንዋር፣ አቶ ከበደ፣ አቶ ሰይድ እና ሌሎች አንድነት ፓርቲ የደሴ ነዋሪዎች በራሪ ወረቀት ሲበትኑ በአማራ ክልል ልዩ ፖሊስና በአድማ በታኝ እንዲያቆሙ በማድረግ ወደ ፖሊስ ጣቢያ ወስደዋቸው ነበር፡፡

በወቅቱም ከአንድ ካሜራ ባለሙያ ባልደረባዬ ጋር ለቅስቀሳ የወጡት የአንድነት ፓርቲ የደቡብ ወሎ ዞን ኃላፊዎች አቶ ብስራት አቢ፣አቶ መኳንንት፣ አቶ ሰይድ እና አቶ አንዋር በክልሉ ፖሊስ ወደ ተወሰዱበት ደሴ 1ኛ ፖሊስ ጣቢያ ሄደን ስለጉዳዩ ስንጠይቃቸው ፖሊሶቹ እኛ አላሰርናቸውም፣ ነግር ግን ከበላይ አካል ቅስቀሳውን አስቁሙ ብለው ትዕዛዝ ሰጥተውን ነው፤ ለዚህም ልናናግራቸው እንጂ ልናስረዳቸው አይደለም ሲሉ ምላሽ ሰጥተውናል፡፡ እኛም ያዘዛችሁ የበላይ አካል ማን ነው? የፀጥታው ዘርፍ ኃላፊ አቶ ሙሉጌታ በላይን ስንጠይቃቸው እኮ እኛ አልከለከልንም፣ ከልክሉም አላልንም፣ የሚከለክልም የለም ብለውናል፣ እናንተስ በምን የህግ አግባብ ነው ቅስቀሳውን የምትከለክሉት ስል ጥያቄ አቅርቤላቸው ነበር፡፡

ፖሊሶቹ በበኩላቸው ያዘዘንን አካል ማንነት መግለፅ አንፈልግም፣ ይሄ እኮ ምስጢር ነው፣ ከፈለጋችሁ የከተማው ፖሊስ መምሪያ ጠይቁ ሲሉ ምላሽ ከሰጡ በኋላ የያዟቸውን የአንድነት ፓርቲ አመራሮች ለቀዋቸዋል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ የፓርቲው አመራሮችና አባላት ለነገ ሐምሌ 7ቱ ህዝባዊ ሰላማዊ ሰልፍ ዛሬ ቅዳሜም በራሪ ወረቀቶችን በመበተንና ፖስተር በመለጠፍ የቅስቀሳ ስራ እያደረጉ እንደሚገኙ ለማይት ችለናል፡፡

በተመሳሳይ ዜና በሰሜን ጎንደር ዞን ጎንደር ከተማ ነገ እሁድ ሐምሌ 7 ቀን 2005ዓ.ም. ለሚደረገው ተመሳሳይ ሰላማዊ ሰልፍ ከአዲስ አበባ የሄዱት የአንድነት ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች አቶ አስራት ጣሴ፣ አቶ ዘካርያስ የማነብርሃን፣አቶ አበበ አካሉ፣አቶ ሀብታሙ አያሌው፤ እንዲሁም የሰሜ ጎንደር ዞን የአንድነት ፓርቲ አመራሮች አቶ አለላቸው አታለል፣ አቶ ጀማል አብደላ፣ አቶ አማረ ስጦታውና የቀጠናው ኃላፊ አቶ አእምሮ አወቀን ጨምሮ አባላቱና ደጋፊዎች የቅስቀሳ ስራ እንዳያደርጉ በፖሊስ ተከበው እየተከለከሉ የነበረ ቢሆንም በመጨረሻ ዛሬ ተፈቅዶላቸው የፓርቲው ሰዎች ቅስቀሳውን አጠናክረው መቀጠላቸው ታውቋል፡፡ እዛው ጎንደር በትናንትናው ዕለት ከአዲስ አበባ ለመረጃ ስራ የተላኩት የፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ ባልደረባ አቶ ወንደሰወሰን ክንፈ እንቅስቃሴውን ሲቀርፁበት የነበረውን ካሜራ ከተማው ፖሊሶች ነጥቀው ክስ መመስረቱ ይታወቃል፡፡

በሁለቱም በጎንደርና በደሴ ከተማ ነገ እሁስ ሐምሌ 7 ቀን 2005ዓ.ም. ከጠዋቱ 3 ሰዓት የሚደረገውን ህዝባዊ ሰላማዊ ሰልፍ ለመዘገብ ፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ እና የኢትዮጵያ ቴሌቪዥንን ጨምሮ የተለያዩ የሀገር ውስጥና ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙኃን መግባታቸውን ለማየት ችለናል፡፡ የሁለቱም የደሴና የጎንደር ከተማ ነዋሪዎች ሰላማዊ ሰልፉን ለመውጣት እንደተዘጋጁ እየገለፁ ሲሆን መንግስት ሰልፉን ልከልክል ቢል እንኳ ወደ ሰላማዊ ሰልፉ ከመውጣት ወደ ኋላ እንደማይሉ ያነጋገርኳቸው አንዳድ የከተማው ነዋሪዎች አረጋግጠውልኛል፡፡(ምንጭ ፍኖተ ነፃነት አዲስ አበባ ጁላይ 13,2013)

No comments:

Post a Comment