Monday, February 3, 2014

''ከዚህ በኋላ ስለጀግኖቹ ንጉሶች እየዘፈኑ መኖር ያብቃ፤ ታሪካቸውም እኛም በጀግንነታችን እንጠብቀው'' - የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር በጎንደር

(ምንሊክ ሳልሳዊ በጎንደር የተካሄደውን ህዝባዊ ስብሰባ እንዳለ ተጀምሮ እስኪያልቅ እንዳስቀመጠው አቅርበነዋል)


በጎንደር ከተማ የተካሄደው ሰላማዊ ሰልፍ ህብረተሰቡ
የአካባቢው አስተዳዳሪዎችን ማስፈራሪያ እና ጥርነፋ
ተቋቁሞ የወጣ ሲሆን ቅዳሜ እለት በተሳካ ሁኔታ
ተካሄዷል፡፡ በጎንደር መስቀል አደባባይ በርካታ የከተማው
ነዋሪዎች የወጡ ሲሆን ሀገራዊ ዜማዎችንና መፈክሮችን
አሰምተዋል።

ተጠብቆ የቆየው ባባቶቻችን ደም
እናት ኢትዮጵያ ያስደፈረሽ ይውደም

ሉዓላዊነታችንን አናስደፍርም
አባቶቻችን ያስረከቡንን መሬት አሳልፈን አንሰጥም
ወያኔ አምባገነን ነው ወደሚለው መፈክር ተገብቷል

ወያኔ አይወክለንም ከፍ ባለ ድምፅ እየተስተጋባ ይገኛል መስቀል አደባባይ በዝማሬ የታጀበ መፈክር እየተሰማ ነው


የሰማያዊ ፓርቲ አስተባባሪ ለህብረተሰቡ በዚህ አስቸጋሪ ወቅትና አምባገንን ስርዓት ውስጥ ሆናችሁ የሀገራችን ጉዳይ ያገባናል ብላችሁ
ስለመጣችሁ እናመሰግናለን በሚል ንግግር ፕሮግራሙን ከፍተው የሰልፉን አላማ አብራርተው የፓርቲውን ሊቀመንበር ወደ መድረክ
ጋብዘዋል፡፡ የፓርቲው ሊቀመንበርም ለተሰላፊዎቹ ባስተላላፉት መልእክት ለወጣቶች የሀገራቸውን ክብር እንዲያስጠብቁ እራሳቸውንም
ከፍርሀት እና ከስጋት በማላቀቅ ለራሳቸውም ለሀገራቸውም አለኝታ እንዲሆኑ፤ እንዲሁም ስርዓቱ ላይ ያሉት አስተዳደሮች ስልጣን
ወቅታዊ መሆኑን አውቀው በኢትዮጵያ ድንበር ላይ እየተፈጸመ ያለውን ደባ እንዲያስቆሙ ከታሪክ ተጠያቂነት እንዲድኑ፤
ለልጆቻቸውም ውርደትን ሳይሆን ክብርን እንዲያወርሱ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ ፓርቲውም የጠራውን ሰልፍ እና ማስተላለፍ የፈለገውን
መልእክት በተሳካ ሁኔታ አስተላልፎ ፕሮግራሙን አጠናቋል፡፡ ፓርቲውም በአካባቢው የሚገኙ የፓርቲው አስተባባሪዎችን እንዲሁ
የጎንደር እና የአካባቢው ህዝብን ለዚህ ሰልፍ መሳካት ላደረጉት አስተዋጽኦ ከፍ ያለ ምስጋና አቅርቧል፡፡

የጎንደሩ የተቃውሞ ሰልፍ ሲጠናቀቅ ህዝቡ በመሬቱ ቀልድ እንደማያውቅ በአደባባይ አስረግጦ አሳውቋል። የሰማያዊ ፓርቲ
ሊቀመንበር ኢንጅነር ይልቃል ጌትነት ''ከዚህ በኋላ ስለጀግኖቹ ንጉሶች እየዘፈኑ መኖር ያብቃ ታሪካቸውም እኛም በጀግንነታችን
እንጠብቀው'' ብለዋል። በስልክ ያናገርኳት አንዲት የጎንደር ወጣት አሁን ገና በአይናችን መጡብን ብላኛለች። ለሱዳን ሊሰጥ ነው
የሚለው ወሬ ከተሰማ ወዲህ ኢትዮጵያውያን በሀገር ቤት ድምጻቸውን ሲያሰሙ የጎንደሩ የመጀመሪያው ነው።

ጎንደር ላይ የተካሄደው ሰልፍ ባማረ መልኩ ተጠናቀቀ ለሰልፉ መሳካት ትልቅ ሚና ለተጫወቱት የጎንደር ወጣቶች፣ የሰማያዊ ፓርቲ
አመራሮች እና አባላት እንዲሁም በማህበራዊ ድህረ ገፆች ህዝቡን በመቀስቀስ እና መረጃ በማስተላለፍ ሰልፉ እንዲሳካ ላደረጉት
በሙሉ ከፍ ያለ ምስጋና ይገባቸዋል።

የኢትዮጵያ ትንሣኤ እየቀረበ ነው!!
እምዬ ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር!!







ኢትዮሚድያ - Ethiomedia.com
February 2, 2014

No comments:

Post a Comment