Sunday, June 30, 2013

ቅንነት እና መልካምነት ማስተዋል ቢኖርን ኖሮ?


  መልካምነት ከሁሉም በላይ በእለት እለት ኑሮችን ሊንፀባርቅ የሚገባው አባይ ጉዳይ ነው።
በአለማችን ላይ በመልካም ስራቸው የምናደንቃቸውና የምንከብራቸው የተለያዩ ግለስቦች አሉ መልካሙ ስራቸው
ከትውልድ ወደ ትውልድ የሚተላለፍ በህይወት ካለፉ በኋላ ስማቸው እና ክብራቸው ከመቃብር በላይ ይውላል።
በአገራችን በኢትዮጵያ ብዙ ስራ እየስሩ ያሉ በርካታ ግለሰቦች ግዚያቸውን ጉልበታቸውን እንድሁም ዕውቀታቸውን
ብሎም ህይወታቸውን መስዋት በማድረግ ገንዘባቸውን ለወገናቸው የከፈሉ በርካታ ወድ የኢትዮጵያ ለጆች አሉ።
በግሌ ይህንሀስቤን ለመጻፍና ለመግለፁ ያነሳሳኝ ደከመኝ ስለችኝ ሳይል በተጠራበት ቦታና አገር ለወገኖቹ ፈጣን ምላሽ
እየስጠ ያለውን የኢትዮጵያዊነት ወግናዊነቱን ፍቅሩን አክብሮት እየገለፀ ያለው ውድ የኢትዮጵ ልጅ ሚስተር ኦባንግ ሜቶ።
       ከሁሉም በላይ ይዞየተነሳው ቅድስ አላማው የስውልጅ ሊኖርው የሚገባው ስባዊመብትና ፍትህ
   እኩልነት ዲሞክራሲ ከሚታገልለት አላማዎች ናቸው በተላያዩ የአለም ሀገሮች በትላልቅ መድርኮች በመገኝት በኢትዮጵያ
ያለውን የሰባዊ መብት ጥስትና ህገወጥ የመሪት ንጥቂያ ህዝቦችን ከነሩበት ቄዬ ወይም አገር ያላግባብ ሲፈናቃሉ የሚደርስባቸውን የስባዊ  የመብት ጥስት ሊደርስባቸው የሚችል የፖለቲካም ይሁን የኢኮኖሚ ችግር በአለም አደባባይ እየገልፀና
እያሳወቅ የሚገኝ ታላቅ ስው ነው ዘውትር የሚለው ታላቅ ቃል አለ ዘርኝነት ከሚጠላውና ከሚቃውምው ትልክ ነገር ነው
በአንድነትና በኢትዮጵዊነቱ የሚኮራ ምርጥ የዘመናችን ታላቅ ሰው ነው።
   የተለያዩ የፖለቲካ ድርጅቶችም ቋንቋን መሰርት ያደርጉ የፖለቲካ ድርጅቶችም ይሁን ግለስቦችም ከወገናቸው
ኦባንግ ሜቶ ብዙ ቁም ነገሮችን መማር ይቻላል።
     ይህ ሁሉ ተሟልቶ ቢኖር ኖሮ የሀሳብ ልዩነቶቻችንን ችግሮቻችንን በመነጋገርና ዘመናዊ በሆነ መልኩ መፍታት
በተቻለ ነብር በመጠላለፍ እና በምወቃቀስ የትም እንደርስም የወያኔን እድሜ ከማርዘም በስተቀር።
    ዳዊት ወንድሙ።

No comments:

Post a Comment