Tuesday, December 10, 2013
አንዱዓለም አራጌ ከእስር ቤት “እኔ እስሩ አልከበደኝም፤ በጣም ያሳዘነኝ ግን በኔ መታሰር ልትጠቀሙበት አልቻላችሁም” አለ
(ዘ-ሐበሻ) የ2005 ዓ.ም የዘ-ሐበሻ አንባቢዎች ምርጥ ተብሎ የተሰየመውና በቃሊቲ ማረሚያ ቤት ዕድሜ ልክ እስራት ተፈርዶበት የሚገኘው ወጣቱ ታጋይ አንዱዓለም አራጌ እስር ቤት ሊጠይቁት ለሄዱት የተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎች መልዕክት አስተላለፈ። በጣም ማዘኑንም ገለጸ።
ዕድሜ ልክ እስራቱን ተቀብሎ እስር ቤት የሚገኘው አንዷለም አራጌ “ይቅርታ አልጠይቅም” በሚል እስካሁን በእስር ቤት እየማቀቀ ሲሆን “በእኔ መታሰር ብዙ ልትጠቀሙበት ስትችሉ አለመጠቀማችሁ ያሳዝነኛል:: እኔ አሁን በእስር ባለሁበት ሰዓት የኢትዮጵያን ሕዝብ የነፃነት ትግሉን ወደ ፊት ለመግፋት አጋጣሚ ሊሆንላችሁ ቢችልም አልተጠቀማችሁበትም ” ሲል የተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎችን መውቀሱን የዘ-ሐበሻ ታማኝ ምንጮች ገልጸዋል።
ዕድሜ ልክ እስራቱን ተቀብሎ እስር ቤት የሚገኘው አንዷለም አራጌ “ይቅርታ አልጠይቅም” በሚል እስካሁን በእስር ቤት እየማቀቀ ሲሆን “በእኔ መታሰር ብዙ ልትጠቀሙበት ስትችሉ አለመጠቀማችሁ ያሳዝነኛል:: እኔ አሁን በእስር ባለሁበት ሰዓት የኢትዮጵያን ሕዝብ የነፃነት ትግሉን ወደ ፊት ለመግፋት አጋጣሚ ሊሆንላችሁ ቢችልም አልተጠቀማችሁበትም ” ሲል የተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎችን መውቀሱን የዘ-ሐበሻ ታማኝ ምንጮች ገልጸዋል።
“እኔ መታሰሩና፤ በእስር ቤት እየደረሰብኝ ያለው ስቃይ አልከበደኝም። የከበደኝ ግን በኔ መታሰር ልትጠቀሙበት አለመቻላችሁ ነው። በኔ መታሰር መንግስት ብዙ ጫና ውስጥ እንዳለ ይታወቃል። በኔ መታሰር ብዙ ሥራ ልትሰሩበት፤ ትግሉን ወደፊት ልታስኬዱበት ስትሉ ይህን አላደረጋችሁም” ያለው አንዷለም አራጌ አሁንም የመንፈስ ጥንካሬው አብሮት እንዳለ በ እስር ቤት ካነጋገሩት ወገኖች መካከል ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ የተቃዋሚ ፓርቲ አመራር ለዘ-ሐበሻ ገልጸዋል።
አንዷለም አራጌ የፌደራሉ ማረሚያ ቤት የሚጠይቁህን ሰዎች ስም ዝርዝር አስመዝግብ ተብሎ ተጠይቆ የነበረ ሲሆን እርሱ ግን ማንም ሰው መጥቶ ሊጠይቀኝ መብቱ ነውና ስም ዝርዝር አውጥቼ አልሰጥም ሲል ፈቃደኛ አለመሆኑን ዘ-ሐበሻ ከዚህ ቀደም መዘገቧ አይዘነጋም።
Sunday, December 8, 2013
African Leaders Must Follow in Mandela’s Footsteps – Activists
BY TESFA-ALEM TEKLE, 6 DECEMBER 2013 (ST)
Addis Ababa — As the world mourns the passing of former South African president, Nelson Mandela, political activists in Ethiopia have stressed the need for African politicians to emulate the anti-Apartheid hero.
Reacting to reports of Mandela’s death, activists and ordinary Ethiopians in several interviews with Sudan Tribune said the former South Africa president’s passing should serve as a wakeup call for African leaders to “begin implementing best political practices.”
“African leaders must learn from Mandela on how to leave a better place to the continent and to the world at large” Solomon Negassi, an Ethiopian politician told Sudan Tribune.
Negassi said African leaders are failing in working towards building unity, national reconciliation, Justice and human rights in their respective countries.
Separately, Genet Yohannes, an economist, says unless African leaders follow a positive political path like Mandela achieving African unity will be difficult.
Mandela, who died on Thursday at the age of 95, became the first South African Black president in 1994 after he spent 27 years in prison under the then Apartheid regime.
After serving one term as a president, Mandela handed over power to Thabo Mbeki in 1999, something uncommon among African leaders.
An Ethiopian opposition official who sought anonymity told Sudan Tribune that African leaders particularly the despotic must learn from Mandela and limit their stay in office.
“African leaders must learn to limit their grip on power” the opposition official said adding “I don’t think African leaders are yet ready to make such a decision”
Once he gained power, Nelson Mandela, winner of the 1993 Nobel Peace Prize didn’t seek reprisal against those – under the white minority rule – that threw him in prison to serve a long jail term.
A memorial service will be held in Johannesburg on December 10 and his funeral will take place on 15 December.
ETHIOPIA PAYS TRIBUTE
In a statement released on Friday, Hailemariam Dessalegn, the Ethiopian prime minister and African Union (AU) chairperson expressed sympathy with the family of Mandela and the South African people.
“President Mandela did not only lead his country’s struggle against Apartheid but has also been the torch bearer in the quest for Africa’s freedom” said a statement by the ministry of foreign Affairs.
Mandela inspired generations of world leaders to stand for justice, human dignity and freedom.
The Anti-Apartheid icon was in Ethiopia during his exile in the 1960s while he was leading the struggle for freedom.
“Indeed, President Mandela leaves behind a great vision from which all of us Africans should draw inspiration” said the Ethiopian premier.
The statement added the Ethiopia government will continue to value the principles of democracy, freedom, justice, tolerance and reconciliation for which President Mandela dedicated his life.
source Ethiopian media forum.
Friday, December 6, 2013
በወያኔ ስርዓት ውስጥ በሙስና ያልተጨማለቀ ሰው ቢኖር እኔ ነኝ ዓሉ ወ/ሮ አዜብ
የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ሰራተኛ የነበሩት አቶ ወልደስላሴ ወልደሚካኤል ከሁለት ቤተሰቦቻቸው ጋር በተጠረጠሩበት የሙስና ወንጀል ተጨማሪ ክስ ተመሰረተባቸው። “የአቶ ወልደስላሴ እህት የ8ኛ ክፍል ተማሪ ስትሆን ፥ ምንም አይነት የገቢ ምንጭ የሌላት እንደሆነች ነው በክስ መዝገቡ የተገለጸው…ግለሰቧ በ 81 ሺ ዩሮ የተገዛ አንድ ስካቫተር ፣ አውቶሞቢል መኪና፣ በአዲስ አበባ ቦሌና የካ ክፍለ ከተሞች እንዲሁም በለገጣፎ ፣ በመቀሌና አክሱም ከተሞች 3 ሺህ 266 ካሬ ሜትር ቦታዎች በስሟ ተመዝግቧል ፤ በተለያዩ ባንኮችም ከ 8 ሚሊየን ብር በላይ ተቀማጭ ገንዘብም እንዲሁ ተመዝግቧል።…….” ተከሳሾቹ አቶ ወልደስላሴ ወልደሚካኤል፣ የመከላከያ ሚኒስቴር ባልደረባ የነበሩት ወንድማቸው ዘርአይ ወልደሚካኤል፣ እህታቸው ወይዘሪት ትርሃስ ወልደሚካኤልና የቅርብ ጓደኛቸው ዶሪ ከበደ ናቸው ።ተከሳሹ በ 2002 ዓ.ም ቱሪዝም ኢን ኢትዮዽያ ኤንድ ዘ ሆርን ኦፍ አፍሪካ የተሰኘ መጽሃፍ ያሳተሙ ሲሆን ፥ ይህንን መጽሃፋቸውን በስፖንሰር ለማሳተም ባደረጉት እንቅስቃሴም የመንግስት የልማት ድርጅቶች ተቆጣጣሪ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር የሆኑትን አቶ በየነ ገብረስላሴ የነበራቸውን ቀና አስተሳሰብ ተጠቅመው ያለአግባብ በልጽገዋል ነው የሚለው የክስ መዝገቡ። መጽሃፉ በመስሪያቤታቸው ስም እንደተዘጋጀ በሚያስመስል ሁኔታ አቶ በየነ የሚመሯቸው የቦሌ፣ የብርሃንና ሰላምና የአርቲስቲክ ማተሚያ ቤት ሃላፊዎች በጋራ የአቶ ወልደስላሴን 3 ሺህ መጻህፍት በ124 ሺህ ብር እንዲያሳትሙ ተደርጓል ነው የሚለው ክሱ።
ማተሚያ ቤቶቹ በርካሽ ያሳተሙት አቶ ወልደስላሴ ከነበራቸው ተሰሚነትና ስልጣን መነሻነት መሆኑንና ይህንን መጽሃፍ ኢትዮ ቴሌኮም ምንም በማይመለከተው 10 ሺህ መጻህፍት የሚታተሙበትን የ385 ሺህ ብር ክፍያ ለአቶ ወልደስላሴ እንዲከፍልም መደረጉንም ነው የክስ መዝገቡ የሚያስረዳው። አቶ ወልደስላሴ የሙገር ሲሚንቶ ኢንተርፕራይዝና የአትክልትና ፍራፍሬ ገበያ ማህበር የቦርድ ሰብሳቢ በነበሩበት ጊዜ ሃላፊነታቸውነ ተጠቅመው ፥ ሁለቱ ድርጅቶች 310 ኮፒዎችን በግድ እንዲገዙ መደረጉም ተመልክቷል። 26 የሚሆኑ ግለሰቦችና ድርጅቶችም እያንዳንዳቸው ከ 25 እስከ 1ሺህ 500 ፥ በጥቅሉ ከ73 ሺህ የሚልቁ ኪፒዎችን ሳይወዱ በግድ እንዲገዙ መደረጉ ፣ ይሄ ሁሉ ሲደረግ ተቋማቱ ለመጻህፍቱ ገንዘብ ከፍለው መጻህፍቱን አለመረከባቸውም ጭምር ነው በክስ መዝገቡ የተዘረዘረው። ተከሳሹ አቶ ወልደስላሴ ባልደረባቸወ የሆኑ አንዲት ሴት ጋር በነበራቸው መቀራረብ የመስሪያቤቱን መኪና በህገ ወጥ መንገድ ነዳጅ እያስሞሉ ግለሰቧ እንደልባቸው በአዲስ አበበባና ከከተማ ውጪ እንዲጠቀሙበት አስደርገዋል የሚለውም ተጠቅሶባቸዋል።
ተከሳሹ ከ2003 እስከ 2004 ዓ.ም አቶ ሳቢር አርጋው የተሰኙ ነጋዴን ለምሰራው ቤት ሴራሚክ ስለጎደለኝ የጣሊያን ስሪት ገዝተህ ስጠኝ በማለት ፥ በስልጣናቸው አስፈራርተዋቸው የ65 ሺህ ብር ሴራሚክ ተቀብለዋል ፣ ከ 2001 እስከ 2005 ባሉት የግብር አመታት አሳትሞ ከሸጣቸው መጻህፍት ካገኘው ገቢ ላይ መክፈል የነበረበትን ከ496 ሺህ ብር በላይ ለመንግስት አስታውቆ አለመክፈሉም ተጠቅሷል። ተከሳሹ ባለ4 ፎቅ የግል ቤቱን ወንድሙ ለሆነው ሁለተኛ ተከሳሽ ዘርአይ ወልደስላሴ ውክልና ሰጥቶና ከመኖሪያ ቤት ውጭ ለሆነ አገልግሎት እንዲውል አድርጎ በ14 ወራት ውስጥ 790 ሺህ ብር ገቢ አግኝቷል ፤ ከገቢው 126 ሺህ ብር የሚሆነው የመንግስት ግብርን ለግብር አስገቢው መስሪያቤት ሃሰተኛ መግለጫ በማቅረብ ሳይከፍል መቅረቱም በክሱ ተመልክቷል። ከዚሁ ቤት ኪራይ መንግስት ከተርን ኦቨር ታክስ ማግኘት የነበረበትን ከ119 ሺህ ብር በላይ ገቢ ሳያገኝ መቅረቱና ተከሳሹ በህገ ወጥ መነገድ ያገኘውን ገንዘብ ማንም እንዳያውቅበት ለማድረግ በሰኔ 28 1998 ዓ.ም ለሁለተኛው ተከሳሽ (ወንድም) ዘርአይ ወልደሚካኤል ሙሉ ውክልና መስጠቱ ተዘርዝሯል።
እንዲሁም ምንም አይነት የገንዘብ ልውውጥ ሳያደርጉ ከ3ኛዋ ተከሳሽ እህቱ ትርሃስ ጋር መጋቢት 24፣ 2005 ዓ.ም የብድር ውል ማድረጋቸውም ተጠቅሷል።በተጨማሪም ተከሳሹ ከእህቱና ወንድሙ ጋር ያለአግባብ አፈሯቸው የተባሉ የገንዘብና የአይነት ሃብቶች በክስ መዝገቡ ተጠቅሰዋል። 1ኛው ተከሳሽ ወልደስላሴ ወደሚካአል ከ1983 እስከ የካቲት 2005 ዓ.ም የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት የውስጥ ሰራተኛ ሆኖ ሲሰራ ፥ ወርሀዊ ደመወዙ ከ 1,600 እስከ 6,000 ብር የነበር ሲሆን ፥ ነገር ግን ስልጣኑን እና የነበረውን ተሰሚነት በመጠቀም በፈጸመው የሙስና ወንጀል ከባለ4 ደረጃ ህንጻ ውጪ ፣ ከ3 ሚሊየን ብር በላይ በተለያዩ የግልና የመንግስት ባንኮች ተቀማጭ ማድረጉም ተመልክቷል። 2ኛ ተከሳሽ አቶ ዘርአይ ወልደስላሴ ከመከላከያ ሚኒስቴር በጡረታ እስከሚገለል ድረስ ወርሀዊ ደመወዙ 532 ብር የነበር ሲሆን ፥ በክስ መዝገቡ ተከሳሹ በተለያዩ ባንኮች 5 ሚሊየን ብር የሚጠጋ ገንዘብ ማስቀመጡ ፣ በአዲስ አበባ ቤቴል ቁጥር 3 በተባለ አካባቢ በ74 ካሬ ሜትር ይዞታ ላይ መሰረት የተጀመረበት ቦታ ፣ በአፋር ክልል ከ 1 ነጥብ 4 ሚሊየን ብር በላይ ግምት ያላቸው ሁለት የእርሻ ኢንቨስትመንቶችና 2 ነጥብ 7 ሚሊየን ብር ግምት ያላቸው ሁለት ሎደር ማሽነሪዎችም በስሙ መኖራቸው ተመዝግቧል ።
3ኛዋ ተከሳሽ የአቶ ወልደስላሴ እህት የ8ኛ ክፍል ተማሪ ስትሆን ፥ ምንም አይነት የገቢ ምንጭ የሌላት እንደሆነች ነው በክስ መዝገቡ የተገለጸው።ግለሰቧ በ 81 ሺ ዩሮ የተገዛ አንድ ስካቫተር ፣ አውቶሞቢል መኪና፣ በአዲስ አበባ ቦሌና የካ ክፍለ ከተሞች እንዲሁም በለገጣፎ ፣ በመቀሌና አክሱም ከተሞች 3 ሺህ 266 ካሬ ሜትር ቦታዎች በስሟ ተመዝግቧል ፤ በተለያዩ ባንኮችም ከ 8 ሚሊየን ብር በላይ ተቀማጭ ገንዘብም እንዲሁ ተመዝግቧል።
http://www.zehabesha.com/amharic/archives/10554
Tuesday, December 3, 2013
የወያኔ አገዛዝ በመልዕክተኞቹ በኩል ላቀረበው የ“እንደራደር” ጥያቄ ከግንቦት 7 የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ የተሰጠ ምላሽ
ወያኔ ኢትዮጵያ ዉስጥ የገነባዉ ሥርዓት በከፍተኛ ችግሮች የተወጠረ ነው። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ የመሪው ሞት በወያኔ መሀል ያስከተለው ቀውስ፤ የሕዝብ ሁለገብ ትግል ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጎለበት መሄድ የፈጠረበት ስጋት እና ምርጫ በደረሰ ቁጥር የሚደርስበት ጭንቀት መጨመር ተደማምረው ውጥረቱን ወደ ከፍተኛ ደረጃ እያደረሱት መሆኑን የሚያሳዩ በቂ ምልክቶች አሉ። የእስካሁኑ ተሞክሮዓችን እንደሚያሳየው ወያኔ ውጥረት ሲበዛበትና መዉጪያና መግቢያዉ ሲጠፋዉ ፣ ተቃዋሚ ድርጅቶችን “እንወያይ፣ እንደራደር” በማለት ለውጥረት ማስተንፈሻ ጊዜ የሚገዛ መሆኑን ነው። ሰሞኑን በወያኔ አገዛዝ መልዕክተኞች በኩል የደረሰንን “የእንደራደር” ጥያቄ ንቅናቄያችን በዋናነት ያየው ወያኔ እንደለመደው ድርድርን ለውጥረት ማስተንፈሻነት ለመጠቀም እየሞከረ መሆኑን ነው።
የኢትዮጵያ ሕዝብ የሚመኘው ዲሞክራሲያዊ ለውጥ በሰላማዊ መንገድ በሚደረግ ትግልና በጠረጴዛ ዙሪያ በሚደረጉ ዉይይቶች ቢመጣ የግንቦት 7 ምርጫ መሆኑን ንቅናቄያችን በተደጋጋሚ ግልጽ አድርጓል። ግንቦት 7ን ሁለገብ ትግል ውስጥ እንዲገባ ያስገደደው የወያኔ እምቢተኝነትና እብሪት ብቻ ነው።
የግንቦት 7 ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ የሰሞኑ የወያኔ የእንደራደር መልዕክት እንደደረሰው በጉዳዩ ዙሪያ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ይህ ጉዳይ የኢትዮጵያን ሕዝብ ባጠቃላይ እንጂ ግንቦት 7ን ብቻ የሚመለከት ጉዳይ እንዳልሆነ ከድምዳሜ ላይ ደርሷል። ይህ ጉዳይ የኢትዮጵያ ሕዝብ ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ከሚያደርገው ትግልና እየከፈለ ካለው መስዕዋትነት ጋር በቀጥታ ግንኙነት አለው። በመሆኑም፤ ለቀረበልን ጥያቄ ግልጽ መልስና፤ ድርድር ስለሚባለው ጉዳይም ያለንን አቋም ጉዳዩ በቀጥታ ለሚመለከተው የኢትዮጵያ ሕዝብና የተለያዩ የፖለቲካ ድርጅቶች ሁሉ ለማቅረብ የሚያስችል ተጨማሪ አጋጣሚ አድርገን ወስደነዋል። በዚህም መሠረት ለቀረበልን ጥያቄ የሰጠነዉን መልስና አቋማችንን በድርጅታችን ድረ ገጽ ላይና በሌሎች መገናኛ ብዙሀን በኩል በይፋ ለመግለጽ ወስነናል።
በድርድር ስለሚመጣ ለውጥ ያለን የመርህ አመለካከት:
ከዚህ በፊት በተደጋጋሚ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ግልጽ እንዳደረግነው ድርጅታችን ከምሥረታው ጀምሮ የትግል ስልቱን ሲወስን እምነቱ አድርጎ የተነሳው ዴሞክራሲያዊ ለውጥ በሀገራችን በሰላማዊ መንገድና በድርድር ቢመጣ በእጅጉ የሚፈልገውና የሚመኘው መሆኑን ነው:: ድርጅታችንን ወደ ሁለንተናዊ ትግል የገፋው በመግቢያው ላይ እንደገለጽነው የወያኔ እብሪት ብቻ ነው:: የቀረበልን ምርጫ በባርነትና በውርደት መኖር ወይም ለነፃነት እየታገልን መሞት ቢሆን ኖሮ ንቅናቄያችን የሚመረጠው ምን ግዜም ለነፃነትና ለአገር አንድነት ታግሎ በክብር መሞት መሆኑን በተደጋጋሚ ለሕዝብ ግልጽ አድርገናል። ይህ የማይናወጥ አቋማችን ደግሞ ለይምሰል የተቀመጠ አቋም ሳይሆን ከልባችን የምናምንበትና ኢትዮጵያን ጨምሮ በዓለም ዙሪያ የሚገኙ አባላቶቻችንን ያሰባሰብንበት አቋም ነው። ዛሬ በትግሉ ግንባር የምንንቀሳቀሰውና ወደ ግባችን የሚወስደንን ተጨባጭ እርምጃዎች እየወሰድን ያለነውም በዚሁ አቋማችን ዙሪያ ነዉ።
ይህ አቋማችንና እምነታችን በአንድ ላይ ጎን ለጎን የሚሄዱ ሁለት መርሆችን አጣምሮ የያዘ ነዉ። አንደኛው፣ ሂደትን በሚመለከት ሁሌም ለድርድር ክፍት መሆኑን የሚያመለክት ሲሆን፣ ሁለተኛው ደግሞ፣ ይህ የድርድር ሂደት እንዲያው ለለበጣ የሚደረግ ሳይሆን ወደሚፈለገው ነጻነት በአነስተኛ መስዕዋትነት ሊያደርስ ይችል ከሆነ በሩን ላለመዝጋት እንጂ፣ በምንም አይነት ዋና ውጤቱን፤ ማለትም ኢትዮጵያን እውነተኛ ዴሞክራሲያዊ ሀገር ማድረግን፤ የሚቀይር ወይንም ከዚያ ያነሰ ውጤትን ለመቀበል መፍቀድን ፈጽሞ የማያመለክት መሆኑን ነው::
በእኛ በኩል ድርድሩን አስፈላጊና ጠቃሚ የሚያደርጉት መነሻ የፖለቲካ እሳቤዎችም ከእነኝሁ ሁለት መንታ ገጽታዎች የሚመነጩ ናቸው:: በድርድር ለሚገኝ ፍትሀዊና እውነተኛ ውጤት ክፍት መሆናችንን ሁሌም እናሳያለን፤ ነገር ግን ይህን የምናደርገው የሕዝብ የሥልጣን ባለቤትነት የተረጋገጠባትን ኢትዮጵያን እውን ማድረግ የሚጠይቀውን ማንኛውንም መስዋዕትነት መከፈል አለበት የሚለውን መሠረታዊ የአካሄድ መርህ በመመርኮዝ እንጂ መርሀችንን ለድርድር ለማቅረብ እንዳልሆነ በግልጽ መታወቅ ይኖርበታል::
ስለዚህም:
ሀ) የድርድሩ ውጤት የኢትዮጵያን ሕዝብ የሥልጣን ባለቤትነት ያረጋገጠ የዴሞክራሲያዊ ሥርዓትን በአስቸኳይ እውን ማድረግ መሆን ይኖርበታል:: ይህ ዋናው ግብ ሆኖ ከዚህ በመለስ የሚኖሩ በሂደት የሚገኙ አነስተኛ ግቦች ሊኖሩ ይችላሉ (ለምሳሌ የፖለቲካ እስረኞች ማስፈታት…ወዘተ):: ሆኖም በምንም አይነት ለእነኝህ መለስተኛ ግቦች ተብሎ ዋናውን ግብ የሚያሳጣ ወይንም ጊዜውን ያላግባብ የሚያስረዝም ድርድር፣ ድርድር ነው ብሎ ድርጅታችን አይቀበልም። ስለዚህም ዋናው የድርጅታችን ዓላማና ግብ የሆነው የኢትዮጵያ ሕዝብ የሥልጣን ባለቤትነት ፣ በፍጹም ለድርድር የሚቀርብ ጉዳይ አይደለም:: በሥልጣን ላይ ባለው ኃይል በኩል ወደዚህ ግብ ለመድረስ ቁርጠኝነቱ በሌለበት ሁኔታ በሚደረግ ማንኛውም አይነት ድርድር ውስጥ ግንቦት 7 አይሳተፍም::
ለ) በግንቦት 7 እምነት ማንኛውም ድርድር ወያኔ ከግንቦት 7 ጋር በተናጠል የሚያደረገው ሳይሆን ጉዳዩ የሚመለከታቸውን ሁሉንም የፖለቲካ ኃይሎች ያካተተ መሆን ይኖርበታል:: ድርጅቶችን በተናጠል እየለያዩ “እንደራደር” ማለት በራሱ ጊዜያዊ የፖለቲካ ጥቅም ስሌትን የያዘ እሳቤ እንጂ፣ በዘላቂነት አገሪቱን እውነተኛ ዴሞክራሲያዊ አገር ለማድረግ መፈለግን አያመለክትም:: ለአንድ ድርጅት ለብቻው የሚመጣ ወይም የሚጠቅም ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት የለም:: ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት የመፍጠር ፍላጎት ያለው ድርድር በአገሪቱ ያሉትን የተለያዩ የፖለቲካም ሆነ የሲቪክ ኃይሎችን ያካተተና ያመኑበት መሆን ይኖርበታል:: የሚደረገው ድርድርም ማን በስልጣን ላይ ይውጣ ወይንም የፖለቲካ ስልጣንን ባሉት ኃይሎች መሀከል እንዴት እናከፋፍለው የሚል የስልጣን ቅርምት ድርድር ሳይሆን፤ ሕጋዊና የሕዝቡን የሥልጣን ሉዓላዊነት ባረጋገጠ ሁኔታ የፖለቲካ ስልጣን እንዴት እንደሚያዝ ፍትሀዊ የሆነ ሂደትን ለማስጀመር የሚደረግ ድርድር መሆን አለበት::
ሐ) ቀደም ብለን እንደጠቀስነው ይህ ጉዳይ የሚመለከተው አንድን ድርጅት ወይንም የፖለቲካ ድርጅቶችን ብቻ ሳይሆን መላውን የኢትዮጵያን ሕዝብ ነው:: ይህ እስከሆነ ድረስ እንዲህ አይነት ድርድር ከሕዝቡ በተደበቀ ሁኔታ በሚስጥር የሚካሄድበት ምንም ምክንያት የለም::
2) ከዚህ በፊት ከወያኔ ጋር ከተደረጉ ድርድሮች ያገኘናቸው ተመክሮዎችና ከዚህ በመነሳት ወደፊት በሚደረጉ ምንም አይነት ድርድሮች እንዳይደገሙ ለመጠበቂያ የሚሆኑ ከአሁኑ መወሰድ ያለባቸው እርምጃዎች
ከማንኛውም ወገን ጋር የሚደረግ ድርድር የተደራዳሪዎቹ ምንነት፤ ውስጣዊ ባህርያቸውን፤ ከተለምዶ ተግባራቸው ያላቸውን ተአማኒነትና ወደዚህኛው ድርድር ያመጣቸውን ምክንያቶች በበቂ ከመገንዘብ ጋር ተያይዞ የሚታይ ጉዳይ ነው:: ቃሉን አክባሪና ተዓማኒ ከሆነ ሰው ጋር የሚደረግ ድርድርና ያለፈው ታሪኩ ምንም አይነት የተዓማኒነት ባህርይ ከማያሳይ ቡድን ጋር የሚደረግ ድርድርም ሆነ ለድርድሩ የሚደረግ ዝግጅት ለየቅል ናቸው:: ይህ ማለት ግን ተዓማኒነት ካለው ኃይል ጋር ብቻ ነው ድርድር የሚካሄደው ማለት አይደለም:: በፍጹም ተዓማኒ ካልሆነ ኃይል ጋር የሚደረግ ማንኛውም ድርድር ግን ድርድሩ በእርግጥም ተግባራዊ ሊሆን የሚችል መሆኑን የሚያሳዩ ጠንካራ መጠበቂያዎች (System of Verification) እንዲሁም ግልጽ የመተግበሪያ ሥርዓቶች (Implementation Mechanism) ሲደረጉለት ብቻ ነው ከምር ሊወሰድ የሚችለው:: ከዚህም ባሻገር ግን መጀመሪያውኑ ወደ ድርድር የሚመጣው ለጊዜያዊ የፖለቲካ ጥቅም ሳይሆን በእዉነተኛ መንፈስ ከድርድር የሚመጣውን ውጤት በመፈለግ መሆኑን የሚያሳዩ “የመተማመኛ” ምልክቶች ሲያሳይ ነው በእርግጥም ወደ ድርድር የመጣው ከልቡ ድርድሩንና ከድርድሩ የሚመጣዉን ዉጤት ፈልጎ መሆኑን ለማመን የሚያስችለው::
ወያኔ ከተቀናቃኝ ወገኖች ጋር “ድርድር” ሲያደርግ የመጀመሪያ ጊዜዉ አይደለም:: እኛ እስከምናውቀው ድረስ ምናልባት በኃይል ይበልጡኛል ብሎ ከሚያምናቸው ወገኖች ጋር ካልሆነ በስተቀር፣ በረሃ ከነበረበት ጊዜ ጀምሮ በማንኛውም ጊዜ ለቃሉ ታማኝ፤ ለመርሁ እውነተኛ፤ ለደረሰበት ስምምነት ተገዢ ሆኖ አያውቅም:: ይልቁንም ሶስተኛ አደራዳሪ ወገኖችን በሚያሸማቅቅና በሚያሳፍር መልኩ ውሸትን እንደ አዋቂነት፤ ማጭበርበርን እንደ ብልጠት፤ የተስማማበትን በገሀድ ማፍረስን እንደ የአመራር ብልሀት አድርጎ የሚያይ፤ ምንም እፍረትና ጨዋነት የሚባል ነገር ያልፈጠረበት እኩይ ኃይል ነው:: ከራሱ የድርጅት ጥቅምና በስልጣን ከሚገኝ የዝርፊያ ሀብት ማካበት ባሻገር፤ ለአገር ዘላቂ ጥቅም ብሎ የራሱን ጥቅም አሳልፎ የሚወስደው ምንም እርምጃ እንደሌለ በተግባር በተደጋጋሚ ያረጋገጠልን ኃይል ነው:: በግንቦት 7 ውስጥ ያለን ወገኖች ይህንን የወያኔ ባህርይ በንድፈ ሀሳብ ደረጃ ሌሎች ጽፈውት ያነበብነው ሳይሆን፣ እራሳችን በተግባር በተሳትፈንበት ሂደት ያገኘነው ጥልቅ ግንዛቤ ነው:: ይህንን ደግሞ በአንድ አጋጣሚ ብቻ ሳይሆን ከድርጅቱ ታሪክ ጋር የተጣበቀ፤ በአመራር አባላቱ ላይ እንደ ግል ባህርይ የሰረጸ መሆኑን እስክንገነዘብ ድረስ በተደጋጋሚ የተመለከትነው ነው:: ስለዚህም ከዚህ ኃይል በኩል የሚመጣን የ “እንደራደር” ጥያቄ ከዚህ በፊት እንዳደረገው ለገባበት የፖለቲካ ውጥረት ማስተንፈሻ፣ ለውሸት ፕሮፓጋንዳው መጠቀሚያ፤ ለጊዜያዊ የፖለቲካ ትርፍ መሰብሰቢያ፤ የዴሞክራሲ ታጋዮችን ትጥቅ ማስፈቺያና ወኔ መስለቢያ አድርጎ እንዲጠቀምበት በፍጹም አንፈቅድለትም:: ስለዚህም ከላይ በመርህ ደረጃ ከጠቀስናቸው ሶስት ጉዳዮች በተጨማሪ ምንም ዓይነት ድርድር ከመደረጉ በፊት ወያኔ ጉዳዩን ከምር የወሰደው መሆኑን የሚያሳዩ “የመተማመኛ” እርምጃዎች መውሰድ አለበት ብለን እናምናለን::
እነኝህም፣
ሀ) ሁሉንም የፖለቲካ እስረኞች፤ ጋዜጠኞች፤ የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች ያለምንም ቅድመ ሁኔታ መፍታት:: ይህ ደግሞ በግልጽ የሚታወቁ እስረኞችን ብቻ ሳይሆን በድብቅ የተቋቋሙ ማጎሪያና ማሰቃያ ቤቶች ያሉትን ሁሉ ማጠቃለል አለበት።
ለ) በሕዝብ በተለይ በተቃዎሚ ኃይሎች ላይ ወያኔ በየቀኑ እያካሄደ ያለውን ወከባና እንግልት ባስቸኳይ ማቆም፣ ሰብዓዊና የዜግነት መብታቸውን ማክበር አለበት።
ሐ) በፖለቲካ ምክንያት ከዚህ በፊት የተወሰዱ ሁሉም ዓይነት ፍርድ ተብዮ ውሳኔዎች እንዲሻሩ ማድረግ፤ በሂደት ላይ ያሉ ከፖለቲካ ጋር የተያያዙ ምንም አይነት ክሶችን ማቋረጥ አለበት።
መ) ሕዝብን በፍርሃትና በስጋት ለማቆየት ሆነ ተብለው የወጡ አፋኝ ህጎችን በአስቸኳይ ማንሳት አለበት።
ሠ) ማንኛውም ድርድር ገለልተኛ የሆኑ ሶስተኛ ወገኖች ባሉበት፤ የድርድሩ ሂደት በምስልና በድምጽ ተቀርጾ በገለልተኛ ወገኖች እጅ ብቻ የሚቀመጥ፣ የድርድሩ ቦታም የተደራዳሪ ወገኖች በጋራ በሚስማሙበት ቦታ መሆኑን መቀበልና ይህንንም በግልጽ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ማሳወቅ አለበት።
እነኝህ ከላይ ያስቀመጥናቸው በወያኔ በኩል የሚወሰዱ “የመተማመኛ” እርምጃዎች ለተቃዋሚዎች ተብሎ የሚወሰዱ እርምጃዎች አይደሉም:: ወያኔ እነዚህን እርምጃዎች ለመውሰድ ቁርጠኝነት ሳይኖረው ለእውነተኛ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት መመስረት የሚደረግ ድርድር ላይ ከምር ይሳተፋል ብለን ማመን በፍጹም ስለማንችል ነው ::
እስከዚያው ድረስ ግን ግንቦት 7ም ሆነ ሌሎች ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት መመስረት በቁርጠኝነት የምንታገል ኃይሎች፣ ወያኔ እነኝህን የመተማመኛ እርምጃዎች እስኪወስድና ቀደም ብለው በተቀመጡት መርሆች መሠረት በሚደረግ ድርድር በተግባር ሊመነዘር የሚችል ስምምነት፣ አልፎም ለምንም አይነት ማጭበርበርና መንሸራተት እድል የማይሰጥ ጠንካራ መጠበቂያዎች መኖራቸው እስኪረጋገጥ ድረስ፣ የጀመርነውን ትግል ይበልጥ አጠናክረን የምንገፋበት እንጂ በምንም አይነት ለአንድ አፍታም ቢሆን በድርድር ስም የማንዘናጋ መሆኑን አበክረን እናስታውቃለን::
የግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ፣
ኅዳር 23፣ 2006 ዓ:ም
Monday, December 2, 2013
ኡ ኡ - የመግባባት ያለህ!! ግርማ ሠይፉ ማሩ
ግርማ ሠይፉ ማሩ
ኢትዮጵያዊያን በተለያየ ፓርቲ አባል ሆንን ማለት ላለመግባባት ቃልኪንዳን ያሰርን እስኪመስል ድረስ መላቅድሳችንየጠፋብን ይመስለኛል፡፡ ለምሳሌ የመለስን ራዕይ እናሳካለን በሚለው ዙሪያ መስማማት ላይጠበቅብን ይችላል፡፡ እንጋባባ
ሲባል ደግሞ አንድ እንሁን ማለታችን አይደለም፡፡ ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማሪያም እንደሚሉት ከፋብሪካ እንደወጣ
ሳሙና አንድ መሆን የህይወትን ቅመም ያሳጣል ብቻ ሳይሆን ለስው ልጅ ተፈጥሮውም አይደለም፡፡ በቤት ውስጥ እንኳን
አንድ ዓይነት መሆን ለጫወታም አይመችም፡፡ ከኢህአዴግ ጋር ለመግባባት ብሎ እናስቀጥላለን የሚሉትን የሟች ጠቅላይ
ሚኒስትር ራዕይ ማወቅ የሚፈልግ አንድ ቅን ሰው ቢገኝ ይህ የሚባለውን ራዕይ በግልፅ ከየትም አያገኝም፡፡
እርግጠኛ ሆኜ የምነግራችሁ የመጀመሪያ ደረጃ ተማሪዎች፣ የወጣትና የሴት ሊግ አባላት፣ የሀርብቶ አደርና
የሌሎችም መሰል ስብሰባዎች መሪ መፈክሮች ስለ መለስ ራዕይ የሚያወሩ ቢሆንም አንድም ተመሳሳይ የሆነ አጭር
ሀረፍተ ነገር “የመለስ ራዕይ ይህ ነው” ብሎ የሚያስረዳችሁ አታገኙም፡፡ አሁን ደግሞ የመለስ አሰተምሮ የሚል ፈሊጥ መጥቶዋል፡፡
ለእኔ ራዕይ የሚባለው በረጅም ጊዜ ለመድረስ ያሰብንበት ግብ (የተለወጠ ደረጃ) ሲሆን እዚያ ግብ ለመድረስ ግን ብዙ የምናደርጋቸው
ተግባራዊ እንቅስቃሴዎች መኖር ይኖርባቸዋል፡፡ የእነዚህ ተግባራት ድምር ነው በእርግጥ ካስብንበት የሚያደርሰን፡፡ ራዕይ ያለ ትክክለኛ
ተግባር የተሳሳተ ጅምር ከመሆን አያልፍም (Vision without proper action is a false start)፡፡ ስለዚህ ዛሬ “ራዕይ”
እናሰቀጥላለን ከሚሉ የጅምላ መፈክሮች ወጥትን መቀጠል የሌለባቸውን የተሳሳቱ ተግባሮችን እያነሳን መወያየት ተገቢ መሰለኝ፡፡
መግባባት ያለብን ነው ብዬ ስለማምን፡፡
ከነዚህ የተሳሳቱ ተግባሮች አንዱ በተለያዩ ደረጃ ያሉ ሞዴል/አርሃያ ያላቸውን ሰዎች ያለማመስገን ሲሆን የሚከፋው ደግሞ እነዚህን ሰዎች
እየተከታተሉ አንገት የማስደፋት ተግባር ነው፡፡ ባለ ራዕይ መሪዎች ይህን አያደርጉም፤ ይልቁንም እነዚህ ሰዎች እንዲበራከቱ እና ለጋራ
ራዕይ ሌሎችን እንዲያስልፉ ያበረታታሉ፣ አርሃያም ይሆናሉ፡፡ ኢህአዴግ ከዚህ አንፃር ባህሪው እንዴት ነው የሚታየው የሚል ነገር በሃሳቤ
መጣና ብንወያይበት እና ለመግባባት መንገድ የሚከፍት ከሆነ ብዬ ኡ! ኡ! ማላት ፈለግሁ፡፡ መጮኽ፡፡ ለዚህ ጩኸት መነሻ የሆኑኝ
በአጭሩ የሚከተሉት ናቸው፡፡
በቅርቡ አሜሪካን ያለ አንድ ወዳጃችን (ግርማ ጌታቸው ካሣ የሚባል) በሳውዲ ጉዳት ስለደረሰባቸው ዜጎቻችን የተሰማውን መልዕክት
ሲያስተላልፍ የኢህአዴግ ባለስልጣናትን በጅምላ ክፉና ጭራቅ አድርጎ መሳል ተገቢ አለመሆኑን አበክሮ አንስቶ ከእነ ሽመልስ ከማል
ዓይነት አደገኞች ኢህአዴግንም ቢሆን መጠበቅ እንደሚያስፈልግ እና እንደ ዶክተር ቴዎድሮስ አድሃኖም ዓይነቶችን ደግሞ ማወደስ
እንደሚያስፈልግ ጠቆም አድርጎ ነበር፡፡ የዚህ መልዕክት በጎ መሆን የሚያጠራጥር አይደለም፡፡ ይህ ፅሁፍ በደረሰኝ ዕለት ምሽት ደግሞ
እንዲሁ በኢህአዴግ ሰፈር በደግ ስለሚነሳ ታታሪ ታጋይ እና የኢህአዴግ ሹመኛ የሆነ አቶ ሀይለሥላሴ ቢሆን የሚባል በዓለማችን ከጦር
መሳሪያ ቀጥሎ አደገኛ ሙስና ውስጥ ለውስጥ የሚስራበትን የሕክምና መሳሪያዎችና መድሐኒት የሚቆጣጠር መስሪያ ቤት እየመራ በክፉ
ሰሙ የማይነሳ ሰው መሆኑን ሰዎች ነገሩኝ፣ በስራ አጋጣሚ ግለሰቡን ስለማውቀው የሚሉትን ለማመን ብዙ አልተቸገርኩም፡፡
በዚያው ሰሞን በእድሜ ልክ እስር ነገር ግን ከህሊና ዕዳ ነፃ የሆነው ወንድማችን አንዱዓለም አራጌ በጻፈው መፅሃፍ ደግሞ ወደ 1997
ምርጫ ወስዶ አቶ አርከበ ዕቁባይ በአዲስ አበባ ምርጫ ያለመመረጣቸው አንዳንዴ ፍርዳችን ፍርደ ገምድልና የጅምላ እንደሆነ ጠቅሶ
አስነበበን፡፡ የሚገርማችሁ ከ1997 ምርጫ ቀደም ብሎ ሟቹ ጠቅላይ ሚኒስትር ኤች.አይ.ቪ/ኤድስን በሚመለከት ምንም ቃል
በማይሉበት ወቅት አቶ አርከብ ዕቁባይ እራሳቸው ኤች.አይ.ቪ ተመርምረው በአዲስ አበባ አስደናቂ የመሪነት ሚና ሲጫወቱ ይህን እንደ
ተምሳሌት ተደርጎ ቸርልችል ጎዳና ጫፍ ላይ ከአራዳ ሕንፃ ግርጌ ትልቅ ቢል ቦርድ እና በብዙ ሺ የሚቆጠሩ ፖስተሮችን እንዲታተሙ
ተደርጎ ነበር፡፡ በማግስቱ ቢል ቦርዱ ወደቀ ተብሎ ተነሳና ምን ተፈጠረ ሲባል ሟቹ ጠቅላይ ሚኒስትር “የምን እዩኝ እዩኝ ነው” ብለው
እንዲነሳ ትዕዛዝ እንደሰጡ ሰማን፡፡ በይፋ የተሰጠ ትዕዛዝ ስለአልነበረ በሚያስደንቅ ፍጥነት ፖስተሩን እንዳይሰበሰብ አድርገን በማስራጨት
አቶ አርከበን ኤች.አይ.ቪ/ኤድስን አስመልክቶ የሚያደርጉትን የመሪነት ሚና በመላው ሀገሪቱ እንዲስራጭ ተደረገ፡፡ ሟቹ ቢወዱትም
ባይወዱትም ጥሩ ውጤት አመጣና ውሎ አድሮ እራሳቸው ተመርምረው “እዩልኝ ስሙልኝ” ለማለት አበቃቸው፡፡ አንዱን አንገት አስደፍቶ
እራሰን ቀና ቀና ማድግ ተገቢ ባለመሆኑ ላይ ሁላችንም መግባባት ያለብን ጉዳይ ይመስለኛል፡፡
ከላይ እንደመግቢያ ያነሳሁትን ሃሳብ ያነሳሁት በኢህአዴግ ፖለቲካ ውስጥ በጎ ምግባር ያላቸው እና የተግባቦት ችግር የሌለባቸው ሰዎች
እንዳሉ እሙን ነው፡፡ እነዚህን ሰዎች አንሰቶ በበጎ ምግባራቸው ተገቢውን ቦታ መስጠት አስፈላጊ እንደሆነ ከልቤ አምናለሁ፣ ለነዚህም
ሰዎች በበጎ ሰራቸው እንዲቀጥሉበት ስንቅ ሊሆናቸው እነደሚችል ምንም ጥርጥር የለኝም፡፡ አሰፈሪው ነገር ግን ኢህአዴግ በባሕሪው
እንደዚህ ዓይነት ሰዎችን እንዴት አድርጎ ነው የሚመዝናቸው የሚለው ነው፡፡ እነኚህ ሰዎች ከእኛ ከሚያገኙት ክብርና ሞገስ በተፃራሪ
በቁጥጥር ስር ያዋላቸው ፓርቲ እንዳይሞቱ እንዳይድኑ አድርጎ ማኮላሸት ይችልበታል፡፡ ለእነደዚህ ዓይነት ተግባር የሟቹ ጠቅላይ
ሚኒስትሩ ሚና ከፍተኛ እንደ ነበር በተግባር የተረጋገጠ ነው፡፡ እንግዲህ ይህ ተግባር መቀጠል አለበት የሚል እምነት የለኝም፡፡ ባለ ራዕዩ
መሪ ካስቀመጡልን መጥፎ ተግባራት አንዱ ነው እና ላለማስቀጠል መግባባት ይኖርብናል፡፡
ግርማ ሰይፉ ማሩ
ምክንያቱ በውል ባይታወቅም/የተለያዩ መላ ምቶች አሉ/ ከአቶ መለስ ዜናዊ ሞት በኋላ በኢህአዴግቾ መንደር መነቃቃት የታየባቸው
የኢህአዴግ ሰዎች እንዳሉ ሁላችንም የምንታዘበው መሬት የወረደ ሀቅ ነው፡፡ እነዚህ ሰዎች አንገታቸውን ቀና እንዳያደርጉ ሟቹ ጥላቸውን
አጥልተው ነበር፡፡ አለበለዚያም የሆነ ፍላፃ ይዘው ከጀርባቸው ነበሩ ማለት ይቻላል፡፡ አሁንም ቢሆን እነዚህን ሰዎች በስም እያነሱ ማወደስ
በተግባራቸው እንዲገፉበት ማበረታት በተገባ ነበር፡፡ ከኛ በኩል ውዳሴ ካገኙ በዚያ በኩል መጥረቢያ የሚሳልላቸው ከሆነ ከጥቅሙ ጉዳቱ
ስለሚያመዝን ለጊዜው ስማቸውን አለማንሳት ተገቢ ይመስለኛል፡፡ እነሱም ይህን ይረዱታል፡፡ በእኔ እምነት አቶ ኃይለማሪያም ደሰለኝ
ማስቀጠል ከሌለባቸው ተግባሮች አንዱ በእንዲህ ዓይነት ሰዎች ላይ የሚመሩት ፓርቲ መጥረቢያ መሳሉን እንዲያቆም ማድረግ
ይመስለኛል፡፡ ለእርሳቸውም ለሌሎች ተተኪ መሪዎችም ከህዝብ በጅምላ ለፓርቲ ከሚሰጥ ድጋፍ በተጨማሪ ለግለሰቦች በአስተዋፅኦ
ደረጃቸው የሚመሰገኑበትና የሚጠየቁበት ስርዓት ፓርቲውንም ቢሆን ይጠቅመዋ እንጂ አይጎዳውም፡፡ ቀና የሚሉትን እየተከተሉ አንገት
ማስደፋት መቆም ይኖርበታል፡፡ ተግባባን!!
ኢሕአዴግ ማሸማቀቅ የሚፈልገው ግለሰቦችን ብቻ ሳይሆን የፈለገ ቀን የተወሰኑ የህብረተሰብ ክፍል ብሎ በጅምላ ህዝቡን ሊሆን ይችላል፡፡
እንደምታስታውሱት በቅርቡ በተደረገው የፕሬዝደንት ለውጥ ኢህአዴግ የህዝብን አስተያየት ለመስማት ደንታ አልነበረውም፡፡ ይልቁንም
ለማሳሳት ተግቶ የሰራ ይመስለኛል፡፡ ፓርቲው ለዕጩነት ያሰባቸውን ጥቂት ሰዎች መደበኛ ባልሆነ መልኩ ይፋ አድርጎ የህዝብን ይሁንታ
ቢያዳምጥ ምንም አይጎዳውም ነበር፡፡ መግባባትን ከመፍጠር ውጭ፡፡ ህዝቡን አይደለም ለጥቅምም ይሁን ለመስዋዕትነት የተሰለፉ
አባላቶቹን ባይተዋር አድርጎ ስራውን አጠናቀቀ፡፡ ይህ ብቻ አይደለም ኢህአዴግ ሲፈልግ ቡና ነጋዴዎችን፣ ከፈለገ የፋይናንስ ሴክተሩን፣
ባሻው ቀን የሪል እስቴት ሴክተር፣ ከፈለገ በአከራይ ተከራይ፣ ወዘተ ነጥሎ ይመታል፡፡ ዓላማውም አንገት ማስደፋት ነው፡፡
በዚህ በኩል በተቃዋሚ ጎራም ቢሆን የጠራ አቋም አለ ብዬ አላምንም፡፡ ምስጋና ለሚገባው ምስጋና ከመስጠት ይልቅ እየገፉ ከክፋተኞቹ
ጎራ ለመቀላቀል ጥረት የሚደረግ ይመስለኛል፡፡ ለዚህ የሚቀርበው አመክንዬም ኢህአዴግን እንደ ስርዓት ነው መቃወም የሚል ነው፡፡
ይህን ስናደርግ ደግሞ ሁሉንም የፓርቲ አባላት በተለይም ከፍተኛ ሹሞች የሚያደርጉትን መቃወም ነው ብሎ የሚያምነው ቁጥር ቀላል
አይደለም፡፡ ይህ አስተሳሰብ ከመቀራረብ ይልቅ መራራቅን፣ ከመተማመን ይልቅ ጥርጣሬን፣ በማስፋት ሀገራችን ለምንላት ኢትዮጵያ እና
ለህዝቡ አለን የምንለውን ራዕይ ማሳካት እንዳንችል እርስ በእርስ ተጠላልፈን እንድንቀር እያደረገ ነው፡፡ በእኔ እምነት ለብዙ የኢህአዴግ
አባላት በሚፈፅሙት በጎ ምግባር የሚገባቸውን በቸርነት ለማድረግ ዝግጁ መሆን ይጠበቅብናል ከታቀፉበት ፓርቲ ሊወርድባቸው
የሚችለውን ፍላፃ ከግምት ውስጥ በማስገባት ጭምር፡፡ የእኛን ሰፈር ፍላፃ ለመቋቋምም ቢሆን ጥንካሬ ይጠይቃል፡፡ እባካችሁ በፓርቲ
ደረጃ ያሉን ልዩነቶች እንደተጠበቁ ሆነው ግለሰቦች በተናጥል ለሚያደርጉት በጎነት እውቅና ለመስጠት ብንግባባ አንዱን የልዩነት ግንብ
አፈረስን ማለት ነው፡፡ ከዚያም ለመቀራረብ መንገድ እንጀምራለን፡፡ የዛሬ ሁሁታዬ ይህው ነው፡፡
ቸር እንሰንብት!!
ኢትዮሚድያ - Ethiomedia.com
December 1, 2013
Sunday, December 1, 2013
የማለዳ ወግ ...የጅዳ ሸረፍያ እስከ ሽሜሲ የተሰማው የወገን ዋይታና እዚህ ያደረሰን መንገድ ! (ነቢዩ ሲራክ)
ፈታኙን ወቅት ለማለፍ ...
የሳውዲ የምህረት Aዋጅ Aልቆ በሪያድ መንፉሃ ላይ Aለምን ያሳዘነ ሰቆቃ ተፈጸመ
...ስጋት ነግሶ ፣ ኑሮ ከብዶን ጨንቆን ጠቦን ከርመናል ! በዚህ ክፉ ቀን ወገን ወገኑን
ለመርዳት ደፋ ቀና በማለቱ ረገድ የሃገሬ ልጅ ከጫፍ Eስከ ጫፍ በቁጭት ስሜት
ሲንቀሳቀስ የፖለቲካው ትኩሳት ወላፈን Eያጓተተን Aልሰነበትንም Aይባልም። ግልጥልጥ
Aድርግን Eናውራ ካልን የኑሮ ውድነት Eና ድህነቱ Eየደቆሰን ቢያስቸግረን ከወገን
ቤተሰቦቻችን ተለይተን ፣ የEማማ Iትዮጵያውያን ምድር ለቀን በስደት ስንባዝን
በደረሰብን የከፋ Aደጋ ለመቋቋም ከምናደርገው ትግል ባልተናነሰ ልዩነትን የሚያገዝፉ
መሰናክሎችን ማለፉ የከበደ Aበሳ ሆኖብን ሰነባብቷል!
በዚህ ፈታኝ ወቅት መፈተን ግድ ሆነና የዜጎች Eንግልት ከሪያድ Aልፎ ወደ ጅዳና
Aካባቢው ሲሸጋገር በርካታ ወገኖች በግልና በቡድን በመሰባሰብ በጎ Eርዳታ ለማድረግ
መንቀሳቀስ ጀመሩ። ቀጠሉና ወገኖችን ለመርዳት ብቸኛው Aደራጅ ለሆኑ የIትዮጵያ
መንግስት Iንባሲና ቆንስ ነመ/ቤቶች " ለወገኖቻችን Eንድረስ !" በሚል ያቀረቡት ጥያቄ
ምላሽ Aገኘ። የጅዳ ቆንስል በማህበራትና በIህAዴግ ድርጅቶችን "በነጻ የበጎ Eርዳታ
ድጋፍ Eናቅርብ " ባይ ዜጎች ጋር ጥምር Aስቸኳይ ስብሰባ በመጥራት በAይነቱ ነጻ
የተባለውን "ወገን ለወገን ደራሽ " የተባለውን ኮሚቴ Aቋቋመ። ኮሚቴው የEርዳታ Eና
ድጋፍ ሰጭ፣ የመረጋጋትና የህዝብ ግንኙነት ንUስ ኮሚቴን Aቋቋመ።
የጅዳ ሸረፍያው ሁከት...
በኮሚቴው መዋቀር መባቻ በጅዳ ሸረፍያ በተባለው Aንድ ሰፈር "ወደ ሃገር Eንግባ !"
ብለው ድልድይ ስር ከተቀመጡ Iትዮጵያውያን መካከል Aንዲት Aራስ Eህት "ልጇን
ሜዳ ላይ ጥላ ሔደች !" ተባለና ህጻን ወድቆ ተገኘች፣ ያንኑ ቀን ከቀትር በኋላ ሌላ Aሳዛኝ
ክስተት በድልድይ ተከሰተ። ከድልድዩ የቅርብ ርቀት Aንድ ወንድም በድንገት በመኪና
Aደጋ ሞተ! የቀን ጸሃይ ፣ የማታው ወበቅ ያደከመውን ወገን Aስቆጣው። ሸረፍያ
ታመሰች! ጸጥታ Aስከባሪዎች ጸጥታ ለማስከበር Aካባቢውን ከበቡት ፣ ፍጥጫ ነገሰ!
በሁኔታውን ግራ የተጋቡት ፖሊሶች ጥይት ወደ ሰማይ በመተኮስ ሁከቱን ለማረጋጋት
ሞክረው ባይሳካላቸውም ከጅዳ ቆንስል የተላኩ የድርጅት Aባላት ሁከቱን ለማረጋጋት
ቻሉ!
በተፈጠረው ግርግር የተደናገጡት በድልድዩ ሁለት ሳምንታትን በመከራ የገፉ ወገኖች
"ለደህንነታችን ሰጋን! " ሲሉ በዚያው ምሽት ወደ ጅዳ ቆንስል ተመው በመምጣት
በቆንስሉ Aካባቢ ባለው ሜዳ በAሳዛኝ ሁኔታ ከተሙ። የወዳደቀ Eንጨት ፣ፕላስቲክና
Eንጨት Eየለቃቀሙ ጎጆ ሰሩ ! በከፋ ቀን ያልታሰበው ያልተገመተው ሁሉ ይሆናልና ፣
ያላሰብነው ሆነ ! ውሎ ሲያድር የሰው ቁጥር Eየበዛ የጅዳ ቆንስል በከፋቸው ዜጎች
ተጥለቀለቀ ... Aስደሳቹ የወገን ርብርብ ...
ይህን ጊዜ ነበር ሰው ለሰው ልብሱ መሆኑን የታዘብኩት ። የከፋቸውን ለማጽናናት ፣
የጠማ የደረቀውን ጉሮሮ ለማርጠብ፣ በርሃብ የታጠፈውን Aንጀት ምግብ በማቅረብ
በመታደግ ፣ በተለይም ህጻናትን ለመደገፍ የተደረገው ርብርብ ፍጹም ልዩነታችን ያስረሳ
ልዩ የታሪክ Aጋጣሚ ነበር ። ... ፍጹም ከህሊናየ የማይጠፋ ህብረት !
የወገኖች የሜዳ ቆይታ ከሳምንት Eንዳያልፍ የተደረገው ጥረት የሚያስደስት ሲሆን
ይህንን ለማደረግ "የዜጎቸ ስቃይ Aኔንም ያገባኛል! " በሚል ቀድሞ Eስከ Aስር ሽህ
የሳውዲ ሪያል በማዋጣት ከመጀመሪያው ቀን Aንስቶ Eስከ መጨረሻዎቹ ቀናት የሰሜንና
ደቡብ " ዋይት " ማህበር Aባላት ምግብ Eና ውሃ በማቅረብ ያሳዩት ትጋት ከEድሜ ጠገብ
ወንድሞች ያልጠበቅኩት ነበር ። ይህ ማህበር በተቋቋመው ኮሚቴ ውስጥ በEርዳታ Aልፎ
በማረጋጋቱ ኮሚቴ በመታቀፍ ያሳየው ፋና ወጊ Eንቅስቃሴ ወደር Aልነበረውም! የጅዳ
ኮሚኒቲ ፣ የIህAዴግ የድርጅት ፣ ለAደጋው የተቋቋመው ኮሚኒቴ ፣ የOሮሞ ልማት ፣
የጂዳ ቆንስል ሰራተኞች ፣የሳውዲው ትውልድ Iትዮጵያዊው የመርባይ ቤተሰቦች ፣
ስማቸው Eንዳይጠቀስ የፈለጉ ግለሰቦች Eና በግል ከጎናችን የተሰለፉ ነዋሪዎች ውሃ ምግብ
በተወሰነ ደረጃ ከማቅረብ ጀምሮ ሻንጣ በማጓጓዝ Eና ዜጎችን በማመላለስ ማስተናገዱ
ረገድ በህብረት የሰሩትን በጎ ምግባር ሳስበው ኩራት ይሰማኝል! ይህ ለበጎ ምግባር
የተደረገ ትብብር የባጀንበትን የከረረ ልዩነት ከAEምሯችን ሲያጠፋው በህብረት ለAንድ
Aፍታም ቢሆን የከፋውን ህይዎት ጠግኖት ማየት መቻል ስለ Eውነት ያኮራል !
የሽሜሲው መጠለያ ቆይታና የግፉAኑ ምሬት ...
በዚህ መንገድ በቆንስላው ለቀናት የቆዩት ወገኖች መካ መግቢያ የቅርብ ርቀት ወደ
ሚገኘው የሽሜሲ መጠለያ Eስር ቤት ተላኩ ። "ወገኖቻችን ወደ ማጠለያ ገብተው ወደ
ሃገራቸው በሰላም ሊመለሱ ነው !" ብለን ደስታችን ወሰን ባጣበት Aጋጣሚ ግን ወደ
መጠለያው የተወሰዱ ወገኖች ከመጠለያው ሳይገቡ ከግቢው ውጭ ፈሰው ለሶስትና Aራት
ቀናት Eንግልት Eንደ ደረሰባቸው ተሰማ ! ተከፋን ! Eኔም Eንደለመድኩት በሰላም
የሸኘናቸውን ወገኖች ሮሮ መስማት ጀመርኩ ! በቀጣይ ቀናት በግልና ከኮሚቴው ጋር
በመቀናጀት የውሃ ፣ የምግብና የመጸዳጃ ጥያቄውን ለሚመለከታቸው ለማቅረብ ያደረግነው
ሙከራ ሳይሳካ ቀረ። በEርዳታና ድጋፍ ሰጭው ኮሚቴ በኩል የውሃ Aቅርቦቱን ለማድረግ
በተደረገው ሙከራ በAርባ Aውቶቡስ የሞላውን ወደ ሶስት ሽህ የሚሆነውን ሁሉንም
ማስተናገድ Aቅም Aጣን ! የሚቻለውን ግነወ Aደረፍን። Eለተ ሃሙስ ከሽሜሲ መጠለያ
በር ሜዳ ይ የተጣሉት ወገኖች ሮሮ በማየሉ ማታውኑ የEርዳታ Aስተባባሪዎች ባደረጉት
ጥረት የሰሜንና ደቡብ "ዋይት" ማህበር Aባላት ለAርብ ጠዋት የምግብ Eና ውሃ Eንዲ
ያቀርቡ ተጠይቆ በማህበሩ ይሁንታን Aግኝቶ Aርብ ጠዋት Aቅርቦቱን ለመከወን ቀጠሮ
ተያዘ !
የሽሜሲው ሁከት ...
Eንዲህ Eንደሆነ ሃሙስ በAርብ ተተካ ! Aርብ ጎህ Eንደ ቀደደ በተንቀሳቃሽ ስልኬ
በውሃ ጥማት Eና በርሃብ የታመሱት ወገኖች በተለይም ህጻናትን የያዙ Eናቶች Eንባ
የተቀላቀለበትን የምሬት ጩኸት Eያመመኝ መስማት ጀመርኩ ... በደረሰባቸው ሰቃይ Aምርረው "ወደ ጅዳ Eንመለስ ፣ ሱቅ Eንኳ ከሌለበት ቦታ ከምንሰቃይ ሰው ሊያየን
ወደሚችል ቦታ Eንሄዳለን! " ያሉኝን መልEክት ለማሰማትና መፍትሔ ለማፈላለግ
ብሞክርም ሙከራየ የተሳካ Aልነበረም ። Eናም Eኩለ ቀን ላይ ምሬት ፈንቅሏቸው ወደ
መካና ጅዳ Aውራ ጎዳና መውጣት ሲሞክሩ ከጸጥታ Aስከባሪዎች ጋር መጋጨታቸውን
ተረዳሁ! የሁከት ብጥብጡን ጅማሬ ሂደት በቀጥታ በስልክ መረጃውን ከሚያቀብሉን
ግፉAን ወገኖች ድመጽ Aልፎ የሚሰማው የተኩስና የሁከት ጫጫታ ድምጽ Eየሆነ ያለውን
ያሳይ ነበር ... ይህ በEንዲህ Eንዳለ የሰሜንና ደቡብ "ዋይት" ማህበር Aባላት ለAርብ
ጠዋት የምግብ Eና ውሃ Aዘጋጅተው ወደ ሽሜሲ ሊንቀሳቀሱ ሲሉ የሁከቱን መረጃ
ደረሳቸው! የተዘጋጀው ምግብ ማቅረብ ሳይቻል ቀረ!
ከሰAታት በኋላ የጅዳ ቆንስል ሃላፊዎች Eና የሳውዲ መንግስት ከፍተኛ ሃላፊዎች
ችግሩ Eስኪከሰት ዘግይተውም ቢሆን ባደረጉት ድርድር ሁከቱ በርዶ ለሶስት ሰAታት
ተዘግቶ የነበረው የጅዳ መካ Aውራ መንገድ ተከፈተ ... የተዘጋጀው ምግብ ማቅረብ
ያልቻሉት ወንድሞች ምግብ ውሃውን በሽሜሲ ላሉት ወገኖች መድረስ ባይችሉም በመካ
ኩደይ በተባለ Aካባቢ በተመሳሳይ መንገድ "ወደ ሃገር Eንግባ! " በሚል Aደባባይ ለወጡት
ወገኖች ምግብና ውሃውን በAፋጣኝ መንገድ Aቀረቡ ፣ Aሁንም ካለው የህዝብ ብዛት
Aንጻር ምግቡና ውሃው ለሁሉም ባይዳረስ Eንደሚሆን Eንደሚሆን Aድረገው Eርዳታውን
Aከፋፈሉ ! ወገን ለወገን ደራሽ መሆኑን ለማየት ፣ ለመስማት ብሎም የመከራው ቀን በጎ
ስራ Eማኞች ለመሆንን ታደልን !
ይቅርታው ...
Aርብ ምሽት - የወገን ለወገን ደራሽ ኮሚቴ መደበኛ ስብሰባ Aድርገን Aንዱን
Aንስተን Aንዱን ስንጥል Aመሸን ። Eኩለ ሌሊት ስብሰባው ሲከወን የኮሚቴውን Aካሔድ
ለማስተካከል የተወሰደው ውሳኔ ተላለፈ፣ ከጎናችን ሆነው ደፋ ቀና የሚሉትን ወገኖች
Aስከፋ : ( ውሳኔው መተግበር ቢኖርበትም ከውሳኔው በፊት መስራት ያለብንን ስራ
ባለመስራታችን ወንደሞቻችን Aስቀይመናል! የሚሰራ ይሳሳታል ፣ ስንሰራ ተሳስተናል!
ይቅርታችን የከበደ ነው ! የAካሔድ ጠፋቱ Aካል ነበርኩና ያች ምሽት ለEኔ ከባድ ነበረች
... የከበደኝ መሆን ያለበት ወገንን ለመታደግ የሚደረገውን ሂደት ለማስተካከል
የተደረሰበት ውሳኔው ሳይሆን ቡና Eየጨለጡ የሚፈላሰፉ በበዙበት ከባቢ ደጋግ በጎ
Aድራጊ ወንድሞቻችን በማስከፋታችን ነበር! በዚሁ ስብሰባ "ገጽታችን Eንገንባ! "
የምትለው የAንዳንድ ወገኖች Aካሔድ Aንድምታ ግራ ሲያጋባኝ Aለም Aቀፉን ህብረት
Eየነቀነቀ ያለውን የወገን ለወገን የመድረስ Aላማ ወደ ሌላ Aቅጣጫ የሚጎትት ምሽት ላይ
በስልክ ካደረግኩት የራዲዮ ውይይት ጋር በAንድና በሌላ Aቅጣጫ ሲሳሳብ ከፊቴ ተደቀነ!
ስብሰባው Eኩለ ሌሊት ተጠናቀቀ! ... ወደ ቤት ገብቸ Eንዲህ ስል የተጎዳ ስሜቴን
Eንዳሻኝ ስሜት ህመም ፣ ተስፋ ህልም ስጋቴነወ Eንዳሻኝ በምገልጽባት የፊስ ቡክ ገጼ
ተነፈስኩት ...ተቃዋሚው ባንድ ወገን መንግስትና ደጋፊው በሌላ ወገን ይሳሳባሉ ፣ ሁለት
ዝሆኖች ይታገላሉ ፣ ድሃ መውጫው ቀዳዳ ጠቦታል ፣ ወገኔ ከዝሆኖች ጥል ስር የበቀለ
ያልታደለ ሳር ሆኖ ይደቆሳል ፣ የባሰውኑ ታምሜ Aመሸሁ ! Aይመሽ የለም መሽቶ
ከተማሩ ከተመራመሩ ፣ ከወለዱ ከከበዱት ወንድሞቸ ጋር ወገኔን መረጃ ከማቀበል
በተግባር ወደ መርዳት ልሸጋገር ስብሰባ ተቀመጥኩ ! ትልልቆቹ Aንሰን ቢታየኝ ህምም
ታምሜ Eኩለ ሌሊት ወደ ቤት ገባሁ ! ያየሁ የሰማሁ የሆነውን ለመርሳት Eየሞከርኩ
Aይተኛ የለም ተመስገን ብየ ተኛሁ ! ዛሬ Eንጃ ! የማውቀው የትናንቱን ክፉ ቀን ነው ! በተስፋ የተጀመረው ቀንና የምስራቹ ...
Eለተ ሰንበት ቅዳሜ - በልጀ የማለዳ ሳቅ ታጅቤ በተስፋ ተነሳሁ ... Eንዲህም Aልኩ
...ዛሬ Eንጃ ! የማውቀው የትናንቱን ክፉ ቀን ነው ! ልጀ ሆይ! መውለድ ደጉ ዛሬን ባንች
ፈገግታ በተስፋ ሊጀመር ነው ! ተመስገን ! ተመስገን ! ተመስገን ! መልካም ቀን
ለሁላችሁ!
የEኔን የሃጥUን ጸሎት ሳይሆን ልጆቻቸውን ታቅፈው ጨንቋቸው ፣ ጮኸው ሰሚ
ያጡትን ወገኖች ሃያሉ Aምላክ Aልተዋቸውም! EግዚAብሔር Aምላክ በስደት የተሰበረውን
የወገኖቻችን ጉዳት ሰማ ! የጨነቃቸው የጠበባቸው በደስታ ፊስታ ተናኙ ! በጭንቀት
ሁከት የሰነበቱት ወገኖች ወደ ሃገር ቤት ለመሄድ ዝግጅት መጠናቀቅ መረጃ የደረሰኝ
በተስፋ የጀመርኩትን ቀን የሚያበላሽ ቧልት ሰምሁና Aዘንኩ ። ሞራል ያጡ ፣ በወገን
ችግር ጀርባ በቪዛ ሽያጭ ፣ በድለላ Eና በመሳሰሉት ጥቅምን በማጋበስ የለመዱ ክፉዎች
በዚህ ክፉ ቀን Eንኳ ስለሚንገላታው ወገን Aይጨነቁም! ለጆቻቸውን ስለሚያስተምሩበት
ትምህርት ቤት Eያደር መበለሻሸት ግዳቸው Aይደለም! Eናም ተበሳጭቸ ከጅዳ ኮሚኒቲ
ካፍቴርያ Eንደወጣሁ ስልክ ተደውሎ የምስራች መልEክት ደረሰኝ!
" ነቢዩ ደስ ብሎናል ! Eንኳን ደስ ያለህ ! ትናንት Eየደወልን ስጨናንቅህ የነበርነው
ሁላችንም ወረቀታችን Aልቆልን ወደ ጅዳ Aየር መንገድ Eየተጓዝን ነው! " ተመሳሳይ
የስልክ ጥሪ ደረሶኝ ተመሳሳይ የምስራች ሰማሁ! ዛሬ ለቅሶ የለም! Eኒያ ሲንገላቱ የሰነበቱ
ወገኖች ሳቅ በሳቅ ሆነው ፣ በደስታ ተውጠው የምስራቹን ሲያበስሩኝ የተሰማኝ ደስታ ወሰን
የለውም ! Aዎ ወደ Aራት ሽህ የሚገመቱት ወገኖች የሃገራቸውን መሬት ለመርገጥ
መታደላቸው በEርግጥም ታላቅ የምስራች ነው ! ተመስገን !
ከሽሜሲው ግጭት የምንማረው ...
ከሽሜሲው ግጭት ብዙ ልንማር ይገባል ። በጅዳ ቆንስል የቅርብ ርቀት ከትመው
ለሳምንት ከቆዩ በኋላ ወደ ሺሜሲ መጠለያ በወገን ትብብር የተወሰዱት ወገኖች
በመጠለያው ግቢ Eንዳይገቡ ተደርገው ነበር። በጠራራው ጸሃይ በAውቶቡስ Eና በሜዳ
ላይ ያለ ምግብና ወሃ መሰንበታቸውን የጅዳ ቆንስል ሰራተኞችና ሃላፊዎች ወደ መጠለያው
ሲገቡና ሲዎጡ ይመለከቷቸው ነበር ። ያም ሆኖ ከሶስትና ከAራት ቀናት በላይ ህጻናትን
የያዙተን ጨምሮ Aቅመ ደካማ Eህቶች በወሃ ጥማት ሲጠበሱና በርሃብ Aንጀታቸው
ሲታጠፍ ከቅርብ ርቀት ያሉት የቆንስል መስሪያ ቤቱ ሰራተኞችና ሃላፊዎች መፍትሄ
Aላፈላለጉላቸውም። በዚህ መሰል Aስከፊ ሁኔታ ህጻናት ደክመው ፣ ነፍሰ ጡር Eህቶች
ደክመው ፣ የተወሰኑት AEምሯቸው ተነክቶ ታዝበናል። የሁከቱ መንስኤ ለቀናት በርሃብና
በውሃ ጥማት የተቸገሩት ግፉAኑ ወገኖች ትEግስት ማጣት Eንጀ ሁከትን ለማስነሳት ታቅዶ
የተፈጸመ Eንዳለሆነ ግልጽ መሆን Aለበት!
" ወደ መጠለያ Aስገባሁ !" ብሎ በመጠለያው በር ሜዳ ላይ ያፈሰሳቸውን የሳውዲ
መንግስት Aካል ከመሞገት ባለፈ ይህን መሰል Aስነዋሪ ስራ Eንዳይሰራ የጅዳ ቆንስል
ሃላፊዎች መስራት የነበረባቸውን ስራ በበቂ ሁኔታ ሰርተዋል Aልልም። የጅዳ ቆንሰል
ሃላፊዎች ወደ መጠለያው የተላኩ ዜጎቹን ጉዳይ በEግር በEግር ተከታትለው ማስፈጸም
ነበረባቸው። ይህ Aልተደረገም ወይም ተደርጎ Aልተሳካም ይሆናል። በAንድ Aቅጣጫ
ያልተሳካውን በሌላ Aቅጣጫ ለማስፈጸም የቆንስሉ ሃላፊዎች ያደረጉት ሙከራ Aንድ ሁለት ቀን ቢከሽፍ ከAራት ቀን በላይ መጓተቱ ዲፕሎማቶቻችን ከፍተኛ ጫናን ፈጥረው
ጉዳዩን በማስፈጸሙ ረገድ Eንዳልተሳካላቸው በግልጽ ያሳያል። የሳውዲ መንግስት Eና
የጅዳ ቆንስል ሃላፊዎች በፈጻሚና Aስፈጻሚ Aለካት መካከል መግባባት ቢኖር ኖሮ ዜጎችን
ወደ መጠለያው Eንኳ ማስገባት ቢገድ ካሉበት ቦታ ምግብና ውሃ በማቀበል Aጠቃላይ
ሂደቱን መቆጣጠር ይቻል ነበር። በሂደቱን የጅዳ ቆንስል ሃላፊዎች በቅርብ ተከታትለውት
ቢሆን ኖሮ Aነወዱ Aንኳ ቢያስቸግር የጉዳዩን Aሳሳቢነት ለማስረዳት ከከፍተኛ የሳውዲ
መንግስት ሃላፊዎች መድረስ ይችሉ ነበር። ከዚህ በተጓዳኝ ለመገናኛ ብዙሃን በAሰራር
የሚገጥማቸውን መሰናክል በማቅረብ ድምጻቸውን ሊያሰሙ ይገባ ነበር ። ይህ Aልሆነምና
ትኩረት ባለመሰጠቱ ሰው ተራበ ተጠማ ሁኔታዎች ከቁጥጥር ውጭ ሆኑ ! ወደ ዝርዝር
ሳንገባ ካለፈው ጥፋት ልንማር ግድ ይለናል! ካለፈው ስህተት ከተማርን ከተመሳሳይ ሁከት
ልንድን Eንችላለን !
የማይበጀን ሁከት ፣ የማይፈይድልን መረጃ ....
ይህን መሰል ችግር መቅረፍ የሚቻለው ሁላችንም ያገባናል ብለን በህብረት ስንደጋገፍ
ብቻ ነው! ሰላማዊ ሰልፍ Aና የAደባባይ ላይ ተቃውሞ በማይፈቀድ በማይታሰብባት
ሳውዲ Aረቢያ ችግር Eንኳ ቢሆር የሚፈታባቸውን መንገዶች ከማፈላለግ ባለፈ ሁከት
Aመጽን መከተል Aይጠቅመንም። ወደ ሁከት የሚወስደውን ሁሉ Eንቅስቃሴ በማስዎገድ
Eና መረጃን በመለዋወጥ ችግሮች Eንዲሰሙ ማድረግና ማስተካከል ይቻል ይመስለኛል!
በነጻነት መረጃን ከተለዋወጥን የማይቻል የለም ይቻላል! ነዋሪውን ለማረጋጋረት ብሎ
ያልሆነውን ሆነ ብለን "የዋሽቶ ማስታረቅ! " ዘይቤ ፍጹም Aይበጀንም! ገጽታን Eናሳምር
ምናምን ብለን "ቅባቱን " ተጠቅመን መረጃውን Eና Eውነቱን ካዛባነው መረጃው ዘባተሎ
ይሆናል ፣ ከዚሁ ጋር ችግሩን ለመታደግ የምንወጣ የምንወርደው ሁሉ የተዛባው ባለቅባት
መረጃ ተAማኒነትን ያሳጣናልና ድካሙን ሁሉ የEንቧይ ካብ ያደርገዋልና ጥንቃቄ
ማድረግ ይገባል : )
የስኬቱ ባለድርሻዎች ...
በመላ ሳውዲ ችግሩ በEኛ ላይ ከጠና ወዲህ ወገኖቻችን ወደ ሃገራቸው Eንዲገቡ
የሚደረገው ስኬት በተወሰኑ ግለሰቦች ወይም ቡድኖች የተከወነ Aይደለም ። በሃገር ቤት
በውጭ ሃገር ያሉ ወገኖች በሳውዲ መንግስት ላይ ያሳደሩት ተጽEኖ ፣ በሳውዲ Aረቢያ
የተለያዩ ከተሞች የምንገኝ ሁላችንም በህብረት የሰራነው ስራ ውጤት ነውና ደስ ሊለን
ይገባል! ምስጋናውም ለሁሉም ነው ! ወገንን መደገፍ ምስጋና ካስፈለገው ማለቴ ነው ...
ደስ ሲል ...!
ለወገን ደራሹ ወገን ነው ፣ በህብረቱ ፣ Eንበርታ !
ነቢዩ ሲራክ
ምንጭ የኢትዮጵያ ሜዲያ መድረክ
የሳውዲ የምህረት Aዋጅ Aልቆ በሪያድ መንፉሃ ላይ Aለምን ያሳዘነ ሰቆቃ ተፈጸመ
...ስጋት ነግሶ ፣ ኑሮ ከብዶን ጨንቆን ጠቦን ከርመናል ! በዚህ ክፉ ቀን ወገን ወገኑን
ለመርዳት ደፋ ቀና በማለቱ ረገድ የሃገሬ ልጅ ከጫፍ Eስከ ጫፍ በቁጭት ስሜት
ሲንቀሳቀስ የፖለቲካው ትኩሳት ወላፈን Eያጓተተን Aልሰነበትንም Aይባልም። ግልጥልጥ
Aድርግን Eናውራ ካልን የኑሮ ውድነት Eና ድህነቱ Eየደቆሰን ቢያስቸግረን ከወገን
ቤተሰቦቻችን ተለይተን ፣ የEማማ Iትዮጵያውያን ምድር ለቀን በስደት ስንባዝን
በደረሰብን የከፋ Aደጋ ለመቋቋም ከምናደርገው ትግል ባልተናነሰ ልዩነትን የሚያገዝፉ
መሰናክሎችን ማለፉ የከበደ Aበሳ ሆኖብን ሰነባብቷል!
በዚህ ፈታኝ ወቅት መፈተን ግድ ሆነና የዜጎች Eንግልት ከሪያድ Aልፎ ወደ ጅዳና
Aካባቢው ሲሸጋገር በርካታ ወገኖች በግልና በቡድን በመሰባሰብ በጎ Eርዳታ ለማድረግ
መንቀሳቀስ ጀመሩ። ቀጠሉና ወገኖችን ለመርዳት ብቸኛው Aደራጅ ለሆኑ የIትዮጵያ
መንግስት Iንባሲና ቆንስ ነመ/ቤቶች " ለወገኖቻችን Eንድረስ !" በሚል ያቀረቡት ጥያቄ
ምላሽ Aገኘ። የጅዳ ቆንስል በማህበራትና በIህAዴግ ድርጅቶችን "በነጻ የበጎ Eርዳታ
ድጋፍ Eናቅርብ " ባይ ዜጎች ጋር ጥምር Aስቸኳይ ስብሰባ በመጥራት በAይነቱ ነጻ
የተባለውን "ወገን ለወገን ደራሽ " የተባለውን ኮሚቴ Aቋቋመ። ኮሚቴው የEርዳታ Eና
ድጋፍ ሰጭ፣ የመረጋጋትና የህዝብ ግንኙነት ንUስ ኮሚቴን Aቋቋመ።
የጅዳ ሸረፍያው ሁከት...
በኮሚቴው መዋቀር መባቻ በጅዳ ሸረፍያ በተባለው Aንድ ሰፈር "ወደ ሃገር Eንግባ !"
ብለው ድልድይ ስር ከተቀመጡ Iትዮጵያውያን መካከል Aንዲት Aራስ Eህት "ልጇን
ሜዳ ላይ ጥላ ሔደች !" ተባለና ህጻን ወድቆ ተገኘች፣ ያንኑ ቀን ከቀትር በኋላ ሌላ Aሳዛኝ
ክስተት በድልድይ ተከሰተ። ከድልድዩ የቅርብ ርቀት Aንድ ወንድም በድንገት በመኪና
Aደጋ ሞተ! የቀን ጸሃይ ፣ የማታው ወበቅ ያደከመውን ወገን Aስቆጣው። ሸረፍያ
ታመሰች! ጸጥታ Aስከባሪዎች ጸጥታ ለማስከበር Aካባቢውን ከበቡት ፣ ፍጥጫ ነገሰ!
በሁኔታውን ግራ የተጋቡት ፖሊሶች ጥይት ወደ ሰማይ በመተኮስ ሁከቱን ለማረጋጋት
ሞክረው ባይሳካላቸውም ከጅዳ ቆንስል የተላኩ የድርጅት Aባላት ሁከቱን ለማረጋጋት
ቻሉ!
በተፈጠረው ግርግር የተደናገጡት በድልድዩ ሁለት ሳምንታትን በመከራ የገፉ ወገኖች
"ለደህንነታችን ሰጋን! " ሲሉ በዚያው ምሽት ወደ ጅዳ ቆንስል ተመው በመምጣት
በቆንስሉ Aካባቢ ባለው ሜዳ በAሳዛኝ ሁኔታ ከተሙ። የወዳደቀ Eንጨት ፣ፕላስቲክና
Eንጨት Eየለቃቀሙ ጎጆ ሰሩ ! በከፋ ቀን ያልታሰበው ያልተገመተው ሁሉ ይሆናልና ፣
ያላሰብነው ሆነ ! ውሎ ሲያድር የሰው ቁጥር Eየበዛ የጅዳ ቆንስል በከፋቸው ዜጎች
ተጥለቀለቀ ... Aስደሳቹ የወገን ርብርብ ...
ይህን ጊዜ ነበር ሰው ለሰው ልብሱ መሆኑን የታዘብኩት ። የከፋቸውን ለማጽናናት ፣
የጠማ የደረቀውን ጉሮሮ ለማርጠብ፣ በርሃብ የታጠፈውን Aንጀት ምግብ በማቅረብ
በመታደግ ፣ በተለይም ህጻናትን ለመደገፍ የተደረገው ርብርብ ፍጹም ልዩነታችን ያስረሳ
ልዩ የታሪክ Aጋጣሚ ነበር ። ... ፍጹም ከህሊናየ የማይጠፋ ህብረት !
የወገኖች የሜዳ ቆይታ ከሳምንት Eንዳያልፍ የተደረገው ጥረት የሚያስደስት ሲሆን
ይህንን ለማደረግ "የዜጎቸ ስቃይ Aኔንም ያገባኛል! " በሚል ቀድሞ Eስከ Aስር ሽህ
የሳውዲ ሪያል በማዋጣት ከመጀመሪያው ቀን Aንስቶ Eስከ መጨረሻዎቹ ቀናት የሰሜንና
ደቡብ " ዋይት " ማህበር Aባላት ምግብ Eና ውሃ በማቅረብ ያሳዩት ትጋት ከEድሜ ጠገብ
ወንድሞች ያልጠበቅኩት ነበር ። ይህ ማህበር በተቋቋመው ኮሚቴ ውስጥ በEርዳታ Aልፎ
በማረጋጋቱ ኮሚቴ በመታቀፍ ያሳየው ፋና ወጊ Eንቅስቃሴ ወደር Aልነበረውም! የጅዳ
ኮሚኒቲ ፣ የIህAዴግ የድርጅት ፣ ለAደጋው የተቋቋመው ኮሚኒቴ ፣ የOሮሞ ልማት ፣
የጂዳ ቆንስል ሰራተኞች ፣የሳውዲው ትውልድ Iትዮጵያዊው የመርባይ ቤተሰቦች ፣
ስማቸው Eንዳይጠቀስ የፈለጉ ግለሰቦች Eና በግል ከጎናችን የተሰለፉ ነዋሪዎች ውሃ ምግብ
በተወሰነ ደረጃ ከማቅረብ ጀምሮ ሻንጣ በማጓጓዝ Eና ዜጎችን በማመላለስ ማስተናገዱ
ረገድ በህብረት የሰሩትን በጎ ምግባር ሳስበው ኩራት ይሰማኝል! ይህ ለበጎ ምግባር
የተደረገ ትብብር የባጀንበትን የከረረ ልዩነት ከAEምሯችን ሲያጠፋው በህብረት ለAንድ
Aፍታም ቢሆን የከፋውን ህይዎት ጠግኖት ማየት መቻል ስለ Eውነት ያኮራል !
የሽሜሲው መጠለያ ቆይታና የግፉAኑ ምሬት ...
በዚህ መንገድ በቆንስላው ለቀናት የቆዩት ወገኖች መካ መግቢያ የቅርብ ርቀት ወደ
ሚገኘው የሽሜሲ መጠለያ Eስር ቤት ተላኩ ። "ወገኖቻችን ወደ ማጠለያ ገብተው ወደ
ሃገራቸው በሰላም ሊመለሱ ነው !" ብለን ደስታችን ወሰን ባጣበት Aጋጣሚ ግን ወደ
መጠለያው የተወሰዱ ወገኖች ከመጠለያው ሳይገቡ ከግቢው ውጭ ፈሰው ለሶስትና Aራት
ቀናት Eንግልት Eንደ ደረሰባቸው ተሰማ ! ተከፋን ! Eኔም Eንደለመድኩት በሰላም
የሸኘናቸውን ወገኖች ሮሮ መስማት ጀመርኩ ! በቀጣይ ቀናት በግልና ከኮሚቴው ጋር
በመቀናጀት የውሃ ፣ የምግብና የመጸዳጃ ጥያቄውን ለሚመለከታቸው ለማቅረብ ያደረግነው
ሙከራ ሳይሳካ ቀረ። በEርዳታና ድጋፍ ሰጭው ኮሚቴ በኩል የውሃ Aቅርቦቱን ለማድረግ
በተደረገው ሙከራ በAርባ Aውቶቡስ የሞላውን ወደ ሶስት ሽህ የሚሆነውን ሁሉንም
ማስተናገድ Aቅም Aጣን ! የሚቻለውን ግነወ Aደረፍን። Eለተ ሃሙስ ከሽሜሲ መጠለያ
በር ሜዳ ይ የተጣሉት ወገኖች ሮሮ በማየሉ ማታውኑ የEርዳታ Aስተባባሪዎች ባደረጉት
ጥረት የሰሜንና ደቡብ "ዋይት" ማህበር Aባላት ለAርብ ጠዋት የምግብ Eና ውሃ Eንዲ
ያቀርቡ ተጠይቆ በማህበሩ ይሁንታን Aግኝቶ Aርብ ጠዋት Aቅርቦቱን ለመከወን ቀጠሮ
ተያዘ !
የሽሜሲው ሁከት ...
Eንዲህ Eንደሆነ ሃሙስ በAርብ ተተካ ! Aርብ ጎህ Eንደ ቀደደ በተንቀሳቃሽ ስልኬ
በውሃ ጥማት Eና በርሃብ የታመሱት ወገኖች በተለይም ህጻናትን የያዙ Eናቶች Eንባ
የተቀላቀለበትን የምሬት ጩኸት Eያመመኝ መስማት ጀመርኩ ... በደረሰባቸው ሰቃይ Aምርረው "ወደ ጅዳ Eንመለስ ፣ ሱቅ Eንኳ ከሌለበት ቦታ ከምንሰቃይ ሰው ሊያየን
ወደሚችል ቦታ Eንሄዳለን! " ያሉኝን መልEክት ለማሰማትና መፍትሔ ለማፈላለግ
ብሞክርም ሙከራየ የተሳካ Aልነበረም ። Eናም Eኩለ ቀን ላይ ምሬት ፈንቅሏቸው ወደ
መካና ጅዳ Aውራ ጎዳና መውጣት ሲሞክሩ ከጸጥታ Aስከባሪዎች ጋር መጋጨታቸውን
ተረዳሁ! የሁከት ብጥብጡን ጅማሬ ሂደት በቀጥታ በስልክ መረጃውን ከሚያቀብሉን
ግፉAን ወገኖች ድመጽ Aልፎ የሚሰማው የተኩስና የሁከት ጫጫታ ድምጽ Eየሆነ ያለውን
ያሳይ ነበር ... ይህ በEንዲህ Eንዳለ የሰሜንና ደቡብ "ዋይት" ማህበር Aባላት ለAርብ
ጠዋት የምግብ Eና ውሃ Aዘጋጅተው ወደ ሽሜሲ ሊንቀሳቀሱ ሲሉ የሁከቱን መረጃ
ደረሳቸው! የተዘጋጀው ምግብ ማቅረብ ሳይቻል ቀረ!
ከሰAታት በኋላ የጅዳ ቆንስል ሃላፊዎች Eና የሳውዲ መንግስት ከፍተኛ ሃላፊዎች
ችግሩ Eስኪከሰት ዘግይተውም ቢሆን ባደረጉት ድርድር ሁከቱ በርዶ ለሶስት ሰAታት
ተዘግቶ የነበረው የጅዳ መካ Aውራ መንገድ ተከፈተ ... የተዘጋጀው ምግብ ማቅረብ
ያልቻሉት ወንድሞች ምግብ ውሃውን በሽሜሲ ላሉት ወገኖች መድረስ ባይችሉም በመካ
ኩደይ በተባለ Aካባቢ በተመሳሳይ መንገድ "ወደ ሃገር Eንግባ! " በሚል Aደባባይ ለወጡት
ወገኖች ምግብና ውሃውን በAፋጣኝ መንገድ Aቀረቡ ፣ Aሁንም ካለው የህዝብ ብዛት
Aንጻር ምግቡና ውሃው ለሁሉም ባይዳረስ Eንደሚሆን Eንደሚሆን Aድረገው Eርዳታውን
Aከፋፈሉ ! ወገን ለወገን ደራሽ መሆኑን ለማየት ፣ ለመስማት ብሎም የመከራው ቀን በጎ
ስራ Eማኞች ለመሆንን ታደልን !
ይቅርታው ...
Aርብ ምሽት - የወገን ለወገን ደራሽ ኮሚቴ መደበኛ ስብሰባ Aድርገን Aንዱን
Aንስተን Aንዱን ስንጥል Aመሸን ። Eኩለ ሌሊት ስብሰባው ሲከወን የኮሚቴውን Aካሔድ
ለማስተካከል የተወሰደው ውሳኔ ተላለፈ፣ ከጎናችን ሆነው ደፋ ቀና የሚሉትን ወገኖች
Aስከፋ : ( ውሳኔው መተግበር ቢኖርበትም ከውሳኔው በፊት መስራት ያለብንን ስራ
ባለመስራታችን ወንደሞቻችን Aስቀይመናል! የሚሰራ ይሳሳታል ፣ ስንሰራ ተሳስተናል!
ይቅርታችን የከበደ ነው ! የAካሔድ ጠፋቱ Aካል ነበርኩና ያች ምሽት ለEኔ ከባድ ነበረች
... የከበደኝ መሆን ያለበት ወገንን ለመታደግ የሚደረገውን ሂደት ለማስተካከል
የተደረሰበት ውሳኔው ሳይሆን ቡና Eየጨለጡ የሚፈላሰፉ በበዙበት ከባቢ ደጋግ በጎ
Aድራጊ ወንድሞቻችን በማስከፋታችን ነበር! በዚሁ ስብሰባ "ገጽታችን Eንገንባ! "
የምትለው የAንዳንድ ወገኖች Aካሔድ Aንድምታ ግራ ሲያጋባኝ Aለም Aቀፉን ህብረት
Eየነቀነቀ ያለውን የወገን ለወገን የመድረስ Aላማ ወደ ሌላ Aቅጣጫ የሚጎትት ምሽት ላይ
በስልክ ካደረግኩት የራዲዮ ውይይት ጋር በAንድና በሌላ Aቅጣጫ ሲሳሳብ ከፊቴ ተደቀነ!
ስብሰባው Eኩለ ሌሊት ተጠናቀቀ! ... ወደ ቤት ገብቸ Eንዲህ ስል የተጎዳ ስሜቴን
Eንዳሻኝ ስሜት ህመም ፣ ተስፋ ህልም ስጋቴነወ Eንዳሻኝ በምገልጽባት የፊስ ቡክ ገጼ
ተነፈስኩት ...ተቃዋሚው ባንድ ወገን መንግስትና ደጋፊው በሌላ ወገን ይሳሳባሉ ፣ ሁለት
ዝሆኖች ይታገላሉ ፣ ድሃ መውጫው ቀዳዳ ጠቦታል ፣ ወገኔ ከዝሆኖች ጥል ስር የበቀለ
ያልታደለ ሳር ሆኖ ይደቆሳል ፣ የባሰውኑ ታምሜ Aመሸሁ ! Aይመሽ የለም መሽቶ
ከተማሩ ከተመራመሩ ፣ ከወለዱ ከከበዱት ወንድሞቸ ጋር ወገኔን መረጃ ከማቀበል
በተግባር ወደ መርዳት ልሸጋገር ስብሰባ ተቀመጥኩ ! ትልልቆቹ Aንሰን ቢታየኝ ህምም
ታምሜ Eኩለ ሌሊት ወደ ቤት ገባሁ ! ያየሁ የሰማሁ የሆነውን ለመርሳት Eየሞከርኩ
Aይተኛ የለም ተመስገን ብየ ተኛሁ ! ዛሬ Eንጃ ! የማውቀው የትናንቱን ክፉ ቀን ነው ! በተስፋ የተጀመረው ቀንና የምስራቹ ...
Eለተ ሰንበት ቅዳሜ - በልጀ የማለዳ ሳቅ ታጅቤ በተስፋ ተነሳሁ ... Eንዲህም Aልኩ
...ዛሬ Eንጃ ! የማውቀው የትናንቱን ክፉ ቀን ነው ! ልጀ ሆይ! መውለድ ደጉ ዛሬን ባንች
ፈገግታ በተስፋ ሊጀመር ነው ! ተመስገን ! ተመስገን ! ተመስገን ! መልካም ቀን
ለሁላችሁ!
የEኔን የሃጥUን ጸሎት ሳይሆን ልጆቻቸውን ታቅፈው ጨንቋቸው ፣ ጮኸው ሰሚ
ያጡትን ወገኖች ሃያሉ Aምላክ Aልተዋቸውም! EግዚAብሔር Aምላክ በስደት የተሰበረውን
የወገኖቻችን ጉዳት ሰማ ! የጨነቃቸው የጠበባቸው በደስታ ፊስታ ተናኙ ! በጭንቀት
ሁከት የሰነበቱት ወገኖች ወደ ሃገር ቤት ለመሄድ ዝግጅት መጠናቀቅ መረጃ የደረሰኝ
በተስፋ የጀመርኩትን ቀን የሚያበላሽ ቧልት ሰምሁና Aዘንኩ ። ሞራል ያጡ ፣ በወገን
ችግር ጀርባ በቪዛ ሽያጭ ፣ በድለላ Eና በመሳሰሉት ጥቅምን በማጋበስ የለመዱ ክፉዎች
በዚህ ክፉ ቀን Eንኳ ስለሚንገላታው ወገን Aይጨነቁም! ለጆቻቸውን ስለሚያስተምሩበት
ትምህርት ቤት Eያደር መበለሻሸት ግዳቸው Aይደለም! Eናም ተበሳጭቸ ከጅዳ ኮሚኒቲ
ካፍቴርያ Eንደወጣሁ ስልክ ተደውሎ የምስራች መልEክት ደረሰኝ!
" ነቢዩ ደስ ብሎናል ! Eንኳን ደስ ያለህ ! ትናንት Eየደወልን ስጨናንቅህ የነበርነው
ሁላችንም ወረቀታችን Aልቆልን ወደ ጅዳ Aየር መንገድ Eየተጓዝን ነው! " ተመሳሳይ
የስልክ ጥሪ ደረሶኝ ተመሳሳይ የምስራች ሰማሁ! ዛሬ ለቅሶ የለም! Eኒያ ሲንገላቱ የሰነበቱ
ወገኖች ሳቅ በሳቅ ሆነው ፣ በደስታ ተውጠው የምስራቹን ሲያበስሩኝ የተሰማኝ ደስታ ወሰን
የለውም ! Aዎ ወደ Aራት ሽህ የሚገመቱት ወገኖች የሃገራቸውን መሬት ለመርገጥ
መታደላቸው በEርግጥም ታላቅ የምስራች ነው ! ተመስገን !
ከሽሜሲው ግጭት የምንማረው ...
ከሽሜሲው ግጭት ብዙ ልንማር ይገባል ። በጅዳ ቆንስል የቅርብ ርቀት ከትመው
ለሳምንት ከቆዩ በኋላ ወደ ሺሜሲ መጠለያ በወገን ትብብር የተወሰዱት ወገኖች
በመጠለያው ግቢ Eንዳይገቡ ተደርገው ነበር። በጠራራው ጸሃይ በAውቶቡስ Eና በሜዳ
ላይ ያለ ምግብና ወሃ መሰንበታቸውን የጅዳ ቆንስል ሰራተኞችና ሃላፊዎች ወደ መጠለያው
ሲገቡና ሲዎጡ ይመለከቷቸው ነበር ። ያም ሆኖ ከሶስትና ከAራት ቀናት በላይ ህጻናትን
የያዙተን ጨምሮ Aቅመ ደካማ Eህቶች በወሃ ጥማት ሲጠበሱና በርሃብ Aንጀታቸው
ሲታጠፍ ከቅርብ ርቀት ያሉት የቆንስል መስሪያ ቤቱ ሰራተኞችና ሃላፊዎች መፍትሄ
Aላፈላለጉላቸውም። በዚህ መሰል Aስከፊ ሁኔታ ህጻናት ደክመው ፣ ነፍሰ ጡር Eህቶች
ደክመው ፣ የተወሰኑት AEምሯቸው ተነክቶ ታዝበናል። የሁከቱ መንስኤ ለቀናት በርሃብና
በውሃ ጥማት የተቸገሩት ግፉAኑ ወገኖች ትEግስት ማጣት Eንጀ ሁከትን ለማስነሳት ታቅዶ
የተፈጸመ Eንዳለሆነ ግልጽ መሆን Aለበት!
" ወደ መጠለያ Aስገባሁ !" ብሎ በመጠለያው በር ሜዳ ላይ ያፈሰሳቸውን የሳውዲ
መንግስት Aካል ከመሞገት ባለፈ ይህን መሰል Aስነዋሪ ስራ Eንዳይሰራ የጅዳ ቆንስል
ሃላፊዎች መስራት የነበረባቸውን ስራ በበቂ ሁኔታ ሰርተዋል Aልልም። የጅዳ ቆንሰል
ሃላፊዎች ወደ መጠለያው የተላኩ ዜጎቹን ጉዳይ በEግር በEግር ተከታትለው ማስፈጸም
ነበረባቸው። ይህ Aልተደረገም ወይም ተደርጎ Aልተሳካም ይሆናል። በAንድ Aቅጣጫ
ያልተሳካውን በሌላ Aቅጣጫ ለማስፈጸም የቆንስሉ ሃላፊዎች ያደረጉት ሙከራ Aንድ ሁለት ቀን ቢከሽፍ ከAራት ቀን በላይ መጓተቱ ዲፕሎማቶቻችን ከፍተኛ ጫናን ፈጥረው
ጉዳዩን በማስፈጸሙ ረገድ Eንዳልተሳካላቸው በግልጽ ያሳያል። የሳውዲ መንግስት Eና
የጅዳ ቆንስል ሃላፊዎች በፈጻሚና Aስፈጻሚ Aለካት መካከል መግባባት ቢኖር ኖሮ ዜጎችን
ወደ መጠለያው Eንኳ ማስገባት ቢገድ ካሉበት ቦታ ምግብና ውሃ በማቀበል Aጠቃላይ
ሂደቱን መቆጣጠር ይቻል ነበር። በሂደቱን የጅዳ ቆንስል ሃላፊዎች በቅርብ ተከታትለውት
ቢሆን ኖሮ Aነወዱ Aንኳ ቢያስቸግር የጉዳዩን Aሳሳቢነት ለማስረዳት ከከፍተኛ የሳውዲ
መንግስት ሃላፊዎች መድረስ ይችሉ ነበር። ከዚህ በተጓዳኝ ለመገናኛ ብዙሃን በAሰራር
የሚገጥማቸውን መሰናክል በማቅረብ ድምጻቸውን ሊያሰሙ ይገባ ነበር ። ይህ Aልሆነምና
ትኩረት ባለመሰጠቱ ሰው ተራበ ተጠማ ሁኔታዎች ከቁጥጥር ውጭ ሆኑ ! ወደ ዝርዝር
ሳንገባ ካለፈው ጥፋት ልንማር ግድ ይለናል! ካለፈው ስህተት ከተማርን ከተመሳሳይ ሁከት
ልንድን Eንችላለን !
የማይበጀን ሁከት ፣ የማይፈይድልን መረጃ ....
ይህን መሰል ችግር መቅረፍ የሚቻለው ሁላችንም ያገባናል ብለን በህብረት ስንደጋገፍ
ብቻ ነው! ሰላማዊ ሰልፍ Aና የAደባባይ ላይ ተቃውሞ በማይፈቀድ በማይታሰብባት
ሳውዲ Aረቢያ ችግር Eንኳ ቢሆር የሚፈታባቸውን መንገዶች ከማፈላለግ ባለፈ ሁከት
Aመጽን መከተል Aይጠቅመንም። ወደ ሁከት የሚወስደውን ሁሉ Eንቅስቃሴ በማስዎገድ
Eና መረጃን በመለዋወጥ ችግሮች Eንዲሰሙ ማድረግና ማስተካከል ይቻል ይመስለኛል!
በነጻነት መረጃን ከተለዋወጥን የማይቻል የለም ይቻላል! ነዋሪውን ለማረጋጋረት ብሎ
ያልሆነውን ሆነ ብለን "የዋሽቶ ማስታረቅ! " ዘይቤ ፍጹም Aይበጀንም! ገጽታን Eናሳምር
ምናምን ብለን "ቅባቱን " ተጠቅመን መረጃውን Eና Eውነቱን ካዛባነው መረጃው ዘባተሎ
ይሆናል ፣ ከዚሁ ጋር ችግሩን ለመታደግ የምንወጣ የምንወርደው ሁሉ የተዛባው ባለቅባት
መረጃ ተAማኒነትን ያሳጣናልና ድካሙን ሁሉ የEንቧይ ካብ ያደርገዋልና ጥንቃቄ
ማድረግ ይገባል : )
የስኬቱ ባለድርሻዎች ...
በመላ ሳውዲ ችግሩ በEኛ ላይ ከጠና ወዲህ ወገኖቻችን ወደ ሃገራቸው Eንዲገቡ
የሚደረገው ስኬት በተወሰኑ ግለሰቦች ወይም ቡድኖች የተከወነ Aይደለም ። በሃገር ቤት
በውጭ ሃገር ያሉ ወገኖች በሳውዲ መንግስት ላይ ያሳደሩት ተጽEኖ ፣ በሳውዲ Aረቢያ
የተለያዩ ከተሞች የምንገኝ ሁላችንም በህብረት የሰራነው ስራ ውጤት ነውና ደስ ሊለን
ይገባል! ምስጋናውም ለሁሉም ነው ! ወገንን መደገፍ ምስጋና ካስፈለገው ማለቴ ነው ...
ደስ ሲል ...!
ለወገን ደራሹ ወገን ነው ፣ በህብረቱ ፣ Eንበርታ !
ነቢዩ ሲራክ
ምንጭ የኢትዮጵያ ሜዲያ መድረክ
Subscribe to:
Posts (Atom)





