Sunday, December 1, 2013

የማለዳ ወግ ...የጅዳ ሸረፍያ እስከ ሽሜሲ የተሰማው የወገን ዋይታና እዚህ ያደረሰን መንገድ ! (ነቢዩ ሲራክ)

ፈታኙን ወቅት ለማለፍ ...
 የሳውዲ የምህረት Aዋጅ Aልቆ በሪያድ መንፉሃ ላይ Aለምን ያሳዘነ ሰቆቃ ተፈጸመ
...ስጋት ነግሶ ፣ ኑሮ ከብዶን ጨንቆን ጠቦን ከርመናል ! በዚህ ክፉ ቀን ወገን ወገኑን
ለመርዳት ደፋ ቀና በማለቱ ረገድ የሃገሬ ልጅ ከጫፍ Eስከ ጫፍ በቁጭት ስሜት
ሲንቀሳቀስ የፖለቲካው ትኩሳት ወላፈን Eያጓተተን Aልሰነበትንም Aይባልም። ግልጥልጥ
Aድርግን Eናውራ ካልን የኑሮ ውድነት Eና ድህነቱ Eየደቆሰን ቢያስቸግረን ከወገን
ቤተሰቦቻችን ተለይተን ፣ የEማማ Iትዮጵያውያን ምድር ለቀን በስደት ስንባዝን
በደረሰብን የከፋ Aደጋ ለመቋቋም ከምናደርገው ትግል ባልተናነሰ ልዩነትን የሚያገዝፉ
መሰናክሎችን ማለፉ የከበደ Aበሳ ሆኖብን ሰነባብቷል!
 በዚህ ፈታኝ ወቅት መፈተን ግድ ሆነና የዜጎች Eንግልት ከሪያድ Aልፎ ወደ ጅዳና
Aካባቢው ሲሸጋገር በርካታ ወገኖች በግልና በቡድን በመሰባሰብ በጎ Eርዳታ ለማድረግ
መንቀሳቀስ ጀመሩ። ቀጠሉና ወገኖችን ለመርዳት ብቸኛው Aደራጅ ለሆኑ የIትዮጵያ
መንግስት Iንባሲና ቆንስ ነመ/ቤቶች " ለወገኖቻችን Eንድረስ !" በሚል ያቀረቡት ጥያቄ
ምላሽ Aገኘ። የጅዳ ቆንስል በማህበራትና በIህAዴግ ድርጅቶችን "በነጻ የበጎ Eርዳታ
ድጋፍ Eናቅርብ " ባይ ዜጎች ጋር ጥምር Aስቸኳይ ስብሰባ በመጥራት በAይነቱ ነጻ
የተባለውን "ወገን ለወገን ደራሽ " የተባለውን ኮሚቴ Aቋቋመ። ኮሚቴው የEርዳታ Eና
ድጋፍ ሰጭ፣ የመረጋጋትና የህዝብ ግንኙነት ንUስ ኮሚቴን Aቋቋመ።

የጅዳ ሸረፍያው ሁከት...
 በኮሚቴው መዋቀር መባቻ በጅዳ ሸረፍያ በተባለው Aንድ ሰፈር "ወደ ሃገር Eንግባ !"
ብለው ድልድይ ስር ከተቀመጡ Iትዮጵያውያን መካከል Aንዲት Aራስ Eህት "ልጇን
ሜዳ ላይ ጥላ ሔደች !" ተባለና ህጻን ወድቆ ተገኘች፣ ያንኑ ቀን ከቀትር በኋላ ሌላ Aሳዛኝ
ክስተት በድልድይ ተከሰተ። ከድልድዩ የቅርብ ርቀት Aንድ ወንድም በድንገት በመኪና
Aደጋ ሞተ! የቀን ጸሃይ ፣ የማታው ወበቅ ያደከመውን ወገን Aስቆጣው። ሸረፍያ
ታመሰች! ጸጥታ Aስከባሪዎች ጸጥታ ለማስከበር Aካባቢውን ከበቡት ፣ ፍጥጫ ነገሰ!
በሁኔታውን ግራ የተጋቡት ፖሊሶች ጥይት ወደ ሰማይ በመተኮስ ሁከቱን ለማረጋጋት
ሞክረው ባይሳካላቸውም ከጅዳ ቆንስል የተላኩ የድርጅት Aባላት ሁከቱን ለማረጋጋት
ቻሉ!
 በተፈጠረው ግርግር የተደናገጡት በድልድዩ ሁለት ሳምንታትን በመከራ የገፉ ወገኖች
"ለደህንነታችን ሰጋን! " ሲሉ በዚያው ምሽት ወደ ጅዳ ቆንስል ተመው በመምጣት
በቆንስሉ Aካባቢ ባለው ሜዳ በAሳዛኝ ሁኔታ ከተሙ። የወዳደቀ Eንጨት ፣ፕላስቲክና
Eንጨት Eየለቃቀሙ ጎጆ ሰሩ ! በከፋ ቀን ያልታሰበው ያልተገመተው ሁሉ ይሆናልና ፣
ያላሰብነው ሆነ ! ውሎ ሲያድር የሰው ቁጥር Eየበዛ የጅዳ ቆንስል በከፋቸው ዜጎች
ተጥለቀለቀ ... Aስደሳቹ የወገን ርብርብ ...
 ይህን ጊዜ ነበር ሰው ለሰው ልብሱ መሆኑን የታዘብኩት ። የከፋቸውን ለማጽናናት ፣
የጠማ የደረቀውን ጉሮሮ ለማርጠብ፣ በርሃብ የታጠፈውን Aንጀት ምግብ በማቅረብ
በመታደግ ፣ በተለይም ህጻናትን ለመደገፍ የተደረገው ርብርብ ፍጹም ልዩነታችን ያስረሳ
ልዩ የታሪክ Aጋጣሚ ነበር ። ... ፍጹም ከህሊናየ የማይጠፋ ህብረት !
 የወገኖች የሜዳ ቆይታ ከሳምንት Eንዳያልፍ የተደረገው ጥረት የሚያስደስት ሲሆን
ይህንን ለማደረግ "የዜጎቸ ስቃይ Aኔንም ያገባኛል! " በሚል ቀድሞ Eስከ Aስር ሽህ
የሳውዲ ሪያል በማዋጣት ከመጀመሪያው ቀን Aንስቶ Eስከ መጨረሻዎቹ ቀናት የሰሜንና
ደቡብ " ዋይት " ማህበር Aባላት ምግብ Eና ውሃ በማቅረብ ያሳዩት ትጋት ከEድሜ ጠገብ
ወንድሞች ያልጠበቅኩት ነበር ። ይህ ማህበር በተቋቋመው ኮሚቴ ውስጥ በEርዳታ Aልፎ
በማረጋጋቱ ኮሚቴ በመታቀፍ ያሳየው ፋና ወጊ Eንቅስቃሴ ወደር Aልነበረውም! የጅዳ
ኮሚኒቲ ፣ የIህAዴግ የድርጅት ፣ ለAደጋው የተቋቋመው ኮሚኒቴ ፣ የOሮሞ ልማት ፣
የጂዳ ቆንስል ሰራተኞች ፣የሳውዲው ትውልድ Iትዮጵያዊው የመርባይ ቤተሰቦች ፣
ስማቸው Eንዳይጠቀስ የፈለጉ ግለሰቦች Eና በግል ከጎናችን የተሰለፉ ነዋሪዎች ውሃ ምግብ
በተወሰነ ደረጃ ከማቅረብ ጀምሮ ሻንጣ በማጓጓዝ Eና ዜጎችን በማመላለስ ማስተናገዱ
ረገድ በህብረት የሰሩትን በጎ ምግባር ሳስበው ኩራት ይሰማኝል! ይህ ለበጎ ምግባር
የተደረገ ትብብር የባጀንበትን የከረረ ልዩነት ከAEምሯችን ሲያጠፋው በህብረት ለAንድ
Aፍታም ቢሆን የከፋውን ህይዎት ጠግኖት ማየት መቻል ስለ Eውነት ያኮራል !
የሽሜሲው መጠለያ ቆይታና የግፉAኑ ምሬት ...
 በዚህ መንገድ በቆንስላው ለቀናት የቆዩት ወገኖች መካ መግቢያ የቅርብ ርቀት ወደ
ሚገኘው የሽሜሲ መጠለያ Eስር ቤት ተላኩ ። "ወገኖቻችን ወደ ማጠለያ ገብተው ወደ
ሃገራቸው በሰላም ሊመለሱ ነው !" ብለን ደስታችን ወሰን ባጣበት Aጋጣሚ ግን ወደ
መጠለያው የተወሰዱ ወገኖች ከመጠለያው ሳይገቡ ከግቢው ውጭ ፈሰው ለሶስትና Aራት
ቀናት Eንግልት Eንደ ደረሰባቸው ተሰማ ! ተከፋን ! Eኔም Eንደለመድኩት በሰላም
የሸኘናቸውን ወገኖች ሮሮ መስማት ጀመርኩ ! በቀጣይ ቀናት በግልና ከኮሚቴው ጋር
በመቀናጀት የውሃ ፣ የምግብና የመጸዳጃ ጥያቄውን ለሚመለከታቸው ለማቅረብ ያደረግነው
ሙከራ ሳይሳካ ቀረ። በEርዳታና ድጋፍ ሰጭው ኮሚቴ በኩል የውሃ Aቅርቦቱን ለማድረግ
በተደረገው ሙከራ በAርባ Aውቶቡስ የሞላውን ወደ ሶስት ሽህ የሚሆነውን ሁሉንም
ማስተናገድ Aቅም Aጣን ! የሚቻለውን ግነወ Aደረፍን። Eለተ ሃሙስ ከሽሜሲ መጠለያ
በር ሜዳ ይ የተጣሉት ወገኖች ሮሮ በማየሉ ማታውኑ የEርዳታ Aስተባባሪዎች ባደረጉት
ጥረት የሰሜንና ደቡብ "ዋይት" ማህበር Aባላት ለAርብ ጠዋት የምግብ Eና ውሃ Eንዲ
ያቀርቡ ተጠይቆ በማህበሩ ይሁንታን Aግኝቶ Aርብ ጠዋት Aቅርቦቱን ለመከወን ቀጠሮ
ተያዘ !
የሽሜሲው ሁከት ...
 Eንዲህ Eንደሆነ ሃሙስ በAርብ ተተካ ! Aርብ ጎህ Eንደ ቀደደ በተንቀሳቃሽ ስልኬ
በውሃ ጥማት Eና በርሃብ የታመሱት ወገኖች በተለይም ህጻናትን የያዙ Eናቶች Eንባ
የተቀላቀለበትን የምሬት ጩኸት Eያመመኝ መስማት ጀመርኩ ... በደረሰባቸው ሰቃይ Aምርረው "ወደ ጅዳ Eንመለስ ፣ ሱቅ Eንኳ ከሌለበት ቦታ ከምንሰቃይ ሰው ሊያየን
ወደሚችል ቦታ Eንሄዳለን! " ያሉኝን መልEክት ለማሰማትና መፍትሔ ለማፈላለግ
ብሞክርም ሙከራየ የተሳካ Aልነበረም ። Eናም Eኩለ ቀን ላይ ምሬት ፈንቅሏቸው ወደ
መካና ጅዳ Aውራ ጎዳና መውጣት ሲሞክሩ ከጸጥታ Aስከባሪዎች ጋር መጋጨታቸውን
ተረዳሁ! የሁከት ብጥብጡን ጅማሬ ሂደት በቀጥታ በስልክ መረጃውን ከሚያቀብሉን
ግፉAን ወገኖች ድመጽ Aልፎ የሚሰማው የተኩስና የሁከት ጫጫታ ድምጽ Eየሆነ ያለውን
ያሳይ ነበር ... ይህ በEንዲህ Eንዳለ የሰሜንና ደቡብ "ዋይት" ማህበር Aባላት ለAርብ
ጠዋት የምግብ Eና ውሃ Aዘጋጅተው ወደ ሽሜሲ ሊንቀሳቀሱ ሲሉ የሁከቱን መረጃ
ደረሳቸው! የተዘጋጀው ምግብ ማቅረብ ሳይቻል ቀረ!
 ከሰAታት በኋላ የጅዳ ቆንስል ሃላፊዎች Eና የሳውዲ መንግስት ከፍተኛ ሃላፊዎች
ችግሩ Eስኪከሰት ዘግይተውም ቢሆን ባደረጉት ድርድር ሁከቱ በርዶ ለሶስት ሰAታት
ተዘግቶ የነበረው የጅዳ መካ Aውራ መንገድ ተከፈተ ... የተዘጋጀው ምግብ ማቅረብ
ያልቻሉት ወንድሞች ምግብ ውሃውን በሽሜሲ ላሉት ወገኖች መድረስ ባይችሉም በመካ
ኩደይ በተባለ Aካባቢ በተመሳሳይ መንገድ "ወደ ሃገር Eንግባ! " በሚል Aደባባይ ለወጡት
ወገኖች ምግብና ውሃውን በAፋጣኝ መንገድ Aቀረቡ ፣ Aሁንም ካለው የህዝብ ብዛት
Aንጻር ምግቡና ውሃው ለሁሉም ባይዳረስ Eንደሚሆን Eንደሚሆን Aድረገው Eርዳታውን
Aከፋፈሉ ! ወገን ለወገን ደራሽ መሆኑን ለማየት ፣ ለመስማት ብሎም የመከራው ቀን በጎ
ስራ Eማኞች ለመሆንን ታደልን !
ይቅርታው ...
 Aርብ ምሽት - የወገን ለወገን ደራሽ ኮሚቴ መደበኛ ስብሰባ Aድርገን Aንዱን
Aንስተን Aንዱን ስንጥል Aመሸን ። Eኩለ ሌሊት ስብሰባው ሲከወን የኮሚቴውን Aካሔድ
ለማስተካከል የተወሰደው ውሳኔ ተላለፈ፣ ከጎናችን ሆነው ደፋ ቀና የሚሉትን ወገኖች
Aስከፋ : ( ውሳኔው መተግበር ቢኖርበትም ከውሳኔው በፊት መስራት ያለብንን ስራ
ባለመስራታችን ወንደሞቻችን Aስቀይመናል! የሚሰራ ይሳሳታል ፣ ስንሰራ ተሳስተናል!
ይቅርታችን የከበደ ነው ! የAካሔድ ጠፋቱ Aካል ነበርኩና ያች ምሽት ለEኔ ከባድ ነበረች
... የከበደኝ መሆን ያለበት ወገንን ለመታደግ የሚደረገውን ሂደት ለማስተካከል
የተደረሰበት ውሳኔው ሳይሆን ቡና Eየጨለጡ የሚፈላሰፉ በበዙበት ከባቢ ደጋግ በጎ
Aድራጊ ወንድሞቻችን በማስከፋታችን ነበር! በዚሁ ስብሰባ "ገጽታችን Eንገንባ! "
የምትለው የAንዳንድ ወገኖች Aካሔድ Aንድምታ ግራ ሲያጋባኝ Aለም Aቀፉን ህብረት
Eየነቀነቀ ያለውን የወገን ለወገን የመድረስ Aላማ ወደ ሌላ Aቅጣጫ የሚጎትት ምሽት ላይ
በስልክ ካደረግኩት የራዲዮ ውይይት ጋር በAንድና በሌላ Aቅጣጫ ሲሳሳብ ከፊቴ ተደቀነ!
ስብሰባው Eኩለ ሌሊት ተጠናቀቀ! ... ወደ ቤት ገብቸ Eንዲህ ስል የተጎዳ ስሜቴን
Eንዳሻኝ ስሜት ህመም ፣ ተስፋ ህልም ስጋቴነወ Eንዳሻኝ በምገልጽባት የፊስ ቡክ ገጼ
ተነፈስኩት ...ተቃዋሚው ባንድ ወገን መንግስትና ደጋፊው በሌላ ወገን ይሳሳባሉ ፣ ሁለት
ዝሆኖች ይታገላሉ ፣ ድሃ መውጫው ቀዳዳ ጠቦታል ፣ ወገኔ ከዝሆኖች ጥል ስር የበቀለ
ያልታደለ ሳር ሆኖ ይደቆሳል ፣ የባሰውኑ ታምሜ Aመሸሁ ! Aይመሽ የለም መሽቶ
ከተማሩ ከተመራመሩ ፣ ከወለዱ ከከበዱት ወንድሞቸ ጋር ወገኔን መረጃ ከማቀበል
በተግባር ወደ መርዳት ልሸጋገር ስብሰባ ተቀመጥኩ ! ትልልቆቹ Aንሰን ቢታየኝ ህምም
ታምሜ Eኩለ ሌሊት ወደ ቤት ገባሁ ! ያየሁ የሰማሁ የሆነውን ለመርሳት Eየሞከርኩ
Aይተኛ የለም ተመስገን ብየ ተኛሁ ! ዛሬ Eንጃ ! የማውቀው የትናንቱን ክፉ ቀን ነው ! በተስፋ የተጀመረው ቀንና የምስራቹ ...
 Eለተ ሰንበት ቅዳሜ - በልጀ የማለዳ ሳቅ ታጅቤ በተስፋ ተነሳሁ ... Eንዲህም Aልኩ
...ዛሬ Eንጃ ! የማውቀው የትናንቱን ክፉ ቀን ነው ! ልጀ ሆይ! መውለድ ደጉ ዛሬን ባንች
ፈገግታ በተስፋ ሊጀመር ነው ! ተመስገን ! ተመስገን ! ተመስገን ! መልካም ቀን
ለሁላችሁ!
 የEኔን የሃጥUን ጸሎት ሳይሆን ልጆቻቸውን ታቅፈው ጨንቋቸው ፣ ጮኸው ሰሚ
ያጡትን ወገኖች ሃያሉ Aምላክ Aልተዋቸውም! EግዚAብሔር Aምላክ በስደት የተሰበረውን
የወገኖቻችን ጉዳት ሰማ ! የጨነቃቸው የጠበባቸው በደስታ ፊስታ ተናኙ ! በጭንቀት
ሁከት የሰነበቱት ወገኖች ወደ ሃገር ቤት ለመሄድ ዝግጅት መጠናቀቅ መረጃ የደረሰኝ
በተስፋ የጀመርኩትን ቀን የሚያበላሽ ቧልት ሰምሁና Aዘንኩ ። ሞራል ያጡ ፣ በወገን
ችግር ጀርባ በቪዛ ሽያጭ ፣ በድለላ Eና በመሳሰሉት ጥቅምን በማጋበስ የለመዱ ክፉዎች
በዚህ ክፉ ቀን Eንኳ ስለሚንገላታው ወገን Aይጨነቁም! ለጆቻቸውን ስለሚያስተምሩበት
ትምህርት ቤት Eያደር መበለሻሸት ግዳቸው Aይደለም! Eናም ተበሳጭቸ ከጅዳ ኮሚኒቲ
ካፍቴርያ Eንደወጣሁ ስልክ ተደውሎ የምስራች መልEክት ደረሰኝ!
" ነቢዩ ደስ ብሎናል ! Eንኳን ደስ ያለህ ! ትናንት Eየደወልን ስጨናንቅህ የነበርነው
ሁላችንም ወረቀታችን Aልቆልን ወደ ጅዳ Aየር መንገድ Eየተጓዝን ነው! " ተመሳሳይ
የስልክ ጥሪ ደረሶኝ ተመሳሳይ የምስራች ሰማሁ! ዛሬ ለቅሶ የለም! Eኒያ ሲንገላቱ የሰነበቱ
ወገኖች ሳቅ በሳቅ ሆነው ፣ በደስታ ተውጠው የምስራቹን ሲያበስሩኝ የተሰማኝ ደስታ ወሰን
የለውም ! Aዎ ወደ Aራት ሽህ የሚገመቱት ወገኖች የሃገራቸውን መሬት ለመርገጥ
መታደላቸው በEርግጥም ታላቅ የምስራች ነው ! ተመስገን !
ከሽሜሲው ግጭት የምንማረው ...
 ከሽሜሲው ግጭት ብዙ ልንማር ይገባል ። በጅዳ ቆንስል የቅርብ ርቀት ከትመው
ለሳምንት ከቆዩ በኋላ ወደ ሺሜሲ መጠለያ በወገን ትብብር የተወሰዱት ወገኖች
በመጠለያው ግቢ Eንዳይገቡ ተደርገው ነበር። በጠራራው ጸሃይ በAውቶቡስ Eና በሜዳ
ላይ ያለ ምግብና ወሃ መሰንበታቸውን የጅዳ ቆንስል ሰራተኞችና ሃላፊዎች ወደ መጠለያው
ሲገቡና ሲዎጡ ይመለከቷቸው ነበር ። ያም ሆኖ ከሶስትና ከAራት ቀናት በላይ ህጻናትን
የያዙተን ጨምሮ Aቅመ ደካማ Eህቶች በወሃ ጥማት ሲጠበሱና በርሃብ Aንጀታቸው
ሲታጠፍ ከቅርብ ርቀት ያሉት የቆንስል መስሪያ ቤቱ ሰራተኞችና ሃላፊዎች መፍትሄ
Aላፈላለጉላቸውም። በዚህ መሰል Aስከፊ ሁኔታ ህጻናት ደክመው ፣ ነፍሰ ጡር Eህቶች
ደክመው ፣ የተወሰኑት AEምሯቸው ተነክቶ ታዝበናል። የሁከቱ መንስኤ ለቀናት በርሃብና
በውሃ ጥማት የተቸገሩት ግፉAኑ ወገኖች ትEግስት ማጣት Eንጀ ሁከትን ለማስነሳት ታቅዶ
የተፈጸመ Eንዳለሆነ ግልጽ መሆን Aለበት!
 " ወደ መጠለያ Aስገባሁ !" ብሎ በመጠለያው በር ሜዳ ላይ ያፈሰሳቸውን የሳውዲ
መንግስት Aካል ከመሞገት ባለፈ ይህን መሰል Aስነዋሪ ስራ Eንዳይሰራ የጅዳ ቆንስል
ሃላፊዎች መስራት የነበረባቸውን ስራ በበቂ ሁኔታ ሰርተዋል Aልልም። የጅዳ ቆንሰል
ሃላፊዎች ወደ መጠለያው የተላኩ ዜጎቹን ጉዳይ በEግር በEግር ተከታትለው ማስፈጸም
ነበረባቸው። ይህ Aልተደረገም ወይም ተደርጎ Aልተሳካም ይሆናል። በAንድ Aቅጣጫ
ያልተሳካውን በሌላ Aቅጣጫ ለማስፈጸም የቆንስሉ ሃላፊዎች ያደረጉት ሙከራ Aንድ ሁለት ቀን ቢከሽፍ ከAራት ቀን በላይ መጓተቱ ዲፕሎማቶቻችን ከፍተኛ ጫናን ፈጥረው
ጉዳዩን በማስፈጸሙ ረገድ Eንዳልተሳካላቸው በግልጽ ያሳያል። የሳውዲ መንግስት Eና
የጅዳ ቆንስል ሃላፊዎች በፈጻሚና Aስፈጻሚ Aለካት መካከል መግባባት ቢኖር ኖሮ ዜጎችን
ወደ መጠለያው Eንኳ ማስገባት ቢገድ ካሉበት ቦታ ምግብና ውሃ በማቀበል Aጠቃላይ
ሂደቱን መቆጣጠር ይቻል ነበር። በሂደቱን የጅዳ ቆንስል ሃላፊዎች በቅርብ ተከታትለውት
ቢሆን ኖሮ Aነወዱ Aንኳ ቢያስቸግር የጉዳዩን Aሳሳቢነት ለማስረዳት ከከፍተኛ የሳውዲ
መንግስት ሃላፊዎች መድረስ ይችሉ ነበር። ከዚህ በተጓዳኝ ለመገናኛ ብዙሃን በAሰራር
የሚገጥማቸውን መሰናክል በማቅረብ ድምጻቸውን ሊያሰሙ ይገባ ነበር ። ይህ Aልሆነምና
ትኩረት ባለመሰጠቱ ሰው ተራበ ተጠማ ሁኔታዎች ከቁጥጥር ውጭ ሆኑ ! ወደ ዝርዝር
ሳንገባ ካለፈው ጥፋት ልንማር ግድ ይለናል! ካለፈው ስህተት ከተማርን ከተመሳሳይ ሁከት
ልንድን Eንችላለን !
የማይበጀን ሁከት ፣ የማይፈይድልን መረጃ ....
 ይህን መሰል ችግር መቅረፍ የሚቻለው ሁላችንም ያገባናል ብለን በህብረት ስንደጋገፍ
ብቻ ነው! ሰላማዊ ሰልፍ Aና የAደባባይ ላይ ተቃውሞ በማይፈቀድ በማይታሰብባት
ሳውዲ Aረቢያ ችግር Eንኳ ቢሆር የሚፈታባቸውን መንገዶች ከማፈላለግ ባለፈ ሁከት
Aመጽን መከተል Aይጠቅመንም። ወደ ሁከት የሚወስደውን ሁሉ Eንቅስቃሴ በማስዎገድ
Eና መረጃን በመለዋወጥ ችግሮች Eንዲሰሙ ማድረግና ማስተካከል ይቻል ይመስለኛል!
በነጻነት መረጃን ከተለዋወጥን የማይቻል የለም ይቻላል! ነዋሪውን ለማረጋጋረት ብሎ
ያልሆነውን ሆነ ብለን "የዋሽቶ ማስታረቅ! " ዘይቤ ፍጹም Aይበጀንም! ገጽታን Eናሳምር
ምናምን ብለን "ቅባቱን " ተጠቅመን መረጃውን Eና Eውነቱን ካዛባነው መረጃው ዘባተሎ
ይሆናል ፣ ከዚሁ ጋር ችግሩን ለመታደግ የምንወጣ የምንወርደው ሁሉ የተዛባው ባለቅባት
መረጃ ተAማኒነትን ያሳጣናልና ድካሙን ሁሉ የEንቧይ ካብ ያደርገዋልና ጥንቃቄ
ማድረግ ይገባል : )
የስኬቱ ባለድርሻዎች ...
 በመላ ሳውዲ ችግሩ በEኛ ላይ ከጠና ወዲህ ወገኖቻችን ወደ ሃገራቸው Eንዲገቡ
የሚደረገው ስኬት በተወሰኑ ግለሰቦች ወይም ቡድኖች የተከወነ Aይደለም ። በሃገር ቤት
በውጭ ሃገር ያሉ ወገኖች በሳውዲ መንግስት ላይ ያሳደሩት ተጽEኖ ፣ በሳውዲ Aረቢያ
የተለያዩ ከተሞች የምንገኝ ሁላችንም በህብረት የሰራነው ስራ ውጤት ነውና ደስ ሊለን
ይገባል! ምስጋናውም ለሁሉም ነው ! ወገንን መደገፍ ምስጋና ካስፈለገው ማለቴ ነው ...
ደስ ሲል ...!
ለወገን ደራሹ ወገን ነው ፣ በህብረቱ ፣ Eንበርታ !
ነቢዩ ሲራክ
ምንጭ የኢትዮጵያ ሜዲያ መድረክ

No comments:

Post a Comment