Saturday, November 16, 2013

ዓለምአቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያውያን መብት በሳኡዲ አረቢያ Global Alliance for the Rights of Ethiopians in Saudi Arabia

ህዳር 6 ቀን 2006 ዓ/ም

 አስቸኳይ መግለጫ

በቅርቡ፤ በተከታታይና በሚዘገንን ደረጃ በሳውዲ አረቢያ በኢትዮጵያዊያን ላይ የሚካሄደውን እልቂት ለማስቆም ብሄራዊ
ግብረ ኃይል እአ በ November 12, 2013 በተደረገ አስቸኳይ ስብሰባ ተመሰርቷል።

በዓለም ዙሪያ የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን፤ ትውልደ ኢትዮጵያውያን ለሰብአዊ መብቶች፤ ለሰዎች ክብርና የህይወት ክቡርነት
የቆሙ ሁሉ የሳውዺ የጦር፤ የፖሊስ፤ የጥበቃና ሌሎች በመንግሥት የተደራጁ ወጣት ቡድኖች በሰላማዊ ኢትዮጵያዊያን ላይ
የሚያደርጉት ግድያ፤ አስገድዶ መደፈር፤ ግለሰቦችን በገመድ አንቆ ዛፍ ላይ መስቀል፤ ገረፋ፤ በሓያኛው መቶ ክፍለ ዘመን
ከሰለጠነ መንግሥት በማይጠበቅ ደረጃ ግለሰቦችኝ እንደ እንሰሳ አስሮ በመንገድ መጎተት ወዘተ ለህሊና የሚቀፍ ድርጊት።
እኛም በንፁሕ ኢትዮጵያዊያን ላይ መፈፀሙ አስቆጥቶናል፤ አሳዝኖላን፤ አበሳጭቶናል፤ ቀስቅሶናል፤ ለወገኖቻችን መብት
እንድንነሳና ከሚመለከታቸው ጋር አብረን ድምጻችንን እንድናሰማ አስገድዶናል። በመጀመሪያ ደረጃ የምንጠይቀው፤ የሳውዲ
መንግሥት ሃላፊነቱን በመወጣት ይህ አሰቃቂ እልቂት እንዲቆም ማድረግ ነው። ከዚህ ጋር አብረን የምናሳስበው ለሰብእነትና
ለሰው ክብር የቆመው የዓለም ህብረተሰብ ሁሉ ይህን አሰቃቂ ድርጊት ተቀዳሚነት በመስጠት እንዲቆም ማድረግ የሞራል
ሃላፊነት አለበት የሚል ነው። የኢትዮጵያዊያን ህይወት እንደ ማንኛውም ሰባዊ ፍጡር ትልቅ ዋጋ ያለው መሆኑን
እናሳስባለን።
ይህን የተቀደሰ ዓላማ ስኬታማ ለማድረግ የሚከተሉትን ለሰብአዊ መብት፤ ለሰው ክብርና ነጻነት፤ ለእውነተኛ እኩልነት
የቆሙ ሶስት ግለሰቦች በአሰባሳቢነት መርጠናል፤
1. አቶ አበበ ገላው
2. አቶ ብርሃኑ ዳምጤ (አባ መላ) እና
3. አቶ ታማኝ በየነ።
ኢትዮጱያዊያን፤ በተለይ ወጣት ወንዶችና ሴቶች በሳውዲ አረቢያና በሌሎች የመካከለኛው ምስራቅ አገሮች በገፍ
የሚሰደዱበትና በሰላም ሰርተው ለመኖር የሚፈልጉበት ምክንያት በአገራቸው የስራ፤ በሰላም የመኖር፤ የራሳቸውን ስራ
የመፍጠር፤ መብታቸውን የማስከበር እድል ስለሌላቸው ነው። ስለሆነም፤ የሳውዲ አረብያ የጥበቃ፤ ፖሊስና ወጣት አፋኝ
ቡድኖች በኢትዮጵያዊያን ላይ የሚደርጉት ግድያ፤ አፈናና ማሳደድ ከዚህ በፊት ታይቶ የማይታወቅ፤ ለህሊና የሚቀፍ፤
በተባበሩት መንግሥታት ውሎች የተከለከለ፤ የሰለጠነው ዓለም የማይቀበለው በሰብእነት ላይ የተፈፀመ ወንጀል ነው። ይህን
አሰቃቂ ድርጊት የአይን ምስክሮች፤ የቢቢሲ፤ የአልጀዚራና የግል ታዛቢዎች በቪዲዮ ቀርፀው ለዓለም ሕዝብ
አሰራጭተውታል። ከዚህ የበለጠ ምስክር ሊኖር አይችልም። የሳውዲ አረቢያ መንግሥት ሆነ ብሎ የሚያደርገው ህገ ወጥ
ድርጊት መሆኑን አንጠራጠርም፤ ስለሆነም፤ ይህን አሰቃቂ ተግባር ማቆም ያለበት የሳውዲ አረቢያ መንግሥት መሆኑን
እናሳስባለን።

ከላይ እንዳሳየነው፤ ኢትዮጵያዊያን አገራቸውን ለቀው እንዲሰደዱ፤ ሲሰደዱ አሰቃቂና ለህሊና የሚዘገንን ግድያ፤ እስራትና
ሌላ ኢ-ሰብአዊ ወንጀል የሚፈፀምባቸው ወደው አይደለም። አብዛኛው የኢትዮጵያ ወጣት ትውልድ በአገሩ ህይወቱንና
ቤተሰቡን የሚደግፍበት ስራ የለውም፤ የኑሮ ዋስትና የለውም። የሕግ የበላይነት ስለሌለ፤ ከሕግ ውጭ የሆነ አፈና፤ ግድያ፤
እስራት፤ ኢ-ሰብአዊ ቅጣት፤ የውስጥና የውጭ ስደት፤ መባረር ወዘተ እጣው ሆኗል። ስለዚህ ነው ብዙ ሽህ ኢትዮጵያዊያን
ብዙ ሽህ ብር ከፍለው ለህይወታቸው አደጋን የሚጋብዝ ጉዞ የሚያደርጉት። አሰቃቂ ሆኖ ያገኘነው፤ ኑሯችንን እናሻሽል
ይሆናል ብለው ያደረጉት ተስፋ ወደ ጨለማ መርቶ ለህይወታቸው መጥፊያ፤ ለአካለ ስንኩልነት፤ ለክብራቸው መገፈፊያ
ወዘተ ምክንያት መሆኑ ነው። ይህ በሃያ አንደኛው መቶ ክፍለ ዘመን የመጣ “የባርነት” ሁኔታ መፈጠሩን ያመለክተናል፤
መቆም አለበት የምንለው የእነዚህ ወገኖቻችን መዋረድ የሁላችንም ክብር መገፈፍ መሆኑን ስለምንረዳ ጭምር ነው።
ኢትዮጵያዊያን በያሉበት በመገናኛ ብዙሃን፤ በድህረገጾች፤ በሰላማዊ ሰልፍና በሌሎች መንገዶች የሚያሳዩት ጥረት የሚያኮራ
ጅምር ነው። በዚሁ መሰረት የሳውዲ አረቢያ መንግሥት የሚያደርገውን አሰቃቂ ግፍ ለዓለም ህብረተሰብ ለማጋለጥ፤
ወንጀሉን የፈፀሙ ሁሉ በሃላፊነት ለፍትህ ለማቅረብ የሚደረገው ተግባር በተከታታይና አስተማማኝነት ባለው ደረጃ
እንዲካሄድ ቆርጠን ተነስተናል። የተቋቋመው ግብረ ኃይል ዋና ሚና በሳውዲ አረቢያ የሚካሄደውን ወንጀል
ለሚመለከታቸው የዓለም ህብረተሰብ የሰብአዊ መብቶች፤ የፍትህ ተቋሞች፤ የለጋስ ድርጅቶችና ሃላፊዎች ማሳወቅ፤ ቅስቀሳ
ማድረግ፤ የገንዘብና ሌላ ቁሳቁስ ድጋፍ ለወገኖቻችን ለማቅረብ ጥረት ማድራግን ይጨምራል። በዚህም መሰረት፤ ግብረ
 ዓለምአቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያውያን መብት በሳኡዲ አረቢያ
Global Alliance for the Rights of Ethiopians in Saudi Arabia







ኃይሉ፤ እውቅና፤ ተቀባይነትና አስተማማኝ የሆኑ የሰብአዊ መብቶች ድርጅቶችን፤ ሊቆችን፤ ጠበቃዎችን ወዘተ፤ በመቅረብና
በመቀስቀስ፤ የሳውዲ መንግሥት በሰብአዊነት ላይ ያደረገውንና የሚያደርገውን ወንጀል (Crimes against humanity)


ለፍትህ ለማቅረብ የተቻለውን ሁሉ ያደርጋል። በተጨማሪ፤ በሳውዲ አረቢያ ያለውን ሁኔታ በቀጥታ ለመመራመርና
እውነተኛውን ዝርዝር ሁኔታና ስእል ለመገንዘብ አንድ ቡድን ለመላክ አቅዷል።
ይህ የተቀደሰና ሁሉም ኢትዮጵያዊያን፤ የሰው ክብርና መብቶች ደጋፊ የሆኑ ድርጅቶችና ግለሰቦች እንዲሁም መንግሥታት
በያሉበት የሚጋሩት አስቸኳይ ጥሪ ፋታ አይሰጥም። ግድያው፤ ገረፋው፤ እስራቱ፤ የሴቶች ክብር ድፍረቱ ወዘተ የሁላችንም
ስለሆነ ዓለም አቀፍ ጥረት ያስፈልገዋል። ሁላችን ሌሎችን በመቀስቀስ ይህ ግፍ በፍጥነት እንዲቆም በተግባር ማሳየት
የሞራል ግዴታችን ነው። ወንጀሉን የፈፀሙት የሳውዲ አረቢያ ባለስልጣናትና ሌሎች ተሳታፊዎች በሃላፊነት ተጠያቂ መሆን
አለባቸው። የሳውዲ መንግሥት ባለስልጣናት የኢትዮጵያዊያንን መብቶች ገፈው፤ ገድለው፤ አዋርደው፤ አሳደው፤ ሰቅለው፤
ክብር ገፈው በኢትዮጵያ ያላቸውን ዘላቂ ጥቅም ለማስከበር እንደማይችሉ ማመን አለባቸው። ይህን ማሳመን መቻል
አለብን።

የተፈጸመውን አሰቃቂ ግድያ፤ ድፍረትና ሰቆቃ ኢትዮጵያውያንና የዓለም ሕብረተሰብ እንዲያወግዝልን ድርጅታችን ጥሪውን
ያቀርባል። በተጨማሪም፤ በኢትዮጵያዊያን ስደተኞች ላይ አስከፊና ኢሰብአዊ ድርጊት የፈጸሙት ሁሉ ተጠያቂ እንዲሆኑ
እናሳስባለን። እንዲሁም፤ በመረጃና ተሞክሮ መጋራት፤ ኢትዮጵያውያንን ከሳውዲዎች ሰቆቃና ግድያ ለማትረፍ
ስለሚያስፈልገው እርዳታ ሁሉ ኢትዮጵያውያንና ለሰብአዊ መብት የሚታገሉ ድርጅቶች እንዲተባበሩልን ከአደራ ጋር
እንጠይቃለን።

ይህን ለማድረግ የምንችለው ለዚህ ዓላማ በያለንበት ስንነሳ፤ አብረን ተባብረን ስንሰራ፤ ለወገኖቻችን መቆማችንን በተግባር
ስናሳይ፤ ዜና፤ ሃሳብ፤ እውቀት፤ ልምድ፤ ስንለዋወጥ፤ የገንዘብ ሆነ ሌላ አስተዋፅኦ ስናደርግ ነው። ይህን በተቀነባበረና ስልት
ባለው መንገድ ከሰራን በወገኖቻችን ላይ የደረሰውንና የሚደርሰውን እልቂት ለማቆም እንችላለን። የወገኖቻችንን ክብር
በመታደግ፤ የራሳችንን ክብር ለማስከበር እንችላለን።



ሁሉም ህይወት እኩል ዋጋ አለው!!!


Contact information:

Telephone: (877)RING-ETHIOPIA or (877)746 -4384

Email address: Alliance4rightsofethiopians.sa@gmail.com
source quatero

Thursday, November 14, 2013

በሳውዲ አረቢያ በሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ላይ የሚደርሰው ሰቆቃ አሁኑኑ ይቁም!!!

Posted by 
በሳውዲ አረቢያ በሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ላይ የሚደርሰው መከራ መስማት ህሊና መሸከም ከሚችለው በላይ ሆኗል። ኢትዮጵያዊን እህቶቻችን ወንድሞቻችን በአሰቃቂ ሁኔታ እየተገደሉ፤ አካሎቻቸው በስለት እየተቆራረጠ፤ እየተደበደቡና እየተደፈሩ ነው።
ይህ ሁሉ የሚፈፀው በሪያድ፣ ጂዳና አዲስ አበባ የሚገኙ የወያኔ ዲፕሎማቶች መልካም ፈቃድና ሙሉ ተባባሪነት መሆኑ ደግሞ ይበልጥ የሚያንገበግብ ነው። ወያኔ ለአረብ ሀብታም ሸሪኮቹ ለም መሬቶቻችንን ሰጥቶ ኢትዮጵያዊ በአገሩ ሠርቶ የእለት ጉርሱን መሸፈን የማይችልበት ደረጃ ላይ እንዲደርስ አደረገው። ቀጥሎ ደግሞ በሺዎች የሚቆጠሩ ልጃገረዶችና ወጣት ኢትዮጵያንን እየደለለ ከባርነት ላልተሻለ ግርድና አሳልፎ ሰጣቸው። ይህ ሁሉ ግፍ አልበቃ ብሎ “በሏቸው፤ ቀጥቅጧቸው፤ ህገወጦች ናቸው” እያለ በወገኖቻችን ላይ የሚደርሰውን ሰቆቃ በአጋፋሪነት እያስተናገደ ነው።
በኩየት በሚገኙ ኢትዮጵያዊያን ላይ ተመሳሳይ ሰቆቃ ሊደርስ የሚችል መሆኑ ምልክቶች እየታዩ ነው። በኩዌት ያለአንዳች ምክንያት ቁጥራቸው በአንድ ሺህ በላይ የሆኑ ኢትዮጵያዊያን በድንገት ከሥራ ተባረዋል። እዚህም የወያኔ እኩይ እጆች እንዳሉት መረጃዎች አሉ። በሌሎች የመካከለኛው ምሥራቅ አገሮች የሚገኙ ኢትዮጵያዊያንም ሕይወታቸው በዘወትር ስጋት ላይ ወድቋል።
የኢትዮጵያዊያን እጣ ፈንታ በአገር ውስጥም ከአገር ውጭም ሰቆቃና እንግልት መሆኑ የሚያሳዝን ብቻ ሳይሆን የሚያስቆጭ፤ ለመራራ ትግል የሚያነሳሳም ነው። ለአገሩ ሕዝብ የሚቆረቆር መንግሥት ኑሮን ቢሆን ኖሮ ሕይታችን እንዲህ የተመሰቃቀሰ ባልሆነም ነበር።
ግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ የሳውዲ አረቢያ እና ሌሎችም የመካከለኛ ምሥራቅ አገራት መንግሥታት ለኢትዮጵያዊያን እህቶቻንና ወንድሞቻችን ሰብዓዊ ክብር እንዲሰጡ አበክረን እናሳስባለን። ሰብዓዊ መብቶችን መድፈር ዓለም ዓቀፍ ወንጀል መሆኑን ልንነግራቸው እንፈልጋለን። በወገኖቻችን ላይ የሚደርሰው ሰቆቃ አሁኑኑ ይቁም!!! ሰቆቃ ፈፃሚዎች ለፍርድ ይቅረቡ!!!
በተቻለው ፍጥነትና ባገኘነው እድል ሁሉ ተጠቅመን ሕይወታቸው አደጋ ላይ ላሉት ወገኖቻችን እንድንደርስ ግንቦት 7 ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ጥሪ ያደርጋል።
በኢትዮጵያዊያን ላይ የሚደርሰው ሰቆቃ በዘላቂነት የሚወገደው ወያኔ ከሥልጣን ተባሮ የኢትዮጵያ ሕዝብ የመረጠው መንግሥት ሲያስተዳድር በመሆኑ ለዚህ ታላቅ ግብ በኅብረት እንነሳ።
በወገኖቻችን ላይ የሚደርሰው ሰቆቃ ይቁም!!
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!

Monday, November 11, 2013

ኢህአዴግና የሃይማኖት ነፃነት (ተመስገን ደሳለኝ)

ኢህአዴግና የሃይማኖት ነፃነት

…ኢሠፓ መራሹ መንግስት በኢህአዴግ ከተተካ ጥቂት ወራት ቢያልፈውም፣ የተራዘመው የእርስ በእርስ ጦርነት
ያልደረሰባቸው በደቡብ ኢትዮጵያ የሚገኙ አንዳንድ ከተሞችን ገና በቅጡ አልተቆጣጠራቸውም፤ በአናቱም
በኢሠፓ መንግስት ሽንፈት ሳቢያ እንዲበተን ከተገደደው የሀገሪቱ መደበኛ ወታደር፣ አብዛኛው ከእነ ትጥቁ
የትውልድ መንደሩንና ቤተሰቡን መቀላቀሉ በሀገሪቱ ላይ ከባድ ፍርሃት አንብሯል፤ በሰላም ወጥቶ ለመመለስ
እርግጠኛ መሆን የማይቻልበት ከበባዊ አየርም አስፍኗል፡፡ በበርካታ ቦታዎች ተጠንተውና ታቅደው የሚፈፀሙ
ወንጀሎችም፣ ከአምስት እስከ አስራ አምስት በሚደርሱ ወታደሮች የተደራጁ ልዩ ልዩ ህገ-ወጥ ቡድኖች
በየማዕዘኑ እያቆጠቆጡ መሆኑን አመላክቷል፡፡

በሌላ በኩል ደግሞ የአዲስ አበባ ቆዳ ስፋትና የነዋሪዎቿ የአኗኗር ዘይቤን በቀላሉ ለመልመድ የተቸገሩት
‹ተጋዳላዮች›፣ ለትንሽ ትልቁ ግርግር ጠብ-መንጃን እንደ መፍትሄ መምረጣቸው ችግሩን አባብሶታል፤ ጉዳዩ እያሳሰባቸው የሄደው
የኢህአዴግ ዋነኛ መሪዎችም እንዲህ አይነት አለመረጋጋቶችንና ስርዓት አልበኝነቶችን ለመቆጣጠር የመንፈሳዊ መሪዎች አስተዋፅኦ ወሳኝ
መሆኑን ከስምምነት ላይ ደርሰዋል (እንደቀድሞው ስርዓቶች ሁሉ ‹ለቅብሉነት› ከሚጠቀሙበት በተጨማሪ ማለት ነው)፤ ይሁንና
በመንበሩ ላይ የነበሩት አቡነ መርቆርዮስ ሀገር ለቀው እንዲወጡ በመደረጉ ክፍተት ተፈጥሯል፡፡

ይህን ጊዜም ነው ከ1973 ዓ.ም. ጀምሮ መኖሪያቸውን አሜሪካን ሀገር ያደረጉ አንድ መንፈሳዊ አባት ወደ ኢትዮጵያ እንዲመጡ
የተወሰነው፤ በጥሪው መሰረትም ወደ ሀገራቸው ሲገቡ መንግስት የክብር አቀባበል አደረገላቸው፤ እኚህ ሰው ዛሬ በፓትርያርኩ መንበር
የተቀመጡት አቡነ ማቲያስ ነበሩ፡፡ ሆኖም ከሳምንት ሽር-ጉድ በኋላ አቡኑ የኢዲዩ አባል እንደነበሩ በአመራሩ አካባቢ ወሬው በስፋት
መሰራጨቱ ያልተጠበቀ ዱብ-ዕዳ አስከተለ፡፡ ምክንያቱ ደግሞ ኢህአዴግ እና ኢዲዩ በ1970ዎቹ መጀመሪያ ትግራይና ጎንደር ውስጥ
በርካታ መስዋዕትነት ያስከፈለ ውጊያ ማድረጋቸው ብቻ አይደለም፤ የመጀመሪያዎቹ ሊቀ-መንበሮች ስሁል ገሰሰና መሀሪ ተክሌ (ሙሴ)
‹‹የተገደሉት በኢዲዩ ነው›› የሚለው ወሬ በድርጅቱ ውስጥ ከጫፍ ጫፍ የተናኘና የታመነበት ጉዳይ መሆኑ ነበር፤ በዚህም ላይ የህወሓት
መሪዎች ግራ ዘመምነት ተደማምሮ አቡነ ማቲያስ በወቅቱ ወደ ታሪክነት ከተቀየረ ዓመታትን ባስቆጠረው ‹‹ኢዲዩ›› ተፈርጀው፣
ከታጩበት የ‹ፕትርክና መንበር› ተገፈተሩ፡፡

ከዚህ በኋላ ነበር አብላጫውን የትጥቅ ትግል ዘመን በአሜሪካ ያሳለፉት አሰፋ ማሞ እና ብርሃነ ገ/ክርስቶስ ‹ውድብ› የሰጠቻቸውን
ተልዕኮ ተቀብለው ወደ ዋሽንግተን ዲሲ ያመሩት፤ እናም ቀድሞም ትውውቅ ወደ ነበራቸው ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ዘንድ ሄደው
ለ‹ፕትርክና ወንበር› መታጨታቸውን አበሰሯቸው፡፡ በእንዲህ ያለ መንገድ መንግስት የቀባቸው ታጋዩ አባ ጳውሎስም እስከ ህልፈታቸው
ድረስ አወዛጋቢ መሪ ሆነው ዘልቀዋል (በነገራችን ላይ በአሜሪካን ሀገር ለመጀመሪያ ጊዜ ከሲኖዶሱ ተነጥሎ የቆመ ቤተ-ክርስቲያን
የመሰረቱት አቡነ ጳውሎስ እንደነበሩ ይነገራል፡፡ አቡኑ ደርግ ለጥቂት አመት አስሮ ከለቀቃቸው በኋላ ወደ አሜሪካ ሄደው የፈጣሪያቸውን
ሰማያዊ መንግስት ሲሰብኩ ቆይተው፣ የህወሓት ሠራዊት ክንዱ እየበረታ በቁጥጥሩ ስር ያዋላቸው ከተሞችም እየበዙ ሲሄዱ፣ እርሳቸውም
ስብከታቸውን ወደ ትግርኛ ቋንቋ ከመቀየራቸውም በላይ፣ ለ‹ነፃ አውጪ›ው ድርጅት የገንዘብ ድጋፍ ያሰባስቡ ጀመር፡፡ የስርዓት ለውጥ
መደረጉን ተከትሎም በፖለቲከኞች በተቀነባበረ ሴራ ከአቡነ ጳውሎስ ጋር ቦታ የተለዋወጡት አቡነ መርቆርዮስም፣ እዛው አሜሪካን ሀገር
‹ተተኪ›ያቸው የጀመሩትን ብሔር ተኮርና ከሲኖዶሱ የተገነጠለ ቤተ-ክርስቲያን አስፋፍተው ዛሬ ለደረሰበት ‹የጎንደሬ ማሪያም›፣ ‹የትግሬ
ገብርኤል›… ለተሰኘ አሳፋሪ ክፍፍል ዳርገውታል፡፡ በርግጥ ለአቡኑ ከሀገር መባረር የኢህአዴግ እጅ እንዳለበት እንድናምን የሚያስገድደን
በቅርቡ ታምራት ላይኔ ‹‹በእኔ ፊርማ ነው ያባረርናቸው›› ማለቱን ዊክሊክስ ካደረሰን መረጃ በተጨማሪ፣ በትጥቅ ትግሉ ዘመን ህወሓት
በተቆጣጠራቸው በትግራይና ወሎ ነፃ መሬቶች በሚገኙ ከተሞች ያሉ ነዋሪዎችን ቀስቅሶና አደራጅቶ ፓትርያርኩ ላይ ‹‹ሽጉጥ ታጣቂ
ጳጳስ››፣ ‹‹ቀይ ደብተር ያለው /ለኢሠፓ አባላት የሚሰጥ ነው/ የሸንጎ ተወካይ››… የመሳሰሉትን መፈክሮች እያሰሙ በተቃውሞ ሰልፍ
እንዲያወግዟቸው ማስተባበሩን ስናስታውስ ነው)

 ዛሬስ የሃይማኖት ነፃነት የት ድረስ ነው?
ከላይ ታሪክን ወደ ኋላ መለስ ብዬ በደምሳሳው ለመጠቃቀስ እንደሞከርኩት፣ ኢህአዴግ በሃይማኖት ጉዳይ እጁን ጣልቃ ማስገባት
የጀመረው ክንዱ ሳይፈረጥም፣ ገና በርሃ ሳለ ነበር፡፡ በዚህ ሁኔታ የተጀመረው ጣልቃ-ገብነት ዛሬም ድረስ ተባብሶ ቀጥሏል፤ ምንም እንኳን
በሃይማኖት ጉዳዮች ጣልቃ እንደማይገባ በደፈናው ከህገ-መንግሥቱ አንቀፅ 11ን በመጥቀስ በተደጋጋሚ ለማስተባበል ቢሞክርም፣
ያለፉት ዓመታት ተጨባጭ ተግባሮቹ የሚመሰክሩት ግልባጩን ነው፡፡ ድርጅቱ ራሱም ቢሆን ጥያቄው በተነሳ ቁጥር ከህገ-መንግሥቱ
አንቀፅ 11ን የሚጠቅሰው ለማጭበርበሪያነት እንጂ ህጉ ገቢር አለመሆኑን ሳይረዳ ቀርቶ አይደለም፡፡ ተፈራ ዋልዋም በ1998 ዓ.ም
ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ህዳር/ታኀሣሥ ወር ከታተመችው ‹ሐመር› መፅሄት ጋር ባደረገው ቃለ-መጠይቅ ጉዳዩን አስመልክቶ የሰጠው አስተያየት የኢህአዴግን
አጭበርባሪነት ፍንትው አድርጎ የሚያሳይ ነው፡-

‹‹ኢህአዴግ እኮ የሚመራው መንግስት፣ በደርግም ጊዜ፣ በኃይለ ሥላሴም ጊዜ እንደ ሚታወቀው ‹የቤተ-ክርስቲያን ሥራ አስኪያጅ
ሹምልን› ተብሎ ተጠይቆ ‹የለም ራስዋ ቤተ-ክርስቲያኒቱ ትሾማለች እንጂ እንደ ቀድሞው መንግስት አይሾምላችሁም› የሚል መልስ የሰጠ
መንግሥት ነው፡፡››

 በህዝበ ሙስሊሙ ተመርጦ ለእስር የተዳረገው የኮሚቴ አባላትም በአንድ ወቅት ለሚመለከተው የመንግስት ባለስልጣን የፃፈው ደብዳቤ
ጣልቃ ገብነቱን በግልፅ ያሳያል፡-

‹‹መንግስት እንደ መንግስት ህዝቡ ተበድያለሁ፣ ምርጫ ይካሄድ፣ የመጅሊሱን አመራር አላመንኩበትም፣ አልመረጥኩትም፣ ውክልና
የለውም እና ህገ ወጥ ነው ያለውን አካል ህገ ወጥነቱ እንዲረዝም ምርጫውን እሱው እንዲያካሄድ መወሰን ህዝብን ግራ አጋቢ ነው››

ስርዓቱ በሃይማኖት ጉዳዮች ላይ ጣልቃ እንደማይገባ ለማሳመን ይህን ያህል ቢዳክርም፣ በቅርቡ ‹‹የፀረ-አክራሪነት ትግል፣ የወቅቱ ሁኔታና
ቀጣይ አቅጣጫዎች›› በሚል ርዕስ የተዘጋጀው ባለ 44 ገፅ ሰነድ፣ መንግስት በዘወርዋራ በሃይማኖት ጉዳይ ጣልቃ መግባቱን ሙሉ
በሙሉ የሚያምን ሆኖ አግኝቸዋለሁ፡-

‹‹የመንግስት መዋቅራትን ሴኩላር መንግስት መሆናችንን አውቆ የመንግስትን መዋቅር ተጠቅሞ የራሱን ሃይማኖት መሰረት ያደረገ
አገልግሎት ከመስጠት ሙሉ በሙሉ ያልፀዳ መሆኑን የተለያዩ ጥቂት የማይባሉ ገሐድ የወጡ መገለጫዎች አሉ፡፡ እንዲያውም የትኛውም
አክራሪ ኃይል ከመዋቅር (ከመንግስት) አካል ‹በርታ› ሳይባልና ‹ሽፋን› ሳይሰጠው የሚንቀሳቀስ እንደሌለ በገሐድ አማኞቹ ይገልጻሉ፡፡››

መቼም ይህንን ያነበበ ዜጋ መረጃው የተገኘው በመንግስት ከተዘጋጀ ሰነድ ሳይሆን በ‹ኒዮ ሌብራሊስት›ነት ከተፈረጁት እነ‹ሂዩማን ራይት
ወች› እና ‹አምኒስቲ ኢንተርናሽናል› ቢመስለው አይደንቅም፤ ሀቁ ግን ይኸው ነው፡፡ አገዛዙ ላለፉት ሃያ ሁለት ዓመታት ‹መንግስትና
ሃይማኖት› እንዲለያዩ ማድረጉን ሲደሰኩር ከመቆየቱም በላይ በኃይማኖት ጉዳይ ጣልቃ መግባቱን የዘገቡ ጋዜጠኞችን ከስሶ ዛሬም ድረስ
ፍርድ ቤት እያመላለሳቸው እንደሆነ ይታወቃል፡፡ ከዚህ አንፃር ይመስለኛል አለም አቀፍ ማህበረሰብን ጨምሮ በርካታ ኢትዮጵያውያን
በእስር ላይ የሚገኙት የእነ አቡበከር መሀመድ ክስ፣ የሼህ ሁሴን ኑር ግድያ፣ በማህበረ ቅዱሳን ላይ እየተሰነዘሩ ያሉ ውንጀላዎችና መሰል
ፍረጃዎችን አምኖ ለመቀበል የተቸገሩት፡፡

 ያም ሆነ ይህ ሃይማኖትን ብቻ ሳይሆን እድርና ዕቁብንም ሳይቀር ‹ካልተቆጣጠርኩ ሞቼ እገኛለሁ› በሚል የቁጥጥር ልክፍት የተያዘው
ኢህአዴግ፣ በተለይም ‹‹99.6 ድምፅ አግኝቼ አሸንፌያለሁ›› ብሎ ካወጀበት ከምርጫ 2002 ማግስት ጀምሮ ‹‹አናት ላይ ከተቀመጡ
መሪዎቻቸው በቀር ሙሉ በሙሉ አልተቆጣጠርናቸውም›› የሚላቸውን የእስልምናና የኦርቶዶክስ ክርስትና እምነትን ዋነኛ አጀንዳው
አድርጎ እየሰራ ለመሆኑ በርካታ መረጃዎች አሉ፡፡ በ2003 ዓ.ም. ህዳር ወር ‹‹የአምስት አመት የእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድና
የኢትዮጵያ ህዳሴ›› በሚል ርዕስ በአቶ መለስ ዜናዊ ተሰናድቶ የተሰራጨው ጥራዝ፣ የስርዓቱን ቀጣይ አካሄድና ይህንን ሁናቴ የሚያሳይ
ከመሆኑም በተጨማሪ፣ ዛሬም ድረስ በሃይማኖት ጉዳዮች ላይ መንግስት የሚያዘጋጃቸው ስልጠናዎችም ሆኑ ጥናታዊ ፅሁፎች መነሻ
ሃሳባቸው ይኸው ዳጐስ ያለ ጥራዝ እንደሆነ ይነገራል፡፡

 ጥራዙ የእምነት ተቋማትን በተመለከተ ከገጽ 128-132 ያካተተው ሃሳብ፣ ለኪራይ ሰብሳቢነት ዋነኛ ምክንያት ‹‹የሃይማኖት
አክራሪነት›› መሆኑን ከጠቃቀሰ በኋላ፣ ችግሩን ‹‹ተኪ የሆነ ልማታዊ አስተሳሰብ›› በማምጣት ማስወገድ እንደሚቻል ይመክራል፡፡
ይህንን ከግብ ለማድረስ ደግሞ ሚዲያዎችንና ተያያዥነት ያላቸውን ማህበራት መጠቀሙ አዋጭ እንደሆነ ይተነትናል፡፡ የኢህአዴግ አባላት
በየእምነት ተቋሞቻቸው ያሉ ማህበራትን በአይነ ቁራኛ መከታተል እንዳለባቸውም ያሳስባል፡- ‹‹(አባላት) ከእምነት ተቋማት ውጭ
ባላቸው አደረጃጀት አማካይነት በሰፊው መስራት አለብን››፡፡ በርግጥም የእስልምና እምነት ተከታዮች ‹‹የሃይማኖት ነፃነት ይከበር››
የሚል ተቃውሟቸውን ባጠናከሩበት ሰሞን፣ አዲስ አበባን ጨምሮ በተለያዩ ክልሎች የሚገኙ ሙስሊም አባላቱን ለብቻ እየሰበሰበ
እንቅስቃሴውን የማክሸፍ ስራ መስራት ግዴታቸው መሆኑን የሰበከው ከዚሁ መለስ ዜናዊ አዘጋጅቶት ከነበረው ጥራዝ ነው ብሎ
መከራከር ይቻላል፡፡

ከጣልቃ ገብነት ወደ ጠቅላይ ተቆጣጣሪነት

 በዘወርዋራም ቢሆን በሃይማኖት ጉዳይ ጣልቃ መገባቱን ሙሉ በሙሉ የሚያምነው ከላይ የተጠቀሰው ሰነድ በሀገሪቱ ‹‹የሃይማኖት
አክራሪነት›› መከሰቱን ካተተ በኋላ፣ ዋነኛ ተጠያቂዎች አድርጎ ያቀረበው እንደወትሮው ሁሉ ለተደጋጋሚ መሸማቀቅ የተዳረጉትን
መንፈሳዊ መሪዎችንና ማህበራትን ሳይሆን መንግስትን ነው፡-
‹‹የመንግስት መዋቅራችን አካል ሆነው አክራሪነቱን በድብቅም/በገሐድም የሚደግፍ አካል በፌዴራልም በክልልም ከሞላ ጎደል የሚታወቁ
ናቸው፡፡ እነዚሁ አካላት በተቻላቸው ሁሉ በመድረክ ጤናማ እየመሰሉ የሚኖሩ ናቸው፡፡ የፀረ-አክራሪነቱን ትግል ማጧጧፍ
የሚፈልገውን የመዋቅር አካልም ይሁን የህዝብ አካል በተደራጀና በመረባቸው አማካኝነት ከፍተኛ ጫና የሚያሳድሩ፤ የተቋማቸውን ምቹ
ሁኔታ ተጠቅመው በፀረ-አክራሪነት የሚንቀሳቀሱትን አካል የሚቀጡ፣ አሉባልታ እየፈጠሩ የሚያሸማቅቁ፣ ሆን ብለው ድጋፍ የሚነፍጉና
በሐሰት ምስክርም ጭምር ዜጐችን የሚያሳስሩ ናቸው፡፡ የመንግስትን አቅሞች ተጠቅመው አክራሪነትን የሚያስፋፉና ከአክራሪነት
እንቅስቃሴ ጋር በተለያዩ ጥቅሞች የተሳሰሩ ናቸው፡፡››

እነሆም በእንዲህ አይነቱ የውንብድና ተግባር የተሰማሩ ባለስልጣናት የተሰባሰቡበት፣ ውንብድናው መኖሩንም የሚያምን መንግስት
አንድም ተጠያቂዎቹን ለህግ አሳልፎ አለመስጠቱ፣ አሊያም ሥልጣኑን በፍቃዱ አለመልቀቁ በሀገር ላይ ሊያስከትል የሚችለውን አደጋ
ለመረዳት ነብይነትን አይጠይቅም፡፡ በአናቱም ስርዓቱ ለህግ የበላይነት ተገዥ አለመሆኑን የሚያሳየው በዚህ ደረጃ ‹‹ችግሩን
ተረድቸዋለሁ›› እያለም እንኳ፣ ዛሬም የቅጣት በትሩን ያሳረፈው ከመዋቅሩ ጋር አንዳችም ንክኪ በሌላቸው መንፈሳዊ መሪዎች ላይ መሆኑ
ነው፡፡ በርግጥ ይህ አይነቱ አሰራር ከአምባገነን አስተዳደር መገለጫዎች አንዱ ነው፡፡ ኢህአዴግም ያለፉትን አራት ምርጫዎች ጨምሮ
በተለያየ ጊዜ የዴሞክራሲም ሆነ የሰብዓዊ መብትን በአደባባይ መጣስ፣ የሀሰት ክሶችንና ፍረጃዎችን እንደ ምክንያት መጠቀም ነባር ስልቱ
እንደሆነ ይታወቃል፡፡ በማህበረ ቅዱሳን ላይ እየዘረዘረ ያለው የፈጠራ ውንጀላ እና ለሙስሊሙ ጥያቄ ‹‹መፍትሄ አፈላላጊ›› ተብለው
በተመረጡት የኮሚቴ አባላት ላይ የወሰደው እመቃ መግፍኤ ይኸው ነው፡፡

ሌላው ቀርቶ ከዚህ ቀደም በተቃዋሚ ፓርቲ አባላት ላይ ለሚፈፅመው የግፍ ግድያዎች ይሰጥ የነበረውን ምክንያት በመንፈሳዊ ሰዎችም
ላይ ያለአንዳች የይዘት ለውጥ ለመጠቀም አላመነታም፡፡ እንደሚታወሰው በድህረ-ምርጫ 97 በአምቦና በኢተያ በታጣቂዎች የተገደሉትን
የኦህኮ አባላት ከተፈጥሮ ህመም ጋር አያይዞት ነበር፡፡ በያዝነው ዓመት ጥቅምት ወር መጀመሪያ በተካሄደው የሲኖዶሱ ጉባኤ ላይ ደግሞ
የምዕራብ ወለጋና አሶሳ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ አቡነ ሄኖክ ‹‹ቤጊ›› ወረዳ በመንግስት ባለስልጣናት ተፈፀመ ያሉትን ግድያ ለፌደራል
ጉዳዮች ሚኒስትር ተወካይ፡-

‹‹በቤተ-ክርስቲያን 70 ሜትር ርቀት ላይ የሌላ እምነት ተከታዮች የራሳቸውን ቤተ-ክርስቲያን እንዲሰሩ መፈቀዱን ከተቃወሙት መካከል
አንድ ዲያቆን ተደብድቦ በሶስተኛው ቀን ህይወቱ ሲያልፍ ‘በወባ በሽታ ነው የሞተው’ ተብሎ ለፍርድ ቤቱ የሐሰት ማስረጃ ከዶክተሩ
እንዲቀርብ ታዘዘ፡፡›› ማለታቸውን መጥቀሱ ለጉዳዩ አስረጂነት በቂ ይመስለኛል፡፡

የሆነው ሆኖ አገዛዙ በዘረጋው ግዙፍ መዋቅሩ ውስጥ ያልታቀፉ ማህበራትንም ሆነ የሃይማኖት ተቋማትን የስጋት ምንጭ አድርጎ ማየቱ፣
በእምነት ነፃነት ላይ ጣልቃ ለመግባትም ሆነ ምንም አይነት ገለልተኛ ተቋማት እንዳይኖሩ እንቅልፍ አጥቶ መስራቱን ያሳያል ብዬ
አስባለሁ፤ በሚቆጣጠራቸው የኤሌክትሮኒክስና የህትመት ሚዲያዎች ቀን-ከሌት የፕሮፓጋንዳ ከበሮ የሚመታበት የ‹አክራሪ›ነት ፍረጃም
መነሾው ይህ ይመስለኛል፡፡ ሰነዱን ከዚህ ቀደም ካየናቸው ለየት የሚያደርገው፣ በመንግስት መዋቅር ውስጥ አሉ ከሚላቸው ወንበዴዎች
በተጨማሪ የሚከስሳቸውን ማህበራት በደፈናው ‹‹በክርስትና እምነት ውስጥ ያሉ›› ብሎ አለማለፉ ነው፤ ቃል በቃል እንዲህ ይላልና፡-
‹‹በማሕበረ ቅዱሳን ውስጥ የመሸጉ የትምክህት ኃይሎች፣ ጽንፈኛ የፖለቲካ ኃይሎች አካል በመሆን በጋዜጣና በመጽሔት ህዝባችንን
ለአመፅና ሁከት ለማነሳሳት ከፍተኛ ጥረት አድርገዋል፡፡ …በራሳችንም ኃይል እንደሌላው ሰልፍ ልንወጣ ይገባል በሚል የአመፅና የሁከት
ቅስቀሳ ለማድረግ ይፈልጋሉ፡፡››

ይህ ሁኔታ መንግስት መንፈሳዊ ማህበራትን ጠቅልሎ ለመቆጣጠር በመፈለጉ ለተቃዋሚዎች ያሰመረውን ‹ቀይ መስመር› መጣሱን
ያሳያል፡፡ አስገራሚው ጉዳይ ደግሞ የሃይማኖት ተቋማትን የፖለቲካ መሳሪያ አድርጎ መጠቀሙ አልበቃ ብሎት፣ ወደ ማህበራቱ መዞሩ
ነው፤ በገሀድ እንደሚታወቀው የክርስትናም ሆነ የእስልምና መንፈሳዊ መሪዎች በተለያየ ጊዜ ከስርዓቱ ጎን ተሰልፈው ‹ናዳን ለመግታት›
ያደረጉት አበርክቶ በቀላሉ የሚገመት አለመሆኑ ነው፡፡ በርግጥም ‹‹የቄሳርን ለቄሳር›› በሚል አስተምህሮ የሚያድሩ፣ ደሞዛቸው በምድር
ያልሆነ መንፈሳዊ አባቶች በድህረ ምርጫ 97 ህፃናትን ሳይቀር በጥይት የፈጀውን ስርዓት ማውገዝ ቀርቶ መምከር ያለመፈለጋቸው
ምክንያት ፍርሃት ብቻ ሳይሆን፣ የግል ጥቅምን ታሳቢ ያደረገው ግንኙነታቸው ያሳደረው ተፅዕኖ ይመስለኛል፡፡ ከቅዱሳን መጽሐፍት
ይልቅ፣ አብዮታዊ ዴሞክራሲን ‹አዳኝ› አድርገው የመቀበላቸው መግፍኤ ይኸው ነው፡፡ ኢህአዴግም ‹ነገረ መለኮት›ን ለሲኖዶሱና
ለመጅሊሱ አስከማስተማር ድረስ የደፈረው፣ የእነርሱ ‹ለሁለት ጌታ› መገዛት ነው፤ ለፈጣሪና ለገንዘብ፡፡

 የሲኖዶሱ እና የመንግስት ፍጥጫ
 በኦርቶዶክስ ክርስትና እምነት ዶግማ ‹‹ሲኖዶስ›› ከፍተኛውን ስልጣን የሚይዝ ሲሆን፣ ፓትርያርክንም የመሾምና የመሻር ስልጣን
አለው፡፡ ሆኖም ይህ የላዕላይ መዋቅር እስከ አቡነ ጳውሎስ ህልፈት ድረስ ለእርሳቸውም ሆነ ለስርዓቱ ሰጥ-ለጥ ብሎ የሚገዛ ‹ጥርስ
የሌለው አንበሳ› በመሆኑ ለትችት ከመዳረጉም በላይ በአማኞች ዘንድ ለመንፈሳዊ አባቶች የሚሰጠውን ክብርም ነስቶት ቆይቷል፡፡
 ይሁንና በያዝነው ዓመት ጥቅምት ወር መጀመሪያ በተካሄደው ‹‹የመንበረ ፓትርያርክ አጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ 32ኛው አመታዊ
ስብሰባ›› ላይ ከመንግስት የተወከሉ ኃላፊዎች ‹‹የብዝኃነት አያያዝ፣ አክራሪነት/ጽንፈኝነት ዝንባሌዎቹና መፍትሔዎቹ›› በሚል ርዕስ
ያቀረቡትን ጥናት ተከትሎ ከስድስት በላይ ጳጳሳት ቀድሞ ባልታየ መልኩ ጠንካራ ተቃውሞ ማቅረባቸው፣ በብዙዎች ዘንድ የሀይማኖት
መሪዎች ለመንፈስ ልዕልናቸው ሊገዙ ይሆን? ከምድራዊውን ይልቅ ሰማያዊውን ሊመርጡ ይሆን? ‹እመን እንጂ አትፍራ› የሚለውን
አስተምሮአቸውን ሊተገብሩ ይሆን? የሚል ጥያቄ አጭሯል፡፡ በዕለቱ የመጀመሪያው ተናጋሪ የነበሩት የሰሜን ወሎና ዋግ ኹምራ አህጉረ
ስብከት ሊቀ ጳጳስ አቡነ ቄርሎስ በጥናቱ ላይ መቻቻል መጥፋቱን አስመልክቶ የቀረበውን ድምዳሜ እንዲህ ሲሉ ነበር ያጣጣሉት፡-
‹‹ይኼ አክራሪነት ጽንፈኝነት የሚለውን ቋንቋ እናንተው ናችሁ ያሰማችሁን፤ ከዚህ በፊትም አይታወቅም፤ በደርግም ይሁን በሌላ፡፡
እንደገና ደግሞ ብዙ ጊዜ ጽንፈኝነት፣ አክራሪነት እያላችሁ እድሜ ሰጥታችሁ ያበለጸጋችኋቸው እናንተው ናችሁ፡፡››

በርግጥም አቡኑ የተቹት ስርዓቱ የፕሮፓጋንዳው ፋሽን ያደረገውን ‹‹መቻቻል››ን ብቻ አይደለም፤ ‹‹በመቃብሬ ላይ ነው የሚሻሻለው››
የሚለውን የመሬት ፖሊሲንም ነው፡፡ በተጨማሪም ጥናት አቅራቢዎች በነገስታቶቹ ዘመን ቤተ-ክርስቲያኗ በርካታ መሬት መያዟንና ‹ሁሉ
በእጇ ሁሉ በደጇ› እንደነበር አድርገው ማቅረባቸውንም አልተቀበሉትም፡፡

‹‹በፊት መሬትም ህዝብም የነገስታቱ ነበር፤ አሁንስ የማን ነው? ይልቁንም ከአንድ ቤት ‹ግድግዳው የቤቱ ባለቤት ነው፣ ሳሎኑ የመንግስት
ነው› የሚለው አዋጅ የአሁኑ አይደለም እንዴ? ለኢትዮጵያዊነቱ ዋስትና የለውም፤ ይኼ የእኔ ነው የሚለው ከሌለ ምንድን ነው? ይህች
የእኔ የኢትዮጵያዊነቴ መገለጫ ናት ካላለ፣ ምንድን ነው ኢትዮጵያዊነት? አሁንም መሬቱም ህዝቡም የእናንተው ሁኖ ሳለ ለፊቱ፣ ለነገስታቱ
መስጠታችሁ በምን ተመልክተውት ነው?››

የደቡብ ጎንደር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ አቡነ እንድርያስም በሚያስተዳድሩት አካባቢ ያለውን የመንግስት ጣልቃ ገብነትና ተፅዕኖን
ከዘረዘሩ በኋላ፣ ለተሰነዘረው ፍረጃና ማሸማቀቂያ እንዲህ የሚል ምላሽ ሰጥተዋል፡-
‹‹የተበደለ ሰው ሲናገር ‹ፖለቲካ ተናገረ› እየተባለ የውሸት ውሸት ሲያተራምሱን የሚኖሩ ብዙዎች ናቸው፡፡… እንዴ! የመንግስት ስልጣን
የተረከቡ ወንድሞች የእኛን አፍ፣ የእኛን አንደበት ብቻ ነው እንዴ የሚጠብቁት፣ ለሌሎቹ ሞራል ይሰጣሉ ማለት ነው? …ለምንድን ነው
ግን በሽፋን የምትጠቀሙብን? መንግስት እኛን ሽፋን አድርጎ ነው ሲበዘብዘን የምንኖረው፡፡ ሌባውም ቀጣፊውም ሰርጎ ገቡም
ሲያጭበረብረን ሲያታኩሰን መንግስትን ሽፋን አድርጎ ነው፡፡››

የወላይታ ሀገረ ስብከት ስራ አስኪያጅም በተመሳሳይ መልኩ መንግስት በሃይማኖት ጉዳይ ጣልቃ መግባቱን ቤተ-ክርስቲያኗ ስትቃወም
ጉዳዩን ወደ ፖለቲካ እየቀየሩ ማስፈራራቱ እንደተለመደ እና ለቀብር ማስፈፀሚያ የሚሆን መሬት ከመስተዳደሩ በሚጠየቅበት ጊዜ
የሚሰጠው መልስ በሀሰት መወንጀል እንደሆነ ከገለፁ በኋላ፣ ጉዳዩ መፍትሄ ካላገኘ ሊከተል የሚችለውን ስጋታቸውን ተናግረዋል፡-
 ‹‹‘የፖለቲካ ጉዳይ ነው፤ ህዝብን በሃይማኖት ሽፋን ታንቀሳቅሳላችሁ’ እየተባልን እየተሸማቀቅን ያለንበት ሁኔታ ነው ያለው፡፡ ይህን
እንዴት ታዩታላችሁ? መቻቻልስ የሚመጣው ከምን አኳያ ነው? ዝም ብለን የምንቀመጥ ከሆነ ምናልባት ኃላፊነት ለመውሰድ
ስለሚከብደን ይህን ወርዳችሁ እንድትፈትሹ ለማለት ነው፡፡››

(በነገራችን ላይ የሲኖዶሱ ጉባኤ በተጠናቀቀ ማግስት ከማህበረ ቅዱሳን የአመራር አባላት መካከል ሶስት ሰዎች በፌደራል ጉዳዮች ቢሮ
ተጠርተው ዶ/ር ሽፈራውን ጨምሮ ከሚመለከታቸው ኃላፊዎች ጋር ውይይት ማድረጋቸውን ከመስሪያ ቤቱ ምንጮቼ ሰምቻለሁ፡፡
ሚኒስትሩ ከአመራሩ ጋር ለመወያየት የተገደደው ካልተጠበቀው የሲኖዶሱ አባላት ድፍረት ጀርባ ‹የማህበረ ቅዱሳን እጅ አለበት› የሚል
ጥርጣሬ በመያዙ ነው፡፡ በውይይቱም ላይ የተንፀባረቀው የባለስልጣናቱ መለሳለስ፣ ማህበሩን ‹አክራሪ› ብለው እንደማያምኑ እና ከዚህ
ቀደም የተሰራጩት ወንጃይ ሰነዶችን ሳይቀር ‹አናውቃቸውም› እስከማለት የደረሰ እንደነበር አረጋግጫለሁ፡፡ ይሁንና ይህ አይነቱ ‹እሳት
ማጥፊያ› ስልት፣ ከስርዓቱ ጋር የቆየ መሆኑ ይታወቃል፤ የማህበሩ አመራርም ይህ ይጠፋዋል ብዬ ባላስብም፣ ኢህአዴግ መስከረም
22/1998 ዓም ቅንጅትን እንዴት አቂሎ ለታሪካዊ ስህተት መዳረጉን አለመርሳቱ ይጠቅመዋል)

 የሆነ ሆኖ በዕለቱ ከፌደራል ጉዳዮች ተወከለው ከመጡት ሶስት ሰዎች መካከል አቶ ገዛኸኝ ጥላሁን አብዛኛውን ጥያቄ በተመለከተ
የሰጠው ምላሽ፣ የወከለው መንግስት ዛሬም በተሳሳተ የታሪክ ንባብ እያሸማቀቀ፣ እያስፈራራ፣ ህግን እየጠመዘዘ፣ እስር ቤት እየከተተ…
የፖለቲካ ጥቅሙን ማስከበር ላይ ያተኮረ መሆኑን ያሳያል፤ ኃላፊው ማስጠንቀቂያውን ያስተላለፈው እንዲህ በማለት ነው፡-
‹‹መጀመሪያ ግንዛቤ ላይ እንስራ በሚል እርምጃ አልወሰድንም፡፡ ኮሽ ባለቁጥር ወደቃሊቲ መፍትሄ አይሆንም፡፡››

 …‹ቃሊቲ›ን ምን አመጣው? መቼም ለጣልቃ ገብነቱ ከዚህ የበለጠ ማሳያ መፈለግ ‹አውቆ የተኛን…› እንደመሆን ነው፡፡ ‹መንግስትና
ሃይማኖት የተለያዩ ናቸው› ብሎ መከራከሩም ጊዜ ያለፈበት ፕሮፓጋንዳ ይመስለኛል፡፡ እናም የተሻለው መንገድ ከላይ በጠቀስኩት ሰነድ
‹‹በየማዕከላዊ ኮሚቴው በሚካሄደው የስምሪት ተግባር በፀረ-አክራሪነት ትግል ላይ ያለው የእያንዳንዱ ግለሰብ ቁመና መፈተሽ አለበት›› ተብሎ የተገለፀውን ማሳሰቢያ በፍጥነት በመተግበር፣ በቅድሚያ ራስን ከአክራሪነትና አሸባሪነት ማራቅ ነው፡፡ ማረጋገጫ የማይቀርብበትን
አፈ-ታሪክንም እየለቃቀሙ በአንድ ሃይማኖት ላይ መለጠፉ አስተማሪ አይመስለኝም፡፡

 ከዚህ ባለፈ ‹የሃይማኖት ኮማንድ ፖስት አቋቁመን ለችግሩ እልባት እንሰጣለን› የምትሉት ጉዳይ ቀጥታ መንግስት በሃይማኖት ጉዳይ
እጁን ማስገባቱን በአደባባይ ከማመን ያለፈ የፖለቲካ ጠቀሜታ አይኖረውም፡፡ ጳጳሳቶቹም ሆኑ ሼኼዎች ኃላፊነትና ግዴታቸው
ሰማያዊውን መንግስት መስበክ እንጂ፣ ከሰላይ አለቆችና ከፖሊስ አዛዦች ጋር ቢሮ ዘግተው የመንፈስ ልጆቻቸውን ‹ትምክተኛ›፣
‹አሸባሪ›፣ ‹አክራሪ›… እያሉ እንዲፈርጁ መፈታተኑ ያልታሰበ ህዝባዊ ቁጣ መቀስቀሱ አይቀርም፡፡






ኢትዮሚድያ - Ethiomedia.com
November 10, 2013

Saturday, November 9, 2013

ሰማያዊ ፓርቲ የስደተኛ ዜጐች እንግልት እንዲቆም ጠየቀ

 ሰማያዊ ፓርቲ አረብ አገር በሚገኙ ስደተኛ ኢትዮጵያውያን ላይ እየደረሰ ያለው እንግልትና ስቃይ በአስቸኳይ እንዲቆም ጠየቀ፡፡ ፓርቲው ትላንትና ረፋድ ላይ በጽ/ቤቱ “በመንግስት ቸልተኝነት በስደት ላይ ባሉ ዜጐች እየደረሰ ያለው ግፍና መከራ ይቁም” በሚል መርህ በሰጠው መግለጫ እንዳብራራው፤ ዜጐች በኢህአዴግ ዘመን በሚደርሱባቸው ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ጫናዎች በህጋዊና ህጋዊ ባልሆኑ መንገዶች ከሀገራቸው መሰደዳቸውንና ለእንግልት፣ ለሞትና ለስቃይ መዳረጋቸውን ጠቁሟል፡፡
“ፓርቲያችን የዜጐች ስደትና እንግልት ያሳስበዋል፤ መንግስት አስቸኳይ መፍትሔ እንዲሰጥም ድምፃችንን እናሰማለን” ብለዋል፤ የፓርቲው አመራሮች፡፡ የፓርቲው ሊቀመንበር ኢ/ር ይልቃል ጌትነት፣ የፓርቲው የወጣቶች ጉዳይ ሃላፊ ወጣት ዮናታን ተስፋዬ እና የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ ወጣት ብርሃኑ ተክለ ያሬድ በጋራ በሰጡት መግለጫ፤ ዜጐች የሚሰደዱት በአገሪቱ ላይ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ፍትህ ባለመኖሩ ነው ያሉ ሲሆን በነዚህ ጫናዎች ምክንያት ዜጐች በየበረሃው በኮንቴይነር ታሽገው እየሞቱ፣ በባዕዳን ኩላሊታቸው እየተሸጠ፣ በባህር ላይ ሲያቋርጡ በባህር አውሬዎች እየተበሉ መሆኑን አብራርተዋል።
በተለይም ሰሞኑን በሳኡዲ አረቢያ የሚገኙ ዜጐች እየደረሰባቸው ያለውን አስከፊ እንግልትና ስቃይ አጥብቀው እንደሚያወግዙ ተናግረዋል፡፡ “ዜጐች በባዕድ አገር በሚደርስባቸው በደል የኢህአዴግ መንግስት ከዜጐች ጐን በመቆም ስቃያቸውና በደላቸው እንዲቆም በመጠየቅ አጋር መሆን ሲገባው፣ በአገር ውስጥ ባሉ ሚዲያዎች “ሀገሪቱ በልማት እያደገች ባለችበትና ስራአጥነት እየተቀረፈ ባለበት ወቅት ዜጐች ሀገር ለቀው መሰደዳቸው ስህተት ነው” በሚል በዜጐች ላይ ማላገጡን ያቁም ሲል ፓርቲው አሳስቧል፡፡ “በተለይ በሳውዲ አረቢያ በዜጐች ላይ እየደረሰ ስላለው እንግልት፣ የአለም ትልልቅ ሚዲያዎች አጀንዳ አድርገው እየተነጋገሩበት፣ የኢትዮጵያ መንግስት ቸልታ “ይህቺ አገር መንግስት የላትም ወይ’ ያስብላል” ያሉት ኢ/ር ይልቃል የኢትዮጵያ ሚዲያስ ይህን አጉልቶ ካላወጣና ከዜጐቹ ጐን ካልቆመ ፋይዳው ምንድን ነው ሲሉ ጠይቀዋል፡፡
የስዊድን ጋዜጠኞች በህገ ወጥ መንገድ አገር አቋርጠው ወደ ኢትዮጵያ ሲገቡ እና ሲታሰሩ የአገራቸው መንግስት ጥፋተኛ ናቸው ብሎ ችላ ሳይል ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር ተደራድሮ በአጭር ጊዜ እንዲፈቱ ማድረጉንና አገራቸውም ሲገቡ የጀግና አቀባበል እንደተደረገላቸው የገለፁት ሊቀመንበሩ የኢትዮጵያ መንግስት ዜጐቹ በግልጽ እየተሰደዱ እየተንገላቱና እየሞቱ እጁን አጣጥፎ መቀመጡ የሚያስተቻቸው እንደሆነ አብራርተዋል፡፡ የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ ወጣት ብርሃኑ በበኩሉ፤ በእድሜና በእውቀት ያልበሰሉ ህፃናት በህጋዊና ህጋዊ ባልሆነ መንገድ ከአገር እየወጡ ለስቃይ ሲዳረጉ፣ በኤጀንሲዎች እና በህገወጥ ደላሎች ላይ ጥብቅ እርምጃ መውሰድና ዜጐቹን በተለያየ መንገድ ማስገንዘብ ሲገባው፣ ጭራሽ በየክልላቸው ፓስፖርት እንዲያገኙ እያደረገ ማበረታታቱ እንደሚያሳዝነው ተናግሯል፡፡ “ኤጀንሲዎችን ማገድና ፓስፖርትና ቪዛ መከልከል አሁንም ትክክለኛ መፍትሔ አይደለም” ያለው ብርሃኑ፤ መንግስት ፖሊሲዎቹን ማሻሻልና ማስተካከል እንዳለበት አሳስቧል፡፡
የፓርቲው የወጣቶች ጉዳይ ሃላፊ ወጣት ዮናታን በበኩሉ፤ “ኢህአዴግ ለወጣቶች ስራ የሚሰጠውና የሚያደራጀው አባል እስከሆነ ድረስ ብቻ ነው” ካለ በኋላ፤ “አብረን ከዩኒቨርሲቲ የወጣን ሆነን አባል ስለሆኑ ብቻ ትልልቅ ስራና ሃላፊነት ላይ የተቀመጡ ወጣቶች አሉ፡፡ እነሱ በመኪና እኛ በእግር እንተላለፋለን” ሲል አማሯል፡፡ “ኢትዮጵያ ውስጥ ልማትና እድገት ካለ ዜጐች ለቅንጦት አይሰደዱም” ያሉት የፓርቲው አመራሮች፤ በመንግስት ቸልተኝነት በኢትዮጵያ የስራ አጥ ቁጥር 40 በመቶ መድረሱን ገልፀዋል - አለም አቀፍ መረጃ መሆኑን በመጥቀስ፡፡ የኢትዮጵያ የውጭ አገር ብድር ከ12 ቢሊዮን ዶላር በላይ መሆኑን፣ የአገር ውስጥ የብድር መጠን 80 ቢሊዮን ብር መሆኑን፣ ባለፉት 10 ዓመታት ከኢትዮጵያ 11.7 ቢሊዮን ዶላር በህገወጥ መንገድ መውጣቱን እና መሰል መረጃዎችን የገለፁት አመራሮች፤ እነዚህ መረጃዎች የአለም ባንክና የአይኤምኤፍ መሆናቸውን ገልፀው፤ “ይህ ባለበት ስራ አጥነት ተቀርፏል፤ ልማት አለ የሚባለው በህዝብ ላይ ማሾፍ ነው” ብለዋል፡፡
ፓርቲው ባወጣው ባለአምስት ነጥብ የአቋም መግለጫ፤ የዜጐችን ህይወት ለመታደግ መንግስት በአስቸኳይ ከሳኡዲ መንግስት ጋር እንዲነጋገር፣ የሳኡዲ አረቢያ መንግስት በዜጐች ላይ እያደረሰ ያለው በደል የሰብአዊ መብት ጥሰት በመሆኑ በአስቸኳይ እንዲያቆም፣ ዜጐችን ለስደትና ለስቃይ የሚዳርጉ የችግሩ መንስኤዎች፣ ድርጅቶችና ግለሰቦች ለፍርድ እንዲቀርቡ እና ዜጐች የሚሰደዱበትን ምክንያት በጥልቅ በመመርመር አስከፊውን ስደት ለማቆም መንግስት የፖሊሲ ማሻሻያ እንዲያደርግ… የሚሉት ይገኙበታል፡፡ ፓርቲው በቀጣይነት ጥናቶችንና መረጃዎችን በማሰባሰብ ዘላቂ መፍትሔ ለማምጣት ጥረት እያደረገ መሆኑን ገልፆ፤ ለዚህ ስኬት ህብረተሰቡ፣ የሲቪክ ተቋማት፣ የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች፣ የፖለቲካ ፓርቲዎችና አለም አቀፉ ማህበረሰብ ከጐኑ እንዲቆሙ ጥሪ አስተላልፏል፡፡
ምንጭ እዲስ እድማስ

Thursday, November 7, 2013

ሀገራዊ ውርደት እንዲያበቃ ወያኔን ከሥልጣን ማስወገድ!!!

November 7,2013 posted by admin
የወያኔ ገዢ ጉጅሌ በባህርዩ ኢትዮጵያ ከዚህ በፊት አጋጥሟት የማያውቅ ፍጹም ኢሰብዓዊና ነውረኛ ስብስብ እንደሆነ ለመረዳት ኢትዮጵያዊያንን ለማዋረድ የሚጠቀሟቸውን ተግባራትና ቃላትን ማጤን ይበቃል።
በሶማሌ ክልል የኦብነግን ታጣቂዎች ቅስም ለመስበር ልጃገረዶችንና እናቶችን ብቻ ሳይሆን ወንዶችንም ጭምር በቤተሰብ ፊት በደቦ የሚደፍሩ፤ ለዚህ ተግባር የሠለጠኑ የልዩ ጦር አባላት መኖራቸው በስፋት የሚታወቅና በተደጋጋሚም የተዘገበ ጉዳይ ነው። ወያኔ፣ የኦጋዴን ወገኖቻችን በዚህ ጥቃት ተሸማቀው ያነገቡትን መሣሪያ ጥለው ፀጥ-ለጥ ብለው ይገዛሉ ብሎ ተስፋ ያደረገ ቢሆንም እየሆነ ያለው ግን የዚህ ተቃራኒ ነው። ዛሬ የሶማሌ ክልል ወንዱም ሴቱም፤ ወጣቱም አዛውንቱም በፀረ-ወያኔ አቋም የጋራ መግባባት ላይ ደርሷል። በኦጋዴን የወያኔ አስነዋሪ ጥቃት የፈጠረው ምሬት በውጭ አገራትም በሚደረጉ የፀረ ወያኔ ትግሎች የኢትዮጵያ ሶማሌ ተወላጆች ተሳትፎ እንዲጎለብት አድርጎታል። በሶማሌ ወገኖቻችን ላይ የደረሰው ጥቃት በሁላችንም ላይ የደረሰ ነውና ቁጭታቸውን እንጋራለን። በሶማሌ ወገኖቻችን ላይ የደረሰው ጥቃት ሀገራዊ ውርደት ነው።
በአፋር ክልልም ተመሳሳይ ጥቃት የዘወትር ትዕይንት እየሆነ መጥቷል። የአፋር የወል የግጦሽ መሬቶች ለሸኮራ አገዳ ልማት በሚል ሰበብ ሲነጠቁ የተቃወሙ የአገር ሽማግሌዎች ተደብድበዋል፤ ሚስቶቻቸውና ልጆቻቸው ተደፍረዋል። በአፋርም ውስጥ ለጾታዊ ጥቃት የሰለጠነ የወያኔ ልዩ ጦር ተሰማርቶ በሴቶች ብቻ ሳይሆን በወንዶችም ላይ አስነዋሪ ጥቃት አድርሷል። በአፋር ወገኖቻችን ላይ የደረሰው ጥቃት በሁላችንም ላይ የደረሰ ነውና ቁጭታቸውን እንጋራለን። በአፋር ወገኖቻችን ላይ የደረሰው ጥቃት ሀገራዊ ውርደት ነው።
በጋምቤላ ውስጥ ወያኔ ወገኖቻችን ከፈጀ በኋላ በሕይወት የተረፉትም ቅስማቸውን ለመስበር ጾታዊ ጥቃት በመሣሪያነት ተጠቅሟል፤ አሁንም እየተጠቀመ ነው። በጋምቤላ ወገኖቻችን ላይ የደረሰው ጥቃት በሁላችንም ላይ የደረሰ ነውና ቁጭታቸውን እንጋራለን። በጋምቤላ ወገኖቻችን ላይ የደረሰው ጥቃት ሀገራዊ ውርደት ነው።
የወያኔ ዝቅጠት ዘግናኝ ነው። ወያኔ ከላይ የተጠቀሰው ዓይነት ጾታዊ ጥቃት ያላደረሰበት የአገራችን ክፍል የለም። ኦሮሚያ፣ አማራ፣ ደቡብ፣ ቤንሻንጉል … በሁሉም ቦታዎች ያልተነገሩ ጥቃቶች በዜጎታችን ላይ ደርሷል፤ እየደረሰም ነው።
በአንድ ወቅት በመሀል አገር፤ በሰሜን ሸዋ አንዲት ኢትዮጵያዊት እናት በእብሪተኛ ወያኔ የተገደለውን ባለቤትዋን ብልት ይዛ አስክሬኑን እንድትጎትት መደረጉን ከዓይን እማኞች አንደበት ሰምተናል። በመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ ሰበብ መስዋዕትነት እየተቀበሉ ያሉ ወገኖቻችን “ሽንታም አማራ” እየተባሉ ብልቶቻቸው ይቀጠቀጥ እንደነበር የሰማነው እና የምናውቀው ጉዳይ ነው። በወያኔ መዳፍ ውስጥ ውስጥ ገብተው በእስር ቤቶች በሚገኙ ወንድሞቻችንና እህቶቻችን ላይ ዘግናኝ ተግባራት እንደሚፈፀሙ መረጃዎች አሉ። በአዲስ አበባ በየቦታው ባሉት ስውር የማሰቃያ ቤቶችም ተመሳሳይ ተግባራት ዘወትር እንደሚፈፀሙ ይታወቃል።
ወያኔ ለጾታዊ ጥቃት ያሰለጠናቸው ሰዎችን በከተሞችም ውስጥ አሰማርቷል። በእነዚህ ጥቃቶች ግለሰቦች ግንባር ቀደም ተጠቂዎች ቢሆንም የተደፈርነው፣ የተዋረድነው ሁላችንም መሆናችን አጽንዖት ሊሰጠው ይገባል። የተደፈርነው እኛ ኢትዮጵያዊያን በሙሉ ነን። የተዋረደችው የምንወዳት አገራችን ኢትዮጵያ ነች።
ኢትዮጵያ አገራችን እፍረት ባልፈጠረባቸው ነውረኛ የወያኔ ዋልጌዎች እንድትገዛ እንድትረገጥ በመፍቀዳችን ጥፋቱ የኛም ጭምር ነው። ይህን ነውረኛ ቡድን በሥልጣን ላይ እንዲቆይ በፈቀድንለት መጠን በኢትዮጵያዊያን እና በኢትዮጵያችን ላይ የሚደርሰው በደል እየባሰ እንደሚመጣ በዓይኖቻችን እያየን በጆሮዎቻችን እየሰማን ነው።
ሰሞኑን በአንድነት ፓርቲ የምክር ቤት አባል ላይ የደረሰው ጥቃት የዚሁ አካል ነው። እኚህ ወገናችን የደረሰባቸውን ዘርዝሮ ለመናገር የሚከብድ መሆኑ ገልፀዋል። ማፈር የነበረባቸው ጥቃት አድራሾቹ መሆን ይገባቸው ነበር፤ ሆኖም ግን ይሉኝታ አልፈጠረባቸው። ምንም ይሁን ምን በወገናችን ላይ የደረሰው ጥቃት በእሳቸው ላይ ብቻ የደረሰ ሳይሆን በሁላችንም ላይ የደረሰ መስሎ የሚሰማን መሆኑን ልንነግራቸው እንወዳለን። የተዋረደችው ኢትዮጵያ አገራችን ነች።
ይህ ውርደት እንዲያበቃ ወያኔ ከሥልጣን መወገድ ይኖርበታል።
ግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ “ወያኔን ከሥልጣን ማስወገድ” ቀዳሚ ሥራችን ነው የሚለው ኢትዮጵያን ለማዳን ከዚህ የሚበልጥ አንገብጋቢና አጣዳፊ ሥራ ስለሌለ ነው። ወያኔን ለማስወገድ እንተባበር።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!

የማለዳ ወግ: ሳውዲ አረቢያ እና ዘንድሮ … እንዲህም ይኖራል!








ከነብዩ ሲራክ (ጋዜጠኛ)
መስዋዕትነት መክፈል ካለብኝ ዝግጁ ነኝ ! ስለእኔ አትዘኑ !
እለተ ሰኞ – ጥቅምት ሊሸኝ ህዳር ሊገባ የቀሩት ጥቂት ቀናት ብቻ ናቸው። በሳውዲ አረቢያ በህጋዊ መንገድ ገብተው ከአሰሪዎቻቸው ጋር ባለመግባባትና ፈርጀ ብዙ በሆነ ምክንያት መኖሪያ ፍቃድ የተበላሸባቸው ማደስ እንዲችሉ፣ ከአሰሪዎቻቸው ጠፍተው ያለ ህጋዊ ሰነድ በግል ሲሰሩ ለነበ ፣ ከአምስት አመታት በፊት በህጋዊ መንገድ በሃጅ በኡምራ ገብተው ወደ ሃገራቸው ሳይመለሱ በህገ ወጥ መንገድ ያለ መኖሪያ ፈቃድ በሳውዲ የሚኖሩትን ወደ ሁለት ሚሊዮን የሚቆጠሩ የተለያዩ ሃገር ዜጎች ህጋዊ ሰንዳቸውን እንዲያስተካክሉ የሚፈቅደው አዋጅ ተጠናቋል። የጭንቁ ቀን ቀርቧል!
የሳውዲ መንግስት ለሁለተኛ ጊዜ የሰጠው የምህረት ሲጠናቀቅ ህገ ወጥ ተብለው የተፈረጁ በሳውዲ የሚኖሩ የተለያዩ ሃገር ዜጎች ከተያዙ የሁለት አመት እስራት እና የሳውዲ ሪያል 100. 000 ( አንድ መቶ ሽ የሳውዲ ሪያል በግምት ግማሽ ሚሊዮን የኢትዮጵያ ብር) ቅጣት እንደሚጣል አስታውቋል ! …የምህረት አዋጁ ማለቁን ተከትሎ ከፍተኛ ፍተሻ እንደሚደረግ መንግስት ጠንከር ጠንከር ያሉ መግለጫዎችን ሰጥቷል። የውጭ ዜጎች በብዛት የሚገኙባቸውን የሳውዲ ከተሞች እስከ ደንበር የገጠር መንደሮች በልዩ ልዩ ሞተር ሳይክሎች መኪኖች እና ሂሊኮፕተር ሳይቀር በመጠቀም ፍተሻውን እንደሚያጠናክር አስታውቋል ። መንግስት በዚሁ አሰሳና አፈሳ ስራ ተሳታፊ የሚሆኑ የመንግስት ሚኒስትር መስሪያቤት በዋናነት ከሰራተኛ ሚኒስትር ። በፖሊስ እና ከደህንነት በተውጣጡ ኮሚቴዎች ስልጠና ሰጥቶ ፍተሻውን እንደሚያከሂድ ያስታወቀበት ቀን ደርሷል ። በማስጠንቀቂያው ህገወጥ የተባሉትን ብቻ ሳይሆን ህገ ወጥ የተባሉተን ማስጠጋት በራሱ ከከፍተኛ ገንዘብ ቅጣት ከሃገር እሰከ መባረር የሚያደርስ እርምጃ ይወሰድበታል የሚል ተደጋጋሚ ማስጠንቀቂያ መሰጠቱ በእርግጥም ከሰባት ሚሊዮን በላይ ለሚሆነው የውጭ ዜጋ አስፈሪና አሳሳቢ ጉዳይ ነው!
በተፈራው ቀን ሰኞ ጅዳ ከወትሮው በተለየ ጸጥና ረጭ ብላለች ፣ ግህ እንደቀደደ በማለዳው ልጆቸን ይዠ ወደ ጅዳ የኢትዮጵያን አለም አቀፍ ትምህርት ቤት ተጓዝኩ። በትምህርት ቤቱ ስደርስ የምህረት አዋጁን ማብቃት ተከትሎ መምህራን እና ሰራተኞች ባለመምጣታቸው ተረዳሁ። ትንሽ ቆየት እንዳለኩ በስጋት ላይ የነበረው የ3000 ታዳጊዎች የትምህርት ማዕከል መማር ማስተማር ሂደት በትምህርት ቤቱ አስተዳደር፣ በኮሚኒቲና በመንግስት ተወካዮች የቅርብ ክትትልና ግልጽነት ያለው አካሔድ አለመከተል መኮላሸቱ አበሳጭቶ ቀኔን አጨልሞ ጀመረው! ከሃገረ ጀርምን ትናነት ምሽት ያረፉትን የምሰራበት ኩባንያ የስራ ባልደረቦቸን ፊቴ በርቶ እንዳልቀበላቸው ምክንያት የሆነኝን ትምህርት ቤት ልጆቸን ወደ ቤት ከመለስኩ በኋላ በትካዜ ወደ ቢሮየ አመራሁ…!
(ነብዩ ሲራክ)
እለተ ማክሰኞ – ከአመት እስከ አመት ሞቅና ደመቅ ያለ እንቅስቃሴ በሚታይባቸው የጅዳ ፣ የመካ ፣ የመዲናና ዋና ከተማዋ ሪያድ ወትሮ የነበረው እንቅስቃሴ በከፍተኛ ሁኔታ የቀነሰ ሲሆን የተወረሩ ከተማ መስለው መታየታቸው ተጠቅሷል። በመንግስት ጠንካራ ፍተሻ ግራ የተጋቡ ዜጎች በአፈሳና ፍተሻው ፍርሃቻ ከቤት ባለመውጣት ጊዜውን በማሳለፍ ላይ ሲሆኑ በውጭ ዜጎች ይንቀሳቀሱ የነበሩ ሱቆች እና አንዳንድ ግልጋሎት መስጫዎች በመዘጋታቸውም ከተሞቹ ጸጥና እረጭ እንዲሉ በማድረግ በንግድ ልውውጡ ላይ ከፍተኛ ተጽእኖ ማሳደራቸውን መገናኛ ብዙሃን ሳይቀር በመዘገብ ላይ ናቸው ። የምህረት አዋጁን በመጠቀም እንድም መኖሪያ ፈቃድ አለያም የመውጫ ሰነድ ማግኘት ያልቻሉ ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ የተለያዩ ሃገር ዜጎች ለጉዳያቸው መጓተት ሰበቦች የሳውዲ መንግስትን መስሪያ ቤቶች የተቆላለፈ ቢሮክራሲያዊ አሰራር እና የየሃገራቸው ቆንስልና ኢንባሲ ጽህፈት ቤቶችንም ሰነዶችን በጊዜ አለማቅረብ እንደሆነ ገልጸውልኛል ። ይህም ለአሁኑ አፈሳውና መዋከቡ አደጋ እንደጣላቸው ተጨናንቀውና ተስፋ ቆርጠው በምሬት ሲናገሩ መስማት በራሱ ያማል …
የሳውዲ መንግስት ለወራት የሰጠውን የምህረት አዋጅ መጠቀም ካልቻሉት መካከል ቀዳሚ የሆንነው ኢትዮጵያውያን እንደ ቀረው ዜጋ ለፍተሻ ውክበቱና እስሩ ተጋላጭ ሆነናል ። በባህር አድርገው በህገ ወጥ መንገድ በየመን በኩል ወደ ሳውዲ የገቡትን ጨምሮ በአብዛኛው በግል የመኖሪያ ፈቃድ ገዝተው በአሰሪዎቻቸው ውጭ በተለያዩ ድርጅቶችና ኩባንያዎች ተቀጥረው የሚሰሩ ፣ በአሰሪዎቻቸው እጅ አዙር ክፍያ በመክፈል በግል ሱቅ የከፈቱ ፣ በግል መኪና ገዝተው ኮንትራት ተማሪና ሰራተኞችን የሚያመላልሱና ፣ በአሰሪዎቻቸው ስም ጥቃቅን ንግድ ስራን ከፈተው በመስራት ይተዳደሩ የነበሩ በአስር ሽዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን የምህረት አዋጁ ካለቀበት ቀን ጀምሮ ከሞላ ጎደል ስራቸውን አቁመው የሚሆነውን በስጋት ቋፍ ላይ ሆነው በመከታተል ላይ ናቸው።
ፍተሻው ተጠናክሮ ከመቀጠሉ አስቀድሞ አብዛኛው ህጋዊ እና ህገወጥ ተብሎ የተፈረጀው ነዋሪ ስጋት ከፍተሻው ጋር ሊፈጠር የሚችለው ማዋከብና ቤት ለቤት ፍተሻ ይደረጋል የሚለው የነበረ ቢሆንም በምህረት አዋጁ ማለቂያ ዋዜማ መንግስት በሰጠው መግለጫ ፍተሻው በኮሚቴ የተሚመራ በመሆኑ ማዋከብ የሌለበት እንደሚሆን በማሳወቅ “የቤት ለቤት ፍተሻ የለም!” የሚል መግለጫ በመሰጠቱ አፎይታን ፈጥሮ ነበር ። ይሁን እንጅ እለተ ሰኞ ምሽትና ማክሰኞ እስኪነጋጋ መንግስት የሰጠው መመሪያ ተጥሶ በሪያድ ነዋሪ በሆኑ ኢትዮጵያውያን ጥቃት ተሰንዝሮባቸው ሰምቻለሁ፣ አረጋግጨማለሁ! በተለይም በሪያድ ውስጥ ጩቤ እየታጠቁ እስከ መጋደል ባደረሰ እርምጃቸው የሃበሻውን ስም ያረከሱት “ባህር ሃይል ” በሚል ቅጽል ስም የሚጠሩት ህገ ወጥ ዜጎቻችን መናህሪያ የሆኑ የከተማው ክፍሎች ቀደም ሲል በተደረገ ጥናት የመንግስ ኢላማ ሆነው ነበር ። በየመን በኩል በባህር የሚመጡት ኘእኒሁ ኢትዮጵያውያን የሚኖሩበት መንፉሃ ደግሞ የመጀመሪያው የመንግስት የብረት ዱላ አረፈባት! “ለሃጣን የመጣ ለጻድቃን !” እንዲሉ ሁለት ኢትዮጵያንን ህይዎት እስከ መቅጠፍ እና በበርካታዎችን ላይ የአካል ጉዳት እስከ ማድረስ የደረሰ የቤት ለቤት ፍተሻ ተካሔዶ በሰላማዊና በህጋዊ የአካባቢው ነዋሪ ኢትዮጵያውያን ላይ ቤተሰቦች ላይ ግፍ ተፈጸመ… መረጃው በደረሰኝ ቅጽበት ወደ ሪያድ ስልክ በመደወል ያነጋገርኳቸው ኢትዮጵያውያን እያነቡ የገለጹልኝን በትክክል ላመስቀመጥ ይከብደኛል … ብቻ የእኛ ዜጋ ተለይቶ ሲታደን ውሎ አደረ ….


ከጅዳ ከተማ አራት እና አምስት መቶ ኪሎ ሜትር ርቀት በመስክ ስራ ላይ ተሰማርቸ በምገኝበት የሰማዩ የከረረ ጸሃይና ከፊት ለፊቴ የተገጠገጠው በአሸዋ የተዋጠ በርሃ ወበቅ ሳያንገኛታኝ በሚጢጢዋ ከከምፒተሬ የፊስ ቡክ የውስጥ ገጽ እና በተንቀሳቃሽ ስልኬ የሚደርሱኝ በምስል የረደገፉ ሲያንገላቱኝ ዋሉ! እንዳልናገር ሊናገሩት የሚከብድ ፣ ዝም እንዳልለው ዝም የማይባል የወገን ጩኸት ነውና ይህን መረጃ አልሰሜ የሚሰማበትን መንገድ ሳፈላልግ ትናንት ረፋዱ ላይ ጋዜጠኛ ሽዋየ ለገሰ የላከችልኝን ማስታወሻ አስታወስኩና አትኩሮት ሰጥቸ አነበብኩት ” ነቢዩ ስለ ሳውዲ የምህረት አዋጅ ማለቅ መስራት የምትችል ከሆነ ዜና ሰርተህ ላክልን ፣ የማችል ከሆነ ግን ከዚህ እንድንሰራው የአንዳንድ ነዋረሀዎችን የስልክ አድራሻ ላክልን …” ይላል! ለሽዋየ ዜናውን እንደምሰራው ገልጨላት በቀጥታ ወደ ስራው ገባሁ! መረጃየን አሰባስቤ የምህረት አዋጁን ተከትሎ በሪያድ ኢትዮጵያውያነደ ላይ እና በጅዳ ትምህርት ቤት መዘጋትና በአደጋ ላይ መሆነደ ዙሪያ ዜናውን ለእለተ ረቡዕ ምሽት አደረስኩት …
የምሽቱ ዜና ሲተላለፍ እኔ ጅዳ እየገባሁ ነበር ፣ ዜናወ ተላልፎ እንዳለቀ እቤት ብደርስም ከድካም እረፍት የማይሰጡ መልእክቶች ይደርሱኝ ይዘዋል ….በሪያድ የሞቱት ሰዎች ቁጥር ወደ አምስት ማደጉን ፣ በርካታ የመኖሪያ ፈቃድ ያላቸው ኢትዮጵያውያን መንገላታታቸውን ፣ “በመንፉሃ በኢትዮጵያውያን ላይ የተፈጸመው ግድያ ጩቤ ይዘው ለማጥቃት በመሞከራቸው ነው!” ፣ “ሰርገኛ መጣ በርበሬ ቀንጥሱ !” እንደ ሚባለው በጅዳ ትምህርት ቤት ዙሪያ ለመምከር የጅዳ ቆንስል፣ የኮሚኒቲ እና የወላጅ ኮሚቴ ከፍተኛ ሃላፊዎች ስብሰባ መቀመጣቸውና ሌላም ሌላም መረጃዎች ደርሰውኝ አስተናገድኩ ….
አንድ ብርቱ ወዳጀ ስልክ ደውሎ እየሆነ ስላለው መረጃ ጠይቆኝ በሪያድ እየሆነ ያለውን ከፍቶኝ ከገለጽኩለት በኋላ የሰጠኝ ምክርና የእኔን ምላሽ የዛሬ ማለዳ ወጌ ማሳረጊያ ማድረጉን ፈቅጃለሁ.
..
በጥሞና መረጃውን ሰጥቸው እንዳበቃሁ ወዳጀ መናገር ጀመረ ” ነቢዩ ራስክን ጠብቅ! ለልጆችህ ኑርላቸው !” ሲል የወንድም የወዳጅና የአብሮ አደግነቱን ምክር መከረኝ …በአክብሮት ሰማሁት! አመሰገንኩትም! ግንስ ጥቂት ወረበሎች በፈጠሩት ሁከት ብዙሃን ሰላማዊ ነዋሪ ኑሮው ሲናጋ እየሰማሁና እያየሁ ፣ ወገን ልናገረው በሚከብደኝ አሰቃቂ ሁኔታ ግፍ የተፈጸመባቸው ጭብጥ መረጃዎች ይደርሱኛል! ከነ አሰቃቂው በብለት የተተለተለ የወገን ሬሳን ምስል እና በጥይት የተበሳሳና የተቆራረጠ ሰቅጣጭ መረጃ እየደረሰኝ እንዴት ራሴን መጠበቅ ይቻለኛል? አዎ ለልጆቸ እና እንድኖርላቸው ለሚፈልጉ ወገኖቸ ለመኖር ስል የወገንን የመከራ ጸአር ፣ የታፈነ የድረሱልኝ ጩኸት እየሰማሁ እና እያየሁ ዝም ማለቱ ለእኔ ከባድ ነው! እንዴትስ አድርጌ እንደኔ የሚፈልጋቸው ወላጅ ያላቸው ወገኖቸ እያነቡ እንባቸውን ባልጥርግ ለልጆቸ እና ለጠገብኩት የተንደላቀቀ ኑሮ ስል ዝምታን ልምረጥ ? እንዴትስ የህሊና እዳ ተሸክሜ ለልጆቸና ለሚፈልጉኝ ልኑር? እንዴትስ ይቻላል? አዎ ! ፈጣሪ ሁሉንም ያያል …የማይሳነው አምላክ አጥፍተን ከሚያዘንብብን ሰቆቃ ይታደገን ዘንድ በርትታችሁ ጸልዩ! ለእኔንም የፈራችሁ የሰጋችሁ ፣ አንድየ የታይታውን ሳይሆን የልቤን አይቶ እሱ ጽናት ብርታቱን ይስጠኝ ዘንድ ግን በርትታችሁ ጸልዩልኝ !
ይቅርታ የምክራችሁ ምንጩ ፍቅርና አክብሮት እንደሆነ ጠልቆ ቢገባኝም ቅሉ “ለልጆችህ ለወገኖችህ ኑር ! ” ብላችሁ ግን አትምከሩኝ ! መስዋዕቱን እኔው ልቀበለው ስለቆረጥኩ እውነቱን በመናገሬ ለሚደርስብኝ ስቃይ መከራ የተዘጋጀሁ ነኝና ስለእኔ አትፍሩ ፣ አትዘኑ ! ልጆቸን ለማሳደግ እና የእለት እንጀራየን ለማግኘት ደፋ ቀና ከማለቱ ጎን ለጎን ባለችኝ ውሱን ጊዜ ህሊናየ ፈቅዶት ማድረግ ያለብኝን እያደረግኩ እስከ ወዲያኛው እዘልቃለሁ! በግል ጨካኝ አውሬ ፣ ሰላቢ ምቀኛ ፣ ሆዳም አድርባይ ፣ ዋሾ አስመሳይ ቀጣፊ ልሆን ብቸልም በአረብ ሃገር ኑሮ ከከተምኩ ጀምሮ በአደባባይ የምሰጣችሁ መረጃ ከተጨበጠ አሁን አሁን በግላጭ እየታየ ከመጣው ሰቆቃ ሰብዕና የማይጎዳውን እየመረጥኩ ከሞላው እየጨለፍኩ ያቃመስኳችሁ መሆኑን ታምኑኝ ዘንድ ልማጸናችሁ ግድ ይለኛል! አዎ ወገን ሲገፋ ፣ ሲበደል መረጃ በማቀበሌ መስዋዕትነት መክፈል ካለብኝ አስፈላጊውን ሁሉ መስዋዕትነት ለመክፈል ዝግጁ ነኝ ! ይህ ቂል ሆኝ አለያም ራሴን ለመኮፈስ ወጥኘ የኝረጨው ከንቱ ፉከራ እንዳይመስላችሁ! እናም ቃሌን ልድገመው እየሆነ ስላለው ነግ በየግል ቤታችን ስለሚገባው መከራ እሰቡ እዘኑ እንጅ ስለእኔ አትዘኑ … ! ደግሞም መፍትሔ ሃሳብ ከመረጃየ ባታገኙ አይድነቃችሁ … መፍትሔ ይፈልጉ ዘንድ ህዝብና ሃገር ለመጠበቅ ቃል ገብተው ሃገር የሚያስተዳድሩትን በርትታችሁ ጎትጉቱ! መፍትሔው የወገንን መብት የሚከበርበትን መላ ይፈልጉ ዘንድ እስኩሰሟችሁ ጩሁባቸው! እኔ እስክጠፋ መረጃ ከማቀበል የሚያሸሽ ህሊና አጥቻለሁ ! እናም ስለእኔ በፍጹም አትዘኑ ! ቢቻል ማለት ካለባችሁ እንደ መለኩሴዋ እናቴ ” ለእውነት ግንባርክን ስጥ ፣ ዋጋህን ከባለእግዚአብሔር ታገኘዋለህ! ” ብላችሁ ጽናትን ተመኙልኝ ፣ ፍርሃትን ፈርቸው በተገላገልኩት መባቻ ፍርሃትን አታስተምሩኝ ! እውነትን አፍኘ ለልጆቸና ለሚወዱኝ የመኖር አባዜው ትርጉሙ እየኖሩ አለመኖር ነውና ግንባሬን ሊደርስ ከሚችልብኝ የጨካኞች ኢላማ የማሸሸት ሞራሉ የለኝም! ጠባቂየ እውነትን ስበኩ የሚለው አንድ አምላክ እንጅ እኔ አይደለሁም! ልጆቸም የሚጠበቁት በአንድ ፈጣሪ እንጅ በእኔ አይደለም ! እሱ ሁላችንን ይጠብቀን ! በቃ የእኔ ምላሽ ይህ ነው ! ቸር ያሰማን!
ክባሪያችሁ
ነቢዩ ሲራክ

Tuesday, November 5, 2013

አንዷለም አራጌ አርዓያክብር (ICON) ነው!!

ዳንኤል ተፈራ
ወጣቱ የነፃነት ሰላማዊ ታጋይ ፖለቲከኛ አንዷለም አራጌ ዋለ የፃፈው ‹‹ያልተሄደበት መንገድ›› ገበያ ላይ ዋለ፡፡ አንዷለም አርአያ ክብር ነው፡፡ ምሳሌና አርአያ ብናደርገው የምንጠቀምበት ምርጥ ኢትዮጵያዊ ነው፡፡ በቅርበት ስለማውቀው ብቻ እራሴን እንደ ዕድለኛ እቆጥራለሁ፡፡ ማርቲን ሉተር ኪነግንና ማህተመ ጋንዲን አንስቶ አይጠግብም፡፡ ስለፍቅር ሲል ሁሉን አሳልፎ መስጠት የሚችል፤ ስለ ኢትዮጵያ የሚሰስተው የሌለው ውድ ወጣት ነው፡፡ ለአላማው በፅናት መቆምን ተክኖበታል፡፡ እነሆ አሁን ደግሞ ጨለማው ሳይበግረው ያልተሄደበት መንገድን ሊያሳየን በመፅሐፍ መጣ፡፡ የማይበገር ራዕይ ያላቸው ሰዎች እንደዚህ ናቸው፡፡ እድለኛ ካልሆኑ በስተቀር እንደዚህ መሆን ከባድ ነው፡፡

ለቅምሻ ያህልም ከመግቢያው እነሆ ብያለሁ፡-
‹‹….መታሰር ነገሮችን በጽሞና ለማየት እድል ይሰጣል፡፡ በስራ የተጠመደ ሰው ነገሮችን በአንክሮ ለማሰብ የሚፈልገውን ያህል ጊዜ አያገኝም፡፡ ድንገት የሚከሰቱ ነገሮች ማእበል ከአንዱ ጉዳ ወደ ሌላው ያላጋዋል፡፡ እኔ አሁን ከእንዲህ አይነት ሁኔታ ነፃ ነኝ፡፡ስለዚህ ፍፁም አስቸጋሪ በሚባል ሁነታም ቢሆን በግፍ ከተለየሁት የኢትጵያ ህዝብ ጋር በሃሳብ ለመገናኘት መሞከር እንደሚገባኝ ወደንኩ፡፡ ጥረቴ የሚገትመው ፈተና በጣም አስቸጋሪ እንደነበር ግልፅ ነበር፡፡ በመሆኑም የሃገራችን አንዳንድ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ነገሮችን አንስቼ ለመወያየት በማሰብ ‹‹ከዚህ ወዴት እንሄዳለን? ትላንት ዛሬና ነገ›› የሚል ርእስ መዘገብኩ እንደሃገር ካለፈው ይልቅ ስለሚመታው አብዝትን ልንጨነቅ እንደሚገባን ባምንም ያለፈውና አሁን ያለንበት ደግሞ ወደሚመጣው ዘመን የምንደርስበት ሜዳ በመሆኑ መዳሰስ ተገቢ እንደሆነ አምናለሁ፡፡ ያለሁባት ክፍል እጅግ ጠባብ ከመሆኗ የተነሳ ስድስት ሆነን እግርና ጭንቅላታችንን ገጥመን ከዳር እስከዳር ሞልተናታል፡፡ መኝታውም መቀመጫውም ፍራሽ ነው፡፡ እጅና እግር ሲጠጋጉ የጠረጴዛና ወንበር ሚና ይጫወታሉ፤ እጅም የመፃፍ ስራውን ይሰራል፡፡ ለመቀመጥ አስቸጋሪ ከመሆኑ የተነሳ ግን የጀርባ ህመም ማስከተሉ አልቀረም፡፡ በዚህ ሁኔታ ለመፃፍ ሌሊቱን መጠቀም ነበረብኝ፡፡ ለምን ቢሉ እኔ ምን እንደምሰራ እንዲከታተሉ የተመደቡ ወንደሞች በመኖራቸው እነርሱም በማዳከም እንቅልፍ ባለውለታዬ ነው፡፡ ከጎኔ ተኝተው እንቅልፋቸውን ሲያጣጥሙ እኔ ደግሞ በሃሳብ ፈረስ ጋልቤ የምወዳት ሃገሬን የእስር ቤት አጥር ሳይገድበኝ እዞራታለሁ፡፡ በሃሳብ ዶሴዎቿን ከመሳቢያ እያወጣሁ አገላብጣለሁ፤ የሚመስሉኝን ሃሳቦች እሰነዝራለሁ፤ እፅፋለሁ፡፡

በዚህ ሁኔታ ሆኜ ወረቀትና ብእርን ማገናኘት ቀላል ባይሆንም ከሁሉ የሚያስቸግረው ግን ዋቢ መፅሃፍትን ሰብስቦ እያጣቀሱ በጥሩ ሁኔታ የተጠና መፅሃፍ ማዘጋጀት ነበር፡፡ መፅሃፍትን ማስገባት በጣም ከባድ ነው፡፡ ማስገባት ቢቻል እንኳን መፅሃፍቱን በሚገባ አመሳክሮና ጊዜ ወስዶ አንድ መፅሃፍ ማበርከት በጣም ከባድ ነው፡፡ የጊዜ ጉዳይ ሞልቷል፡፡ ነገርግን የሚፃፉ ፅሁፎች በየጊዜው በሚደረግ ፍተሻ ይወሰዳሉ፡፡ የዶ/ር ኪንግን መፅሃፍ ትርጉምን አጥቻለሁ፡፡ ሌላ ተመሳሳይ ችግር ደግሞ ማስተናገድ ከባድ ነው፡፡ ስለዚህ ከጊዜ ጋር የሚደረገው ግብግብም ወሳኝ ነው፡፡ ስለዚህ በተለያዩ ምክንያቶች ዋቢ መፅሃፍትን ማመሳከር አለመቻሌን እንዳለመታደል እቆጥረዋለሁ፡፡ አንባቢም ይኸንን ውሱንነት እንዲረዳልኝ በአክብሮት እጠይቃለሁ፡፡ በእርግጥ ያም ሆኖ እጄ ላይ ያሉ ውሱን መፃህፍትን ማገላበጥ ችለሁ፡፡

በመሆኑም ለመፃፍ እቅድ ማውጣት በንፅፅር ሲታይ ቀለል ቢልም በተለይ አሁን ባለሁበት ሁኔታ ሃሳብን አደራጅቶ ለመከራከር ብሎም ለመፃፍ መሞከር በጣም ከባድ ነበር፡፡ ፈጣሪ ፀጋውን አብዝቶልኝ ግን ለመፃፍ ሞክሬያለሁ፡፡ ለእኔ ትልቁ ቁምነገር በዚህ አይነት ሁኔታም ሆኜ ለሃገሬ ይበጃል የምለውን ነገር ሃሳቤን የመግለፅ ተጠቅሜ መፃፍ መቻሌ ነው፡፡እንደመሸበብ ክፉ ነገር ይኖር ይሆን?
በእኛ ሃገር የፖለቲካ ባህል ውስጥ ላደገ ሰው በግፍ ከሚስቱ፣ ከልጆቹና በዙርያው ካሉ ወዳጅ ዘመዶቹ ተለይቶ በወህኒ ቤት ሆኖ የጭቆናን ገፈት የሚጎነጭ ሰው ስሜታዊ እንደሚሆንና የመጠቃት ስሜትም ሊታይበት እንደሚችል ይጠበቃል፡፡ ከደረሰብኝ ነገር ሁሉ አንዳች ያልጠበኩት ነገር ባይኖርም አንዳንድ ጊዜ ስሜቴ መጎዳቱ አልቀረም፡፡ ስሜቴ በምፅፍበት ወቅትም ሚዛናዊ እንዳልሆን ይልቅስ ስሜቴን ብቻ እንደወረደ እንዳስተናግድ በተደጋጋሚ ቢፈትነኝም በተቻለኝ መጠን ፈተናውን ለማለፍ ጥረት አድርጌያለሁ፡፡ በግል በደል ወይንም ጥቅም ላይ ተመርኩዞ ከመፃፍ ይልቅ ለሁላችን የሚጠቅመውን በተለይም ከዛሬ ይልቅ ለነገ ይበጀናል የምለውን ሃሳብ ለማመላከት ሞክሬያለሁ፡፡ የጊዜ ጉዳይ እንጂ ሞት ለሁላችንም ማይቀር እዳ ነው፡፡ ከሞት በኋላም ግን ዛሬ ያላነሳነው አጀንዳና ያነገብነው እውነት በልጆቻችን ፊት መቅረቡ አይቀርም፡፡ ዛሬ የያዝነው ሃሳብ የጊዜን ፈተና አልፎ በትውልድ ፊት ሞገስ ቢያገኝ ፍሬም ቢያፈራ ትልቅ መታደል ነው፡፡ ስለዚህ በተቻለኝ መጠን ሚዛናዊ ለመሆን አቅሜ የፈቀደውን ጥረት አድርጌያለሁ፡፡

ከዚህ በተጓዳኝ ሌላም የሃሳብ ውጣ ውረድ ለማስተናገድ ተገድጃለሁ፡፡ እንደሚታወቀው የሃገራችን ፖለቲካ በብዙ መልኩ ጠርዝ የያዘ ነው፡፡ ሚዛናዊ ለመሆን ስሞክር በኢህአዴግ በኩል‹‹ ክንዳችንን አቀመስነው፣ አስተነፈስነው›› የሚል ስሌት ውስጥ ሊገቡ እንደሚችሉ በመገመቴ ይኼን አይነት ስሜት በማይፈጥር መልኩ ለመፃፍ መታገል ነበረብኝ፡፡ ይኼን ሳደርግ ደግሞ እኔም ደግሞ በቃራኒው ከእምነቴ ውጪ የሆነ ነገር እንዳላራምድ መጠንቀቅ ከባድ ኃላፊነት ነበር፡፡ በሌላ ወገን አንባቢ የተሳሳተ ግምት እንዳያድርበትም እንዲሁ መጠንቀቅ ነበረብኝ፡፡ በተቀውሞው ጎራ ያለው ወገን ደግሞ ‹‹ተሸጠ፣ተለወጠ፣ ከኢህአዴግ ጋር ተሞዳሞደና እጅመንሻ የውዳሴ መፅሃፍ ፃፈ›› የሚል የተሳሳተ ሃሳብ ውስጥ እንዳይገባ ለመጠንቀቅ ሞክሬያለሁ፡፡በእነዚህ ሁለት ፅንፎች ውስጥ ለማለፍ ስሞክር ማስተላለፍ የፈለኩትን መሰረታዊ ሃሳብና ልከተል የፈለኩትን የሃሳብ መስመር ላለመልቀቅ ተፍጨርጭሬያለሁ፡፡ እንዲህ አይነት የሃሳብ ማእበል ሲኖር ምንም ያህል ቢደከምም የሚፈለገውን ያህል ሌላውን ቀርቶ እራስንም ለማስደሰት ይከብዳል፡፡ ኃላፊነት ከባድ ነው፡፡ ሁላችንም ከልዩነቶቻችን ይልቅ ወደአንድነታችንና በጎ ነገሮቻችንን እንደናይ የሚያስችል ፅሁፍ ለመፃፍ ሞክሬያለሁ፡፡ ስሜቴ አሸንፎኝ ልዩነቶቻችንን የሚያሰፋ ጎዳና ተከትዬ ከሆነ አንባቢ እኔ ያልሄድኩበትን መንገድ እንዲሄድበት እጋብዛለሁ፡፡ ምናልባት በለስ ቀንቶኝ አንድነታችንን የሚያጠናክርና እራሳችንን እንድናርም፤ ያለመቆጠብ ወደ ውስጣችን እንድናይ፣ ልዩነቶቻችንም በሰከነ መንገድ ለመፍታት እንድንችል ሃሳብ ሰንዝሬ ከሆነ በእንዲህ አይነት ሁኔታ ከተዘጋጀ መፅሃፍ ክፍተት አይጠፋምና አንባቢ ክፍተቶችን ለመሙላት ይሞክር፡፡ ውይይቱንም በማስፋት የተሸለና የተሞረደ ሃሳብ እንዲወለድ ሃገራችንም ከምትገኝበት አዘእቅት ውስጥ እንድትወጣ የበኩሉን አስተዋፅዎ ያድርግ ቢለዋ ከቢለዋ ሲፋጭ ስለት ይወጣዋልና፡፡››
 ምንጭ ዘ-ሐበሻ