Thursday, May 29, 2014

ግንቦት 20 ስናስበው!!!!!

  ዳዊት ወንድሙ
 በአብዛኞቻችን ኢትዮጵያን ዘንድ ላንረሳው ልንዘነጋው የማይቻሉ በርካታ ክስተቶች አልፈዋል ወያኔ እስልጣን ዙፋን ላይ
ከተቀመጡበት ግዜ ጀምሮ ህዝብን በእስራት፣ለስደት፣ለረሀብ ከዛም አልፎ በመግደል በማሰቃየት በብሄር እና በጎሳ፣በመንደር
በማደራጀት በመከፋፈል ሌሎችም ያልገለፅኳቸው በርካታ መጠነ ሰፊ ችግሮችን አይተናል ።
   ሁሌም ከህሊናችን ከአእምሮችን የማንረሳው ውድ ወንድማችን በደቡብ ክልል ዳውሮ ዞን የኔሰው ገብሬ  በሙያው መምህር የነበር እሱን
የመሰሉ ብዙ ኢትዮጵያን በእውቀት የሚያፈራ የነበር የህዝቦችን ስቃይ ፍትህና ህግ በተግባር በማይታይበት በማይወሰንበት
ሀገር ከመኖር ይልቅ እራሴን በእሳት አቃጥዬ በሞት ይሻለኛል ብሎ እራሱን ለፍትህ ለነፃነት ብሎ የሰዋው እኔ እራሴን
በመሰዋት ያቀጣጠልኩትን ትገል እዳር እና እውጤት አድርሱ ብሎ  ለኛትቶ አልፏል።
   እንደው እንደምሳሌ አድርጌ የኔሰው ገብሬን ጠቀስኩ እንጂ በወያኔ ስርዓት ስንቱን በዝርዝር ገልፆ መጨረስ አይቻልም
ከሁሉም በላይ ደግሞ ልንረሳው የማንችለው በወያኔ ኣጋዚን አልሞ ተኳሽ በምርጫ 1997 በሰላማዊ መንገድ የተሰረቀው
ድምፃችን ይመለስ በማለት በ አዲስ አበባ በተለያዩ ቦታዎች የተቃውሞ ድምፁን ያስማ የነበረውን ህዝብ ምንም እራሱን የሚከላከልበት
እንኳን ምንም አይነት መሳሪያ የሌለው ሰላማዊና ፍት ህ ፈላጊ ባደባባይ ድምጹን ለማሰማት የወጣውን ህዝብ በ አጠፋው
በምላሹ የጥይት እሩምታ ፍጹም በራስ ወገን ሊደርግ አይደለም ሊታስብ የማይገባውን ፋሽስታዊ ጭካኔ በገዛወገናቸው ላይ
ፈፅመዋል በዚህ ምክንያት መቼም ማንረሳቸው ዘውትር ምንዘክራቸው 200 ወግኖቻችን አጥተናል በሁላችን ልብ ዘወትር
የሚያስለቅሰን እንደ አብሮ አደግ ጓዶኞቹ በሰላም ወደትምህርት ቤት ደብተሩን እንደያዘ እናቱን ስሞ ልጄ በሰላም ተመለስ
በላ መርቃ ልጄ ተምሮ አድጎ እራሱን እኔንም ከዛም አልፎ አገሩን ወገኑን የጠቅማል ብላ እናት ስለልጆ የወደፊት ብሩ ተስፋ
እያለመች እና እያሰበች ሽኘችው ይህ ሁሉ ሳይሆን ቀርቶ በወያኔ ኣጋዚን እናት እንዳሰበችው ሳይሆን በነሱ ጥይት ህፃን ነብዩ
ደብተሩን እንደያዘ ተዘርሮ ከመንገድ ባጭሩ ቀርቶል መግደላቸው ሳያንሳቸው የ 12(14) ዓመት ህፃን ባንክ ሊዘርፍ ሲል ነው
የተገደለው በማለት የአለምን ህዝብ  ለሚዲያ ለማሳሳት ሞክርዋል እንኳን ባንክ ሊዘርፍ ቀርቶ የባንክ ቤትን በር መግቢያ
የማያቅ ልጅ እንዲሁ የትምህርት ደፈተሩን እንደያዘ ከአስፋልት ተዘርሮ ቀርቶል።
   እህታችን ሽብሬንም አንረሳትም አረስንቱን እንዘርዝር ቤት ይቁጠረው አንጂ።
       ግንቦት 20 ስናስበው ምናልባት የትወሰኑ ክፍሎች፣ቡድኖች፣ግለሰቦች የነፃነት ቀናችን ብለው ሊያስቡ ወይም ሊደሰቱ
ይችሉ ይሆናል እነሱም እንደሚሉት ልማታዊ መንግስት 11% ኢኮነሚያችን አደገ የህዝባችን የኑሮ ሁኔታ ተሻሸሎል ማይቀበጣጥሮት የለም እውነተውና ሀቁ እሱ አይደልም ከ አንደነት የልቅ በጎጥ መነፅር የምንተያይበት በተለያዩ አግሮች
በመሰደድ መከራና ስቃይ በተለይም በየ አረብ ሀገር የእህቶቻችን የወንድሞቻችን መከራና ስቃይ ሞት የምንሰማበት የምናይበት እንዲሁም በታሪካችን ተስምቶ ያማይታውቅ ብሔራዊ ውርደታችን ያየንበት ነው።
 
አባቶቻችን እናቶቻችን ለአገራቸውና ለባንዲራቸው ክብር ብለው የሞቱለትን ታሪክ ዛሬ እረስተን በጠላትና በወራሪዎች
አንገዛም አንበርከክም ብለው ለመላው የጥቁር ህዝብ ነፃነትን ጎሕ ያጎናፀፉትን በደማቸው በአጥንታቸው ደማቅ ታሪክ የሰሩትን
ትተን መቼም የማይፋቅና የማይረሳ ከትውልድ ወደ ተውልድ የሚተላለፈውን የ አደዋ ደልን እና ገድል።
  እስከ አፍጢሙ ታጥቆ የመጣውን የጣሊያን ጦር በቂ የመከላከያ ዘመናዊ መሳሪያ ሳይኖራቸው በፍቅር እና በአንድ ልብ
በመሆን አሳፍረው የመለሱበት ታሪክ እና ባንዲራ(ሰንደቅአላማ)ዛሬ ወያኔ የስልጣን እድሜውን ለማራዘም ሰሞኑን ደግሞ
እንደሚሉን እስከ 40 ዓመት የመግዛት የቁም ቅዠት ሀሳብ እንዳላቸው እንሰማለን ለዚህም ነው ክልል በለው ከለለውን
በብዙ ሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያን ደም የፈሰሰበትን ብሄራዊ ባንዲራ እያለን እርስ በርሳችን እንድንተላለቅ
ክልል እያለ የተለያዩ የትግል አርማ ይሁን የመለያ ምልከት ወይም ማስታውቂያ እየተከሉ ልንወጣው የማንችለው ብጥብጥ ውስጥ ለመክተት ከቅደመ አያቱ ጣሊያን በተማረው ባንዳ የባንዳ ልጅ እነሱ ቀደመው ሲመኙት የነበረውን ኢትዮጵያኖችን
የመከፋፈል እና በዘር የመለያየት እቅድ ተሸንፈው የተዋረዱበትን ታሪክ ዛሬ ሊያስፈፅም ቀና ደፋ ይላል ይህን መሰሪ ሴራቸውን
መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ጠንቅቆ ተርድቶታል ምክንያቱም በሀይማኖት ለማበጣበጥ ኢስላማዊ ሃራካት አኬልዳማ የሚል ደራማ ዎችን አሳይን ሙስሊሙ ማህበረስብ በረጅም ግዜ ታሪኩ ከክርስቲያን ወገኖቻቸው በተለያዩ ማሀበራዊ ህይወቶች የተሳሰሩናቸው።
መቼም ቢሆን እንደማይሳካ ተርዱት የበለጠ እንዲተሳሰቡ እንዲፈቃቀሩ ነው ሁለቱንም ያረጋቸው ምክንያቱም ዋናው ጠላታቸው ማንእንደሆነ ጠንቅቀው ሰለሚያውቁ ።
 አሁን ደግሞ ትልቁን የኢትዮጵያን ስርና ግንድ የሆነውን  የኦሮምኛ ቋንቋ ተናጋሪውን ስፊውን ህዝብ ከወገኑ ከአማርኛ
ቋንቋ ተናጋሪ ኢትዮጵያዊ ወንድሙ ጋራ በማጋጨት የመጨረሻውን ካርድ እየሳበነው ወያኔ እንደሚያስበው ኢትዮጵያ እንደ
ሩዋንዳ ህዝብ ሁቱና ቱሲ ተባብለን አንጨፋጨፍም የተለያዩ ብሄርና ብሔርስቦች በመከባብር እና በመፈቃቀድ በመስማማት
የምንኖርበትን አገር ነው መገንባት የምንፈልገው ብዙ ግዜ እንደሚባለው ልዩነታችን ወበታችን ነው ባህላችን ደግሞ መገለጫችን ነው በልዩነታችን ውስጥ መከባበር መተሳሰብ ካለ ሁሉንም ችግራችን በመነጋገር በሰለጠነ በዘመናዊ መንገድ
እንፈታዋለን ይኀውም በቅን ልቦና በማሰብና በንፁ ልብ በመነጋገር።
ኢትዮጵያ ለዘላለም በክብር ትኑር!!!

No comments:

Post a Comment