Sunday, March 30, 2014

ኢህአዴግ የእምነት ተቋማትን በጥብቅ የሚቆጣጠርበት ህግ ሊያጸድቅ ነው ህጉ ጣጣ እንዳያመጣ የሰጉ ኢህአዴግን እየመከሩ ነው

March 29,2014 10:52 am
ኢትዮጵያን ከሁለት አስርተ ዓመታት በላይ እየገዛ ያለው ኢህአዴግ የሃይማኖት ተቋማትንና ምዕመናኑን በጥብቅ የሚቆጣጠርበትን ህግ ለማጽደቅ በዝግጅት ላይ መሆኑ ተሰማ። የህጉ ረቂቅ የደረሳቸው ከፍተኛ ዲፕሎማቶች ኢህአዴግን አበክረው እየመከሩና በሚያመጣው አጠቃላይ መዘዝ ዙሪያ እያስጠነቀቁ ነው።
ጎልጉል ከዲፕሎማት ምንጮቹ ባገኘው መረጃ መሰረት ኢህአዴግ በእምነት ተቋማት ላይ ቁጥጥሩን የሚያጠብቅበትንና ከሃይማኖት ተቋማት ቅጥር ግቢ ውጭ መሰብሰብን፣ ሰላማዊ ሰልፍ ማድረግንና የተቃውሞ ድምጽ ማሰማትን የሚከለክል ህግ አዘጋጅቷል።
የዜናው ምንጮች ዝርዝር ህጉን ለጊዜው ይፋ ከማድረግ እንደሚቆጠቡ አስታውቀዋል። ይሁን እንጂ የሚደነገገውን አዲስ ህግ ጥሰዋል በሚል የሚከሰሱ ምዕመኖች እስከ እድሜ ልክ በሚደርስ እስራት እንዲቀጡ የሚያዝ አንቀጽ አለበት። አዲሱ ህግ ከሽብርተኞች ህግ ጋር የሚጣቀስ እንደሆነም የጠቆሙት ክፍሎች ኢህአዴግ “ከእምነት ነጻነት” ጥያቄ ጋር በተያያዘና በኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ዘንድ ውስጥ ውስጡን እየነደደ ያለው ችግር ስላስጨነቀው ይህንን ህግ ለማውጣት መገደዱን አስረድተዋል። በሌላ በኩልም እስካሁን መፍትሔ ያላገኘው የሙስሊሞች ጥያቄ ከዚያም ጋር ተከትሎ የተከሰተው ደም መፋሰስ ወደፊት ሊያመጣ በሚችለው ጉዳይ ላይ ኢህአዴግን በብርቱ አሳስቦታል፡፡
ኢህአዴግ ከቀን ወደ ቀን ቀውስ እየተደራረበት እንደሆነ የተረዳችው አሜሪካ በከፍተኛ ባለስልጣኖቿ አማካይነት ኢህአዴግን እየመከረች እንደሆነ ከዲፕሎማቶች የተገኘው መረጃ ያመለክታል። ከፖለቲካው ቀውስና በቀጠናው ካለው አለመረጋጋት ጋር በተያያዘ አሜሪካ በተደጋጋሚ የህወሃትን ሰዎች በተናጠል እያነጋገረች እንደሆነም ለማወቅ ተችሏል። ዲፕሎማቶቹ እንደሚሉት አሜሪካ መለስ “ከተሰዉ” በኋላ አገሪቱን ማን እየመራት እንደሆነ በቅጡ ለመረዳት በሚያስቸግር ሁኔታ የስልጣን መዛነፍና ደረጃን የጠበቀ የስልጣን ተዋረድ አለመኖሩም አሳስቧታል። ኢህአዴግ ለህልውናዬ ያሰጋኛል በሚል መንግሥታዊ ባልሆኑ ግብረ ሰናይ ድርጅቶች /መያዶች/ ላይ ያወጣውን አፋኝ ህግም ጠቅሰዋል። ዲፕሎማቶቹ በጉዳዩ ዙሪያ ዝርዝር መረጃ ለመስጠት ወቅቱ አሁን እንዳልሆነ አመልክተዋል።

Saturday, March 29, 2014

በነገሌ ቦረናው ግጭት ከ30 ሰዎች በላይ ተገድለዋል፤ ግጭቱ አልቆመም

ነገሌ ቦረና (ፎቶ ፋይል)
ምንሊክ ሳልሳዊ ፦ በደቡብ ኢትዮጵያ በነገሌ ቦረና ከከተማው ስም ስያሜ ጋር በተያያዘ በጉጂ እና በቦረና ማህበረሰቦች መካከል በነገሌ ቦረና አካባቢ በተነሳ ግጭት ከ30 ሰዎች በላይ መሞታቸውን እና ግጭቱም አለመቆሙን የአከባቢው ባለስልጣናት ምንጮች ማምሻውን በላኩልን መረጃ ገለጹ። ከባለፈው እሁድ ጀምሮ በአከባቢው የተነሳው ግጭት በመስፋፋት ከፍተኛ የሆነ ንብረት ያወደመ ከመሆኑም በላይ ከነገሌ ከተማ ውጪ ለጉላ እና አርዶታ በተባሉ አከባቢዎች ግጭቱ ተስፋፍቶ መቀጠሉ ታውቋል። ከዚህ ጋር በተያያዘ ወደ ግዛቴ ግጭቱ ዘልቆ ሊገባ ይሽላል በሚል ፍራቻ ኬንያ ወታደሮቿን በድንበር አከባቢ አስፍራል እያስጠበቀች መሆኑ ታውቋል።
የኢሕአዴግ ፌዴራል ፖሊሶች እና የኦሮሚያ ክልል ልዩ ሃይል ፖሊሶች በቦታው ደርሰው የነበረ ቢሆንም የአከባቢው ህብረተሰብ ቀየውን በመልቀቅ እየተሰደደ መሆኑን ታውቋል። በከፈትና ፍጥነት እየተስፋፋ የመጣውና የጎሳ ፌዴራሊስም ፖለቲካ ውጤት የሆነው ይህ ግጭት በአካባቢው ባለስልጣናት እና የሃገር ሽማግሌዎች ለመፍታት ቢሞከርም ሳይሳካ ግጭቱ እንደቀጠለ ታውቋል።
ምንጭ ዘ-ሐበሻ

Thursday, March 27, 2014

የሰማያዊ ፓርቲ ሉቀመንበር በአሜሪካ መንግስት የአፍሪካ ስኬታማ ወጣት መሪ ተብለው ተመረጡ

 /ር ይልቃል ጌትነት
አዲስ አበባ፡- የሰማያዊ ፓርቲ ሉቀመንበር ኢንጅነር ይልቃል ጌትነት በአሜሪካ መንግስት ስቴት ዲፓርትመንት የአፍሪካ
ስኬታማና በቀጣይነትም ሀገራቸውን መምራት የሚችለ ወጣት መሪ ተብለው ተመረጡ፡፡

ከፓርቲው የህዝብ ግንኙነት የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው ኢንጅነር ይልቃል ለአሸናፊነት የበቁት ‹‹የአሁኑ
ወጣት የአፍሪካ መሪና ወደፊትም ለአገራቸው መሪ ሉሆኑ የሚችለ፣ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ጥሩ ስራ የሰሩ መሪዎች
መካከል በተደረገ ውድድር በአሜሪካ መንግስት ስቴት ዲፓርትመንት›› መስፈርቱን አሟልተው በመገኘታቸው ነው፡፡

ሉቀመንበሩ ለአሸናፊነት መብቃታቸው ይፋ ከመሆኑ በፊት የአሜሪካ መንግስት የኢንጅነር ይልቃልን መሰረታዊ
የሚባለትን የፖለቲካ ቆይታ፣ የትምህርት ዝግጅት፣ በፖለቲካው ውስጥ የነበራቸውን ተሳትፎ እና የመሳሰለትን
መረጃዎች ወስዶ እንደነበር ለማወቅ ተችሏል፡፡

ኢንጅነር ይልቃል በዚህ ውድድር በመመዘኛዎች መሰረት በማሸነፋቸው በአሜሪካ መንግስት ስቴት ዲፓርትመንት
የጉብኝት ግብዣ ተደርጎሊቸዋል፡፡ በመሆኑም የአሜሪካ መንግስት ሙለውን ወጭ ሸፍኖ ለሶስት ሳምንት በአሜሪካ
የመንግስት አወቃቀርና ዴሞክራሲን ጨምሮ በተግባር የሚሰጡ ስልጠናዎችን የማግኘትና የአሜሪካ መንግስት
ባለስልጣናትም ባለበት ከተለያዩ ተቋማት ጋርም ለመገናኘት እድል እንደሚኖራቸው ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

‹‹የሉቀመንበሩ ለዚህ ሽልማት መብቃት አዲሱን ትውልድ ወደ ፖለቲካው ለማምጣት በሚያደርገው ጥረት እንደ አንድ
ማበረታቻ ተደርጎ ሉወሰድ እንደሚችልና ሰማያዊ ፓርቲ እያደረገው ላለው ሰሊማዊ ትግል ትልቅ እውቅና እንደሆነ
ያሳያል›› በማለት የህዝብ ግንኙነቱ ያደረሰን መረጃ ይጠቅሳል፡፡ ኢንጅነር ይልቃል ጌትነት ዛሬ ወደ አሜሪካ
እንደሚያመሩም መረጃው ጨምሮ ገልጾዋል፡፡
source quatero.net.

Tuesday, March 18, 2014

ሁለቱ ተፎካካሪ ነገስታቶች (ቁምላቸው ገ/መስቀል አምቦ)

ምኒልክ ሁሉን አስገበሩ። ጣሊያንንም አድዋ ላይ አሸነፉ። አንድ ስጋት ብቻ ቀረ ከወደ ደቡባዊ ከፍታዎች የመሸገ ባላንጣ። ከአርሲ ዘመቻ በፊት ምኒልክን በአንድራቻ ደጅ ያስጠና ጌታ።
የኝህ ጀግና መጠሪያ ስም ጭኔቶ ጋሊቶ ሲሆን የዙፋን ስማቸው ካፊ አቲዮ ጋኬ ሻረቾ (አጼ ጋኪ ሻረቾ) የካፋ ንጉሰ ንገስት ነው። ሕዝቡ ዝወትር በፍቅርና በአክብሮት የሚጠራቸው ግን ታተኖ ጭኒ እያለ ነበር።
የካፋና የሞቻ ሕዝብ በነገስታት መሪነት ቢያንስ ሶስት ምዕተ ዓመታት ወረራን በመከላከል የብሔር ህልውናውን አስከብሮ እነሆ ዛሬ የጎንጋ ሕዝብ ታሪክና ባህል ዋና አንጸባራቂ ምልክት ሆኖ ይገኛል። በተለይ የመጨረሻዎቹ ሶስት የካፋ ነገስታት፤
  1. አጼ ካዮ ሻረቾ (ኪም ዩሮ) እ. ኤ. አ. 1854 – 1870
  2. አጼ ጋሊ ሻረቾ (ታተኖ ጋሊ) እ. ኤ. አ. 1870 – 1890
  3. አጼ ጋኪ ሻረቾ (ታተኖ ጭን) እ. ኤ. አ. 1890 – 1897 የምኒልክን የግዛት መስፋፋት ዘመቻ መከላከል ዋና ወታደራዊና ፖለቲካዊ ተግባራቸው አድርገው ቆይተዋል።
የጎጃሙን የንጉስ ተክለ ሀይማኖትንና የራስ ደርሶን ሙከራ ሳይጨምር ከምኒልክ የመጨረሻ የካፋ ዘመቻ ጋር ከአራት መራራ ጦርነት በኋላ ነበር ጥንታዊው የካፋ መንግስት የተደፈረውና ዝነኛው የቡሻሼ ሜንጆ ስርወ መንግስት (ዳይናስቲ) የፈረሰው። ከሽንፈት በኋላም ቢሆን ግን የመጨረሻው የካፋ አቲዮ (የካፋ ንጉሰ ነገስት) ኩሩና ልበ ሙሉ እንደነበሩ ታሪክ ይመስክራል። ለምሳሌ በጠላት እጅ ከወደቀ ጊዜ እንኳ በወርቅ ሰንሰለት እንደታሰሩ እንጂ ብር ሰውነታቸውን እንዳይነካ ነበር የጠየቁት። ሆኖም ራስ ወልደጊዮርግስ አቦዬ (ቆቅማሪ) የወርቅ ሰንሰለት አላዘጋጁም ኖሮ በጥያቄው ተደነቁ። ይሁንና ተሸንፈው ንጉሱ ራሳቸው ባቀረቡት ሰንሰለት ታሰሩ። ጎደንፎ (ጎጀብን) ወንዝ በመሻገር ላይ ሳሉም “የካፋ መንግስት አለቀልሽ ከውሃ የተገኘሽ የንጉስ ወርቅ ከውሃ ውስጥ ሁኚ (አቼ ዳኔቲ ታቲ አቼኔ አጮች ቤበ)” ብለው የንግስና የወርቅ ቀለበታቸውን እወንዝ ውስጥ እንደከተቱት እስከ ዛሬ ይተረካል።
ካፊ አቲዮ ጋኬ ሻረቾ (አጼ ጋኪ ሻረቾ)
ካፊ አቲዮ ጋኬ ሻረቾ (አጼ ጋኪ ሻረቾ)
ከምኒልክ ፊት እንደቀረቡም “ራስህን እንደታላቅ ንጉስ ትቆጥራለህ። ንገር ግን ይሄ ግምትህ ከእኔ ጋር ፈጽሞ ሊወዳደር አይችልም። ላንተ ዘውድ የተጫነው በሰው እጅ ሲሆን የኔው ግን ከላይ ከአንድ አምላክ ከ (ኢኬ የሮ) የወረደልኝ ነው” ማለታቸው ኩሩና አይበገሬ ለመሆናቸው ማስረጃ ነው።
ሕዝቡም እንደ ንጉሱ በቀላሉ አለመበገሩም ጸሐፊ ገብረስላሴ ሲገልጹ “… ነገር ግን ስለስፍራው ከፋት እየተዋጋ አልገብርም ብሎ ንጉሱ ከአንድ ቦታ ወደ አንድ ቦታ እየተዘዋወረ የካፋ አገሩም ጠፋ። ሰውም አለቀ። ከዘማቹም ከክርስቲያኑም ብዙ ሰራዊት አለቀ። ከዚህ በኋላ 9 ወራት ሙሉ ተዋግቶ በነሐሴ 29 ቀን የካፋው ንጉስ ተማረከ። የተረፈውም አገር ሲማረክ ዘውዱ የወርቅ፣ ወንበሩ የወርቅ፣ አለንጋው ስንቴል ነጋሪት ያውም ነጋሪቱ አንዱ የብር አንዱ የነሀስ ነው። በነጋሪቱም ላይ ስሙ ተጽፎበታል። ይህ ሁሉ ከንጉሱ ጋር ተያዘ” በማለት ነበር የገለጹት።
የካፋ መንግስት ለአጼ ምኒልክ አላድርም ብሎ 17 ዓመት ሙሉ እጁን ሳይሰጥ ቆየ። ከአድዋ ጦርነት በኋላ ግን ማለትም ጣሊያን በተሸነፈ በዓመቱ ተረታ። ይህም ሊሆን የቻለው ከጣሊያን ሽንፈት በኋላ መሳሪያ በመገኘቱ በ20000 (ሀያ ሺህ) ዘመናዊ ጠመንጃ በሶስት አቅጣጫ ተከቦ 9 ወራት ገትሮ ከተዋጋ በኋላ ነበር።
አጼ ጋኪ ሻረቾና አጼ ምኒልክ እጅግ ተፎካካሪ ነገስታት ነበሩ። ፉክክሩ በገብር አልገብርም ብቻ የተወሰነ ሳይሆን የስርወ መንግስት (የዳይናስቲ) ጥያቄ ውዝግብ ስለነበረበት ነው። ስለዚህም የካፋ ሕዝብ በታሪኩና በማንነቱ እንደሚመካ ባወቀ ጊዜ አደገኛነቱ ስለታያቸው ፔርሀም እ.ኤ.አ 1948 ሶንታንደን የተባለው አገር አሳሽ ጠቅሶ እንደዘገበው አጼ ምኒልክ የስዊስ አማካሪያቸው የካፋ ነገስታትን የወርቅ ዘውድ ወደ አገሩ እንድወስድ አደረጉ።
አጋራሻ እተሞ የተባሉት ታሪክ አዋቂ አዛውንት እንዳጫወቱኝ ሁለት ካፋዎች ዘውዱን በትረ መንግስቱንና ሌላም ወርቃ ወርቅ የንግስና እቃዎችን ከአንኮበር ይዘው ካፋ ከገቡ በኋላ ከምኒልክ የተላከ ጦር ሰዎቹን አሳዶ ከገደላቸው በኋላ እቃው ወደ አንኮበር ተመለሰ። ከዚያ በኋላ ይሆናል እንግዲህ የዘውዱ በኢትዮጵያ ምድር መኖር ምኒልክን ያሰጋቸው።
ማርስ ግሩል ስለ ጦርነቱ ያገኘውን መረጃ ሲተነትን “ወረራውን የአቢሲኒያ ጦር ለመመከት የካፋ ጦር ያሳየውን የጀግንነት ስራ በተለይም ስለመጨረሻው ፍልሚያ የሚያወሳውን ገጣሚ ወይም ተራኪ ገና አልተነሳም። ሆኖም ይህ የጀግንነት ስራና አሳዛኝ ፍጻሜው በሰው ልጅ የታሪክ ማህደር ውስጥ ቦታ ሊኖረው የሚገባ ነው” ይላል። በምኒልክ የረጅም ጊዜ የመስፋፋት ጦርነት “የካፋ ዘመቻ” የመጨረሻው ምዕራፍ ነበር። በመጨረሻ የተሸነፈው ካፋ ነው። የመጨረሻው ከባድ በትር ያረፈው በእሱ ላይ ነበር።
ምኒልክ የኦሮሞን ክልል በቁጥጥራቸው ስር ካደረጉ በኋላ ፊታቸውን ወደ ካፋ አዞሩ። አሁንም ማክስ ግሩል እንዳስቀመጠው “በዚህ የሰሜን ምስራቅ አፍሪካ ክፍል ለፖለቲካ የበላይነት ከተደረጉ ጦርነቶች የመጀመሪያው ወሳኝ ፍልሚያ በምኒልክና በካፋ መንግስት መካከል የተደረገ ነው” ብሏል፡፡
በ1881 እ .ኤ .አ ምኒልክ ገና የሸዋ ንጉስ ብቻ እንደነበሩ ራስ ጎበናን ወደ ካፋ ላኩ። ሆኖም ካፋዎች በቀላሉ መለሱዋቸው። ምኒልክም ካፋ መገበሩን ገና ሳያረጋግጡ “የሸዋ የካፋና የኦሮሞ አገር” ንጉስ ብለው ራሳቸውን ስለሰየሙ የወቅቱ የኢትዮጵያ ንጉሰ ነገስት አጼ ዮሀንስ አራተኛ ተቆጥተው የጎጃሙን ራስ አዳል ንጉስ ተክለህይማኖት ብለው በካፋ ላይ ሾሙ። በዚህ ምክንያት ምኒልክና ንጉስ ተክለሃይማኖት አምባቦ ላይ ጦርነት ገጥመው ንጉስ ተክለሃይማኖት ተማረኩ።
menelik IIእ ኤ አ 1885 ዓመተ ምህረትም ራስ ጎበና እንደገና ወደካፋ ዘመቱ። በዚህ ጊዜ ለማሟሟቂያ እንዲያደርግ ይመስላል ለጎበና ማእረጋቸው ከፍ ብሎ “የካፋ ንጉስ” ከሚባል ሚካኤል የሚል አዲስ ስም እንዲወጣላቸው ተደረገ። ሆኖም በዚህ ጊዜም ቢሆን ካፋ ባለመሸነፉና ምንም አይነት የመበገር ምልክትም ባለማሳየቱ የራስ አዳልም ሆነ የራስ ጎበና “የካፋ ንግስና” ባዶ ክብር ሆኖ ቀረ።
በጥቅምት 19 ቀን 1886 እ. ኤ. አ. የኢትዮጵያ አካል ያልሆነው ካፋ ለባሻ አቦዬ ተሰጠ። ባሻው ደጃች ተብለው ራስ ጎበና ሁለቴ ሞክረው ያቃታቸውን አገር ባንዴ ድባቅ መተው ካፋ አናት ላይ ቁጭ ለማለት ጨርቀን ማቄን ሳይሉ በከፍተኛ ወታደራዊ ፍጥነት ገስግሰው ጎጀብ (ጎደፎ) ወንዝ ደረሱ። ካፋዎች ግን አስቀድመው የጎደፎን ዳርቻ ከላይ እስከ ታች ዘግተው ስለመሸጉ ፉከራቸው መና ሆኖ ቀረ። በመጡበት ተመለሱ።
ይሁንና የጅማው አባ ጅፋር ብዙም ሳያንገራግር ስለገበሩ ካፋም ይገብራል ተብሎ ተጠብቆ ነበር። ሆኖም የካፋው ንጉስ ይባስ ብለው ለምኒልክ የገበሩበትንም ሊወጉ ይዘጋጁ ጀመር። የካፋ መንግስትም ምንም አይነት ግብር ሳይልክ ድንብሩን በሰራዊት አጥሮ ተቀመጠ። ጅማና ኢሉባቦርንም ሊለውጥ እየተዘጋጀ ነው የሚለው ስጋትም ጨመረ። በዚህን ጊዜ ምኒልክ ታላቅ የዘመቻ ውሳኔ አሳለፉ።
“የካፋ ዘመቻ” በ1889 እ ኤ አ ተጀመረ። የንጉሱ የእህት ልጅ በአውሳ ጦርነት መልስ ራስ ተብለው በካፋ ላይ ተሾሙ። ከራስ ወልደጊዮርጊስ ጋርም የኢሉባቦር ገዢ የሆኑት ራስ ተሰማ ናደውና የወለጋው ደጃች ደምሰው ታዘው ወደ ካፋ ዘመቱ። ይሁንና ራስ ወልደጊዮርጊስ ቀጥታ ካፋ መግባት ስላዳገታቸው ከካፋ በስተምስራቅ የሚገኙትን የዳውሮና የኮንታ መንግስታትን አስከድመው በቁጥጥር ስር ማዋል ነበረባቸው። የካፋ መንግስትም በዚህን ወቅት ከሶስት አቅጣጫ የጦርነት ስጋት አንዣበበበት።
ምኒልክ በቦንጋና አንድራቻ
ምኒልክ ካፋን በጦርነት ሆነ በዲፕሎማሲ ሊያስገብሩ ጥረት አድርገዋል። ራሳቸው ቦንጋና አንድራቻ ድረስ ሄደው ከማንም ሌላ ንጉስ ጋር ያላደረጉትን ውይይት አካህደው ነበር። በ1894 ለወዳጅነት ጉብኝት አንድራቻ እንደደረሱም “ቤቴ ቤትህ ነው” በሚል ባህላዊ አክብሮት ስሜት የካፋው አትዮ ጋኪ ሻረቾ በጥሩ መስተንግዶ ተቀብሎ ሸኛቸው። ምኒልክ በውቅቱ በአርሲ ላይ ከባድ ዘመቻ ከፍተው ስለነበር የካፋ ጦር ከኋላ እንዳይወጋቸው ነበር ስጋት ያደረባቸው።
በመጨረሻ ምኒልክ ካፋ እንዲገብርላቸው አግባብተው “እሽታ” አገኙ። በመልካም ንጉሳዊ ዲፕሎማሲያቸው ረክተው ቢመለሱም ግን የካፋው አጼ ተጠብቀው ምንም ዓይነት የመበገር ምልክት ሳያሳዩ ቆዩ። እንዲህ በመሆኑ የመጨረሻው ፍልሚያ ከአድዋ ጦርነት በኋላ ተካሄደ። የከበባው አቅጣጫ:-
  • ራስ ወልደጊዮርግስ ከምስራቅ በኩል ኮንታ አደርገው ቦንጋ አንድራቻ ገቡ።
  • ራስ ተሰማ ጫካ ጫካውን ተጉዘው ቢጣ፣ ጫናዋቻ እንዲሁም በገሻ ድረስ ዘመቱ።
  • ደጃች ደምሴውም መሐሉን በጌራ በኩል በአባጅፋር እየተረዱ ተሻግረው በገዋታ በኩል ወደ መሀል ካፋ ዘለቁ። በግጭቱም ከፍተኛ የሕይወት ጥፋትና የንብረት ውድመት ተከሰተ።
አውሮፓውያን በነዚህ የካፋ ተራራዎች ስለተፈጸመው ጦርነት ድራማ የነበራቸው እይታ ወይም ስሜት ትንሽ ነበር። ብቻ ስለጦርነት ፍጻሜው አጭር ዘገባ አትመው እንደነበር ይታውሳል። ሆኖም ይህ ጸሀፊ ይህን እትም ሊያገኝ አልቻለም። ስለሆነም በአውሮፓውያንም ሆነ በኢትዮጵያዊያን በኩል ስለ ጦርነቱ ድራማ ጥልቀት ያለው ዘገባ ገና አልተገኘም። በዚህ ረገድ ወደፊት ለጸሀፊ ተውኔትና ለፊልም አቀናባሪዎች ስራ ለዛና ወዘና ያለው ገና ያልተቀዳ የታሪክ ምንጭ መኖሩን ላስታውስ እወዳለሁ።
ሆነም ቀረ ጊዜው በሰጣቸው ኃይል ሚዛን በልጠው በመገኘታቸው ምኒልክ ዘመቻቸውን አሳኩ። እናም እ. ኤ.አ. መስከረም 1897 የመጨረሻው የካፋ የቲዮ (የካፋ ንጉሰ ነገስት) አጼ ጋኪ ሻረቾ የጦር እስረኛ ሆነው ወደ አንኮበር ተውሰዱ። አብረዋቸው የነበሩት ውድ ባለቤታቸውም እ.ኤ.አ. በ1906 አረፉ።
Kumilachew
ቁምላቸው ገ/መስቀል አምቦ
ከአንኮበር የካፋ ዘውድ በካፎች በተሰረቀ ጊዜ በተመሳሳይ መልኩ እስረኛ የነበሩት ንጉስ አምልጠው ካፋ አገር ቢገቡ ሌላ ጦርነት ይፈጠራል የሚል ስጋት ስለተፈጠረ ከአንኮበር ወደ ደሴ ወሎ ተወስደው በንጉስ ሚካኤል ጦር ጥበቃ ስር ቆዩ። ሆኖም ልጅ ኢያሱ እንደንጉሱ ወደ አገራቸው (ካፋ) እንዲመልሱ ስልጣን እንዳያዙ ወስነውላቸው ነበር። ይሁን እንጂ የአቤቶ ኢያሱ ፍታዊና ዲፕሎማሲያዊ የፖለቲካ ስልት በተፈሪ መኮንን አሲረኞች በመቀጨቱ ሁሉ ነገር ተገለበጠ።
ስለሆነም የካፋ ንጉሰ ነገስት (ካፊ እቱዩ) አጼ ጋኪ ሻረቾ የመጨረሻው የካፋ ወርቅ ዘውድ ጫኝ፣ የወርቅ ዙፋን ባለቤት፣ የወርቅ በትር መንግስት ያዥ፣ ከትውልድ ወደ ትውልድ የሚተላለፍ የወርቅ የንግስና ቀለበት ጠባቂ ተወዳጅና ተመላኪው ንጉስ በችግር ኖረው ለሀገራቸው አፈር ሳይበቁ እ ኤ አ 1917 ሲያርፉ አስከሬናቸው ደብረሊባኖስ እንዲያርፍ ተደረገ። ከሁለት አሽከሮቹና ከጥቂት ንብረት በስተቀር ምንም ሀብት አልነበራቸውም። ልጃቸው በዛብህ ወደካፋ ሄዶ እንዲኖር ቢፈቀድለትም ከጥቂት ዓመታት በኋላ ግን እንደገና ታስሮ ወደ አዲስ አበባ ተወሰደ። ግን የሚገርመው ነገር ከአጼ ምኒልክ በኋላም የመጡት የኢትዮጵያ መሪዎች የካፋን ሀገር በቁጭትና በበቀል መግዛታቸው ነው።
(ከኖቾ ወደቡሾ)
source www.goolgule.com

Monday, March 17, 2014

የሀገራችንን ድንበር ለሱዳን መስጠቱን እንደሚቃወሙ በፊርማወ ያስመዝግቡ

የኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ ትግል ሸንጎ (ሸንጎ) 
Ethiopian People's Congress for United Struggle (Shengo) 
www.ethioshengo.org shengo.derbiaber@gmail.com 
መጋቢት 2፣ 2006 ( ማርች 10፣ 2014) 
የሀገራችንን ዳር ድንበር ለሱዳን አሳልፎ ለመስጠት በገዥው ህውሀት/ኢህአዴግ እና በሱዳን መንግስት መካከል 
እየተካሄደ ያለውን ሴራ እንቃወማለን፡፡ 
ይህ ሴራ የሚካሄደው ህዝብን በማይወክል ጠባብ ቡድን በመሆኑ ከኢትዮጵያ ህዝብ ጀርባ የሚፈጸመውን 
ማንኛውንም ውል እንደማንቀበል ካሁኑ እንዲታወቅልን ለተባበሩት መንግስታት፣ ለአፍሪካ ህብረት እና ለሌሎችም 
አለም አቀፍ ድርጅቶችና መሪወች የሚቀርብ የተቃውሞ ፊርማ በማሰባሰብ ላይ እንገኛለን። 
እርሰወም ስመወን በማስፈር የዚሁ ታሪካዊ እንቅስቃሴ አካል እንዲሆኑ በትህትና እንጠይቃለን። የናት ሀገራችን 
ኢትዮጵያ ዳር ድንበር ሲደፈር ሁሉም የሚችለውን ማድረግ ሀገራዊ ግዴታው ነው። 
http://www.ipetitions.com/petition/stop-secret-border-deal-between-ethiopia-and-Sudan
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር 
  Tel: 44 7937600756 , +1 9168486790 E-mail : shengo.derbiaber@gmail.com
source www.ethiomedia.com

Friday, March 14, 2014

በአሜሪካ የሚኖረው የሕወሐት ወንጀለኛ (ከኢየሩሳሌም አርአያ)

(ከኢየሩሳሌም አርአያ)
የሕወሐት አባል የሆነውና በአሜሪካ የሚኖረው ብስራት አማረ በርካታ ወንጀሎችን እንደፈፀመ የቅርብ
ምንጮች አጋለጡ። ሕወሐት በረሃ እያለ የባዶ 6 እስር ቤት ዋና ሃላፊ የነበረው ብስራት አማረ የኢ.ህ.አ.ፓ
አባላት የነበሩት እነ ፀጋዬ ገ/መድህን (ደብተራው) ጨምሮ በሕወሐት የተያዙትን በሙሉ ወረኢ ተብሎ
በሚጠራው ስፍራ በነበረ እስር ቤት በጅምላ አሰቃይቶ እንደገደላቸው ምንጮቹ አረጋግጠዋል።
በሺህ የሚቆጠሩ የትግራይ ሰዎች « ኢዲዩና ፊውዳል..» በሚል ባዶ 6 ተብሎ ይጠራ በነበረው እስር ቤት
ተሰቃይተው እንዲገደሉ የተደረጉት በብስራት አማረ መሆኑን የጠቆሙት ምንጮቹ ከዚህ በተጨማሪ
የድርጅቱን በርካታ አባላት እንዳስገደለ አያይዘው ገልፀዋል። እነተክሉ ሃዋዝ በዚህ ወንጀለኛ ከተገደሉት
ይጠቀሳሉ ሲሉ ያክላሉ። በ1983ዓ.ም ሕወሐት/ኢህአዴግ አገሪቱን ከተቆጣጠረ በኋላ የሟቹ የደህንነት
ሹም ክንፈ ገ/መድህን ምክትል የነበረው ብስራት አማረ ከቤተ መንግስት የጃንሆይ የነበረ ከፍተኛ ወርቅ
በመዝረፍ መውሰዱን ያጋለጡት ምንጮቹ በዚህ የዘረፋ ወንጀል ሆለታ እስር ቤት እንዲገባ መደረጉን
ያመለክታሉ። በነስብሃት ነጋና መለስ ዜናዊ ትእዛዝ እንዲፈታ ተደርጐ ወደ አሜሪካ የተሸኘው ብስራት
አሜሪካ ሲጓዝ የዘረፈውን ወርቅ ይዞ እንደነበረ ጉዳዩን በቅርብ የሚያውቁ ምንጮች በግርምት ይገልፃሉ።

ብስራት አማረ አሜሪካ ከመጣ በኋላ ቅርስ የሆኑትንና የዘረፋቸውን ወርቆች መሸጡንና አንዲት ሴት
ለማሻሻጥ የተቀበለችውን 1ኪሎ ወርቅ ከወሰደች በኋላ እንደካደችው ማወቅ ተችሎዋል። ብስራት አማረ
ስለዚሁ ጉዳይ ተበሳጭቶ የነገራቸው ምንጮች ማረጋገጫ ይሰጣሉ። የብስራት ታናሽ ወንድም የሆነውና
በደህንነት ቢሮ ይሰራ የነበረው ታጋይ ጠስሚ ( ጠስሚ -ትርጉሙ ቅቤ ማለት ነው) ከስራው በመልቀቅ
የአስመጪና ላኪነት ትልቅ ቢዝነስ መክፈቱን የጠቆሙት ምንጮቹ አክለውም፥ ድርጅቱ የተከፈተው
ብስራት አሜሪካ ከገባ በኋላ በላከለት ገንዘብ መሆኑን አስታውቀዋል። (ስለዚሁ ጉዳይ በ1995 ዓ.ም
በኢትኦጵ ጋዜጣ መረጃው ይፋ መደረጉና የብስራት ወንድም ቅቤ ኢትኦጵ ቢሮ ድረስ በመምጣት
የጋዜጣውን አዘጋጅ በድንጋጤ ተውጦ “ የራሴን ቢዝነስ ተቋም ነው፤ እነማን መረጃ እንደሚሰጧችሁ
አውቃለሁ። እባካችሁ የእኔንም፣ የወንድሜንም ስም አታንሱ? ” በማለት ተማጽኖ አቅርቦ ነበር።)

ብስራት አማረ ከሽማግሌው ስብሃት ነጋ ጋር ባለው የጠበቀ ግንኙነት ወደ ኢትዮጵያ ሲመላለስ መቆየቱን
ያወሱት ምንጮቹ፣ ወንጀለኛውና ዘራፊው መቀሌ ሄዶ አስገደ ገ/ስላሴን እንደከሰሰ አስታውቀዋል። የደርግ
ወንጀለኞች ከአሜሪካ በገዢው ፓርቲ እየተወሰዱ ነገር ግን የኢ.ህ.አ.ፓ አባላትንና ሌሎች ንጹሃን
ዜጎችን በጅምላ የፈጀና የአገር ቅርስ የዘረፈ ወንጀለኛ ጠያቂ ማጣቱ አስገራሚ ነው ብለዋል ምንጮቹ።

ጠያቂ አካል ካለ- በወንጀለኛው ብስራት አማረ ላይ ለመመስከር ፈቃደኛ መሆናቸውን አክለዋል። ይህን
ምስክርነትና ማረጋገጫ ሊሰጡ የሚችሉና በአሜሪካ የሚኖሩ ሶስት የቀድሞ የሕወሐት ሹሞች እንዳሉና
የብስራትን ወንጀል ጠንቅቀው የሚያውቁ መኖራቸውን አያይዘው ጠቁመዋል።
source Ethiopian media forum.

Wednesday, March 12, 2014

[የሚኒሶታው ደብረሰላም መድሃኔዓለም ጉዳይ] – ማን ለጠበቃ ፈረመ???

ሰላም ለሁላችሁ፤

ለሰላም እና ለአንድነት ከቆሙ ምዕመናን የተላለፈ መልዕክት፦
በቤተክርስቲያናችን መተዳደሪያ ደንብ መሠረት ቤተክርስቲያኑን ወክሎ ማንኛውንም ውለታ/ሰነድ መፈረም የሚችለው ሊቀመንበሩ ብቻ እንደሆነ በግልጽ ተቀምጧል። የእየአንዳንዱ የቦርድ አባል የሥራ ድርሻ በተዘረዘረበት አንቀጽ 6 ላይ ማን በቤተክርስቲያኑ ስም ሰነዶችን
መፈረም እንደሚችል ተደንግጎ እናገኛለን ። አንቀጽ 6 ክፍል 3 ሀ ተ.ቁ 7 እንዲህ ይላል፦
“ሊቀመንበሩ፦
7. ጠቅላላ ጉባኤው፤ የባለአደራዎች ቦርድና የሥራ አስፈጻሚው ኮሚቴ የተስማሙባቸውን ሰነዶችና ስምምነቶች ቤተክርስቲያኒቱን በመከወከል ይፈርማል”
ቤተክርስቲያኑን ወክያለሁ የምትለው ይህች ጠበቃ ግን ገና ሊቀመንበሩ በቦርድ ሕገወጥ ስብሰባ ታግደዋል ሳይባል ነው የቤተክርስቲያኑ ጠበቃ ነኝ ያለችው። ይህም ለሕጋዊው ሊቀመንበር በማያገባት ገብታ የሕዝብ ተምራጭ የሆኑትን ሊቀመንበር ከቦርድ ተባረዋል ብላ በጻፈችው ደብዳቤ ተጠቅሷል። እነርሱ ሊቀመንበር ያሉት እኛ ግን በሊቀመንበርነት የማናውቀው ሰውም ይህን ሰነድ የመፈረም ስልጣን የለውም። እነርሱም መርጠነዋል ያሉት ከዛ በሗል ነው። እናም የማርች 9ኙ ቤተክርስቲያኑ ተከሰሰ አዋጅ አጣብቂኝ ውስጥ የመግባታቸው ውጤት ነው። ድሮም ወያኔ ወንዝ አያሻግርም።
የእምነት ሕፀጽ የሌለባትን ቤተክርስቲያን በጥብጠው፣ ሲካፈሉት የኖሩትን ቅዱስ አገልግሎት እንደ መርገም ቆጥረው ቀኖና ያጎደለ ቤተክርስቲያን ነው ሲሉ የማይሰቀጥጣቸው፣ ሕዝቡን በማሸበር የፖለቲካ ተልእኳቸው ተከታይ የሚሆን መስሏቸው የሌለውን ችግር ፈጥረው ሰላማችንን ሲያምሱ መክረማቸውን
ያየ መድኃኔዓለም ቤቱን ባጸዳበት ቀን እነዚህንም ሊያጸዳ እያጻፋ አናገራቸው። በጥፋት ላይ ጥፋት በክስረት ላይ ክስረት ብቻ ስለሆነ ትርፉ እባካችሁ የበደላችሁትን ጌታ አና ኅዝብ ይቅርታ ጠይቃችሁ አርፋችሁ ተቀመጡ። የባሰ ሳይመጣ። ጊዜው ለዚህ የተመቸ ነውና።
ይህ ሕዝብ ሳይፈቅድና ሳያምንበት በቤተክርሲታኑ አቋም ላይ አንዳች ለውጥ አይመጣም!!! አሁንም ወደፊትም በአባቶች መካከል ያለው መለያየት እስኪወገድ ድረስ ከቤተክርስቲያናችን ከኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ሳይሆን ከስልጣን ሽኩቻ፣ በዘረኝነትና በሙስና ከተጨማለቀ አስተዳደር ገለልተኛ ነን !!! ወዳጆቼ የአስተሳሰብ ልዩነት እኮ እንዲህ በግትረኝነትና ለምን ፍርስርስ አይልም እያሉ የሚያራምዱት አይደለም። ሕዝብ ወሰነ። እናንተ ግን 40/50 ሰው ጎድሎ ነበርና በክፍተኛ ድምጽ የተወሰነውን ውሳኔ አንቀበልም ብላችሁ በማያዋጣ ጎዳና መጓዝ ጀመራችሁ። መጨረሻችሁም ይኽው ከፍተኛ ወጪ አስከተለ። አሁንም አስቡበት አያዋጣችሁም። ሽንፈትን መቀበል ከባድ ቢሆንም ሊመጣ ካለው ከባድ ሽንፈት ይሻላልና ክርስቲያን ከሆናችሁ ይብቃችሁ። ባስቸኳይ ኅዝቡ ባቀረበው አጀንዳ መሠረት ጠቅላላ ጉባኔ ጥሩ። ሕዝቡ ከፈለገ ትቀጥላላችሁ ካልፈለጋችሁ ደግሞ እንደመረጣችሁ ያወርዳችኋል።
እስኪ እንደ ክርስቲያን ይቅርና እንደሰው ለደቂቃ አስቡት? በዚህ ባመጣችሁት ጉዳይ ምክንያት ምን ተጠቀምን? ምን አተረፍን? ችግር ተፈታ? ተቃለለ? ወይንስ ተባባሰ? ገለልተኝነት ቀረ? የችግሩ ምንጭ ፖለቲካ ነው። ችግሩ የሚፈታውም ፖለቲካው የሆነ ለውጥ ሲያመጣ ነው ወይንም ሲለወጥ ነው። ማንም ቢዳክር የተለያዩት አባቶች ሳይስማሙ/ሳይታረቁ ይህ ችግር አይፈታም!!!

በደብራችን በደብረሰላምም ሆነ በተዋሕዶ እምነታችን ላይ ምንም ከወትሮው የተለየ የእምነት ችግር የለም!!! ችግሩ የአስተዳደርና የፖለቲካ ጣልቃ ገብነት ነው። የእምነት ችግር አለ ለሚል ሰው ግን እስካሁን በገለልተኛ ቢተክርስቲያናት የተካፈለውን መንፈሳዊ አገልግሎት ምን ሊያደርገው ነው? ንሰሐ ሊገባበት ነው? ከዚህ በኋላስ በገለልተኛ ቤተክርስቲያን ይገለገላል? በርግጥ ያየበት መነጽር ስሕተት እንደነበረ ካመነ ምንም አይደል። አለበለዚያግን ክርስትናው አጠያያቂ ነው። ለማንኛውም መድኃኔዓለም ልቦና ይስጣችሁ። እውነት የቤተክርስቲያን ነገር ካሳሰባችሁ ብዙ የሚሰራ ሥራ አልና እዛላይ ብንሰራ ይሻላል። እናም እባካችሁ ይብቃችሁ!!!
source ze-Habesha