Thursday, November 28, 2013

“ሁከት ፈጠሩ” የተባሉት የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ጉዳይ ፍ/ቤት ቀረበ

(አራያ ጌታቸው) ዛሬ ህዳር 18 ቀን 2006 ዓ.ም ከላይ ባለው የክስ መጥሪያ የሰማያዊ ፓርቲ የምክር ቤት ሰብሳቢ አቶ የሽዋስ አሰፋ እና የሰማያዊ ፓርቲ የምክር ቤት አባል አቶ ስሜነህ ጸሀይ አዲስ አበባ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ወንጀል ችሎት ቀርበው፤ አቃቤ ህግ ወንጀሉን ከዘረዘሩ በኋላ ፍርድ ቤቱም ጥፋተኝነታቸውን ያምኑ ወይም ይቃወሙ እንደሆነ ጠይቆ ተከሳሾቹም ምንም አይነት ጥፋት እንዳለጠፉ ገልጸዋል፡፡ ፍርድ ቤቱ የምስክሮችን ቃል ለመስማት ለህዳር 26 ቀን 2006 ዓ.ም. ቀጠሮ ሰጥቶ አሰናብቷቸዋል፡፡
የክሱን ዝርዝር እንዲያነቡት ከዚህ ዜና ጋር አቅርበነዋል።                                                 ምንጭ የኢትዮጵያ ሜዲያ መድረክ

No comments:

Post a Comment