Wednesday, February 26, 2014

የኢትዮጵያ ሴቶች ጉዳይ ሚ/ር ዘነቡ ታደሰ ዩጋንዳ የጸረ ጌይ ሕግ ማውጣቷን ተቹ

(ዘ-ሐበሻ) ኢትዮጵያ የሴቶች ጉዳይ ሚኒስትር የሆኑት ዘነቡ ታደሰ ኡጋንዳ የጸረ ጌይ አዋጅ ማውጣቷን መተቸታቸውን ሃፊንግተን ፖስት የተባለው ጋዜጣ ሚኒስትሯ በትዉተር ገጻቸው የጻፉትን አስተያየት አያይዞ ባቀረበው ዘገባው አስታወቀ። እናት ድርጅታቸው ኢሕአዴግ ከዚህ ቀደም በኢትዮጵያ የአፍሪካ ጊዮች ስብስባ እንዲደረግ መፍቀዱና በጁፒተር ሆቴል ይደረጋል በተባለው በዚህ ስብሰባ ከፍተኛ ተቃውሞ መነሳቱ ይታወሳል።
በትዊተር ገጻቸው ዘነቡ ታደሰ ኡጋንዳ የጸረ ጌይ (ጸረ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን) አዋጅን ካጽደገቀች በኋላ በእንግሊዘኛው There is no place for hate, discrimination in my beloved Africa. It’s not Governments’ business to make dress code or anti-gay laws #Uganda.” ብለው ጽፈዋል ያለው ሃፊንግተን ፖስት የኡጋንዳን መንግስት ሕጉን በማጽደቁ ተችተዋል ብሏል።
“ስለአለባበስም ሆነ የጸረ ጌይ ሕግ ማውጣት የመንግስት ጉዳይ መሆን የለበትም” በሚል የተናገሩት የኢትዮጵያ የሴቶች ጉዳይ ሚኒስተር ዘነቡ ታደሰ የጌይን ሕግ መጽደቅ ይደግፋሉ በሚል መነጋጋሪያ ሆነዋል።
ዘነቡ ታደሰ በትዊተር ገጻቸው የጻፉት የሚከተለው ነው፦
source Ze -Habesha

No comments:

Post a Comment